
Category: ሌ/ጄ ጻድቃን ገብረትንሳኤ – General Tsadkan Gebretinsae
ጄኔራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ (General Tsadkan Gebretinsae) ነባር የህወሓት ታጋይ ሲሆኑ፣ ከ1971 ጀምሮ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል፣ ማሌሊት ሲቋቋም ከመጀመሪያዎቹ 9 የፖሊት ቢሮ አባላት አንዱ የነበሩ ሲሆን እንዲሁም ከ1977 ጀምሮ እስከ1983 የህወሓት ሠራዊት ቺፍ ኦፍ ስታፍ ሆነው ታግለዋል፡፡ በ1987 ህገ-መንግስቱ ሲጸድቅ ከህወሓት አመራርነት ተሰናብተዋል፡፡
ፃድቃን ከ1983-1993 የሀገር መከላከያ ሠራዊት ኤታማጆር ሹም ሆነው የመሩ ሲሆን በ1993 በጡረታ ሲሰናበቱ በወታደራዊ ማዕረግ ሌፍተናንት ጄኔራል (ሌፍተናል ጄኔራል) ማዕረግ ደርሰው ነበር፡፡
በትምህርት ረገድ ከጆርጅ ዋሽንገተን ዩኒቨርሲቲ የዓለም ዓቀፍ ፖሊሲና ትግበራ ማስተርስ ዲግሪ፣ ከኦፕን ዩኒቨርሲቲ በቢዝነስ አድሚኒስተሬሽን ማስተርስ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆን፤ በዓለም አቀፍ ሕግ በአመስተርዳም ዩኒቨርሲቲ ተከታትለው በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ሳቢያ ሳያጠናቅቁ ቀርተዋል፡፡
በተመድ አማካኝነት በደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ወታደራዊ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል፡፡
[Also spelled as ሌ/ጄ ፃድቃን ገ/ትንሳኤ; General Tsadkan Gebretensae, General Tsadkan Gebretinsae]
[caption id="attachment_16432" align="alignnone" width="640"]

(ሪፖርተር ጋዜጣ) ኢሕአዴግ ሥልጣን ከተቆጣጠረ ጀምሮ በሽግግሩ ጊዜና ከሽግግሩ በኋላም በአጠቃላይ ለሰባት ዓመታት የጦር ኃይሎች.
(ፃድቃን ገ/ትንሳኤ – ሌተናል ጄኔራል) መግቢያ የኢትዮጵያ መንግሥት እስካሁን ድረስ በኤርትራ ላይ ሲከተለው የነበረውን ፖሊሲ.
በስራ ላይ ያለው የብሔራዊ ደህንነትና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በቀይ ባህር ላይ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ለኢትዮጲያ ያላቸውን.
ሌፍተናንት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ‹‹የሃገራችን ፖለቲካዊ ሁኔታና የመፍትሔ ሃሳቦች›› በሚል ርዕስ ባቀረቡት.
(ሌተናል ጄኔራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ) መግቢያ ከሃያ አምስት ዓመት ኢህአዴግ የደርግን መንግስት በጦርነት አሸንፎ የሀገራችንን ፖለቲካዊ.
Editor’s note:በቅርቡ ከጄ/ል ጻድቃን ጋር ያደረግነውን ቃለ-መጠይቅ በተከታታይ ማቅረባችን ይታወሳል፡፡ በቃለ-መጠይቁ ከተነሱት ርዕሰ-ጉዳዮች በተወሰኑት ላይ.
የቀድሞው ጠ/ሚኒስተር መለስ ዜናዊ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት አፈጻፀም ሂደት ላይ የነበራቸው አቋም በወቅቱ ከነበረው የጋራ.
የደርግ ሥርዐት መገርሰስን ተከትሎ የቀድሞው ሠራዊት እንዲበተን ቢደረግም 9,000 ገደማ ወታደራዊ ኤክስፐርቶች የአዲሱ መከላከያ ሠራዊት.
* የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ለሻዕቢያ አሉታዊ የሆነ አቋም ያለማቋረጥ ይይዙና ይወተውቱ ነበር * የህወሓት/ኢህአዴግ.
ከ1971 ጀምሮ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት የህወሓት ከፍተኛ አመራር የነበሩት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ‹‹እኔ.