በጦርነቱ ወቅት በመሣሪያ ግዥ ላይ የመለስ ዜናዊ ተቃውሞ አገር ለመጉዳት አልነበረም – ጄ/ል ጻድቃን [+video]

የቀድሞው ጠ/ሚኒስተር መለስ ዜናዊ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት አፈጻፀም ሂደት ላይ የነበራቸው አቋም በወቅቱ ከነበረው የጋራ አመለካከት ሊከሰት የሚገባው ተፈጥሮአዊ ክስተት ነው እንጂ አገር ለመጉዳት በማሰብ አይደለም በማለት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ገለጹት፡፡

ጄኔራሉ ይህንን የተናገሩት፤ በጦርነቱ ወቅት መለስ ለጦር መሣሪያ ግዥ በሚወጣው ገንዘብ መጠን ላይ ተቃውሞ ነበራቸው የሚለውን ስሞታ በመጥቀስ ላቀረብንላቸው በሰጡት ምላሽ ነው፡፡

አንዳንዶቻችን ኤርትራ ልትወረን ትችላለች ብንልም ሌሎች አትወረንም የሚል አመለካከት እንደነበራቸውም ጠቅሰዋል፡፡

Photo - General Tsadkan during an interview with HornAffairs. Feb. 2015
Photo – General Tsadkan during an interview with HornAffairs. Feb. 2015

የሀገር መከላከያ ሠራዊት ኤታማጆር ሹም የነበሩት ጄኔራል ጻድቃን፡- ጦርነቱ ድንገት የመጣ ቢሆንም የመከላከያ ሀይሉን የማደራጀት ሥራ ሲሠራ የነበረ መሆኑን የገለጹት ጄኔራል ጻድቃን፤ በዚህም ረገድ በአንድ ሚሊየን ፓውንድ ክፍያ የእንግሊዝ ኤክስፐርቶችን በመቅጠር የአየር ሀይል እና የአየር መከላከያ ሲስተም ጥናት መሠራቱን፣ የመካናይዝድ፣ ፓራኮማንዶና ኮማንዶ ሀይሎች ስልጠና እና የመሳሰሉ እንዲሁም የአዲስ ምልምል ወታደር የትምህርት ደረጃ 10ኛ ክፍል እንዲሆን እና የነባሩንም ትምህርት የማሳደግ ተግባራት መካሄዳቸውን አውስተዋል፡፡

እነዚህ ይህም በጦርነቱ ወቅት የሠራዊታችንን ብዛት ከ55,000 ወደ 350,000 ሲያድግ ያንን ሊሸከም የሚችል አቅም እንዲኖር ማስቻሉን አስረድተዋል፡፡

በጦርነቱ ወቅት የሴንትራል ኮማንድ አባል የነበሩት ጄኔራል ጻድቃን፡- መለስ ዜናዊ ለጦር መሣሪያ ግዥ በሚወጣው ገንዘብ መጠን ላይ ተቃውሞ እንደነበራቸውና ‹‹ሌሎች ፕሮግራሞችን ሳናፋልስ ባለው በጀት ጦርነቱን እንፈጽም›› የሚል አቋም እንዳራመዱ ያረጋገጡ ቢሆንም፤ ያ አቋም ግን ሁሉም አመራር ይጋራው ከነበረው ለኢኮኖሚ ቅድሚያ ከመስጠት አመለካከት የሚመነጭ አድርገው እንደሚረዱት እንጂ፤ ‹‹አንዱን ለመወንጀል ሌላውን [ለማመስገን] አልጠቀምባቸውም›› ብለዋል፡፡

የጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤን ሙሉ አስተያየት ከታች ባለው ቪዲዮ ላይ ይመልከቱ፡፡

——

Watch Video below

*************

ተዛማጅ፡-

* ማሌሊት መሠረታዊ ወታደራዊ ለውጥ አምጥቷል – ጄኔራል ጻድቃን [Video]

* [Video] ጄኔራል ጻድቃን – የዕርዳታ ገንዘብ ከሕዝብ ቀምተን ለመሣሪያ ስናውል አላውቅም

* በሽረ ጦርነት ዋዜማ ሻዕቢያ ተስፋ ቆርጦ ነበር – ጄኔራል ጻድቃን [+Video]

* ከቀድሞ ሠራዊት ‹‹ክሬም›› የሆነውን ክፍል እንዲቀጥል አድርገናል – ጄኔራል ጻድቃን [+Video]

Daniel Berhane

more recommended stories