[Video] ጄኔራል ጻድቃን – የዕርዳታ ገንዘብ ከሕዝብ ቀምተን ለመሣሪያ ስናውል አላውቅም

ከ1971 ጀምሮ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት የህወሓት ከፍተኛ አመራር የነበሩት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ‹‹እኔ የማውቀው ከደርግ ከሚገኘው ንብረት አብዛኛውን ከሕዝብ ስንካፈል እንጂ ከውጭ ለእርዳታ የመጣውን ገንዘብ ከሕዝብ ቀምተን ለጦር መሣሪያ ስናውል አይደለም›› አሉ፡፡Photo - General Tsadkan

ጄኔራሉ ይህን ያሉት ባለፈው ሰኞ ጥር 30-2007 ባደረግንላቸው ቃለ-መጠይቅ ላይ፡- ለ1977ቱ ረሀብ የመጣው ዕርዳታ ለድርጅት ሥራ እንዲውል ተደርጓል ስለሚለው የዶ/ር አረጋዊ በርኸ ስሞታ ላቀረብንላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ነው፡፡ ዶ/ር አረጋዊ ከቀደምት የህወሓት አመራሮች አንዱ ሲሆኑ የማርክሳዊ ሌኒናዊ ሊግ ትግራይ(ማሌሊት) ምሥረታን ተከትሎ ከድርጅቱ ለቅቀው በአውሮፓ የሚኖሩ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ዶ/ር አረጋዊ ለዕርዳታ ከመጣው ገንዘብ 50 በመቶ ለማሌሊት ማጠናከሪያ፣ 45 በመቶ ለወታደራዊ ወጪ ተመድቦ 5 በመቶ ብቻ ለሕዝብ እንዲውል በማዕከላዊ ኮሚቴ ተወስኖ ተግባራዊ ተደርጓል የሚሉ ሲሆን፤ በወቅቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ግን የዛሬ 5 ዓመት በአሜሪካ ራዲዮ አማርኛ ፕሮግራም ላይ በሰጡት አስተያየት እንደዚያ ዓይነት ውሳኔ አልተወሰነም በማለት መቃወማቸው ይታወሳል፡፡

በሌላ በኩል በቅርቡ ሌላው የቀድሞ የድርጅቱ አመራር ገብሩ አሥራት በቅርቡ ባሳተሙት መጽሐፍ፡- በወቅቱ ድርጅታዊ ድጋፍ የሚያደርጉ መንግስታት የሚጠቀሙት መሥመር ያንኑ የሰብዐዊ ዕርዳታ የሚመጣበትን መሥመር በመሆኑ እና ሁሉም ገንዘብ አንድ ቋት ውስጥ የሚገባ በመሆኑ ስሞታው የወቅቱን አሠራር ካለመገንዘብ የሚመጣ ነው የሚል አጭር አስተያየት አስፍረዋል፡፡

እነዚህን አስተያየቶች በመጥቀስ ጥያቄ ያቀረብንላቸው በወቅቱ የማለሌሊት/ህወሓት ፖሊት ቢሮ አባል እና የሠራዊቱም ቺፍ ኦፍ ስታፍ የነበሩት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ስሞታውን አጣጥለውታል፡፡

በወቅቱ በተለይ በረሀቡ የተጠቃው የራያ(ደቡባዊ ትግራይ) አካባቢ ሀላፊ የነበሩት ጻድቃን የገንዘብ አወጣጥ የመቆጣጠር ሀላፊነት የሳቸው ሳይሆን የማሕበረ-ኢኮኖሚ ክፍል መሆኑን ከጠቀሱ በኋላ ‹‹እኔ የማውቀው ከደርግ ካገኘነው ንብረት አብዛኛውን ከሕዝብ ስንካፈል እንጂ ከውጭ ለዕርዳታ የመጣውን ገንዘብ ከሕዝብ ቀምተን ስንካፈል አይደለም›› ብለዋል፡፡ የዕርዳታ ገንዘብ ለማሌሊት ምሥረታ ግብዣ ዋለ የሚለውን ስሞታም አጣጥለው የታጋዩን ቀለብ ከተቸገረው ሕዝብ ጋር ይካፈል እንደነበር አውስተዋል፡፡

የጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤን ሙሉ አስተያየት ከታች ባለው ቪዲዮ ላይ ይመልከቱ፡፡

——

Watch Video below.

*************

ተዛማጅ፡- ማሌሊት መሠረታዊ ወታደራዊ ለውጥ አምጥቷል – ጄኔራል ጻድቃን [Video]

 

Daniel Berhane

more recommended stories