ባለፈው ሳምንት አዲስ አድማስ ጋዜጣ የዘገበውና (እዚህ ብሎግ ላይም የወጣ) ዜና፤ በበቤንሻንጉል ክልል የሰፈሩ ዜጐች “ሕገወጥ” ተብለው እንደተባረሩ መዘገቡ ይታወሳል፡፡ ዜናው እንዳለው ከሆነ፡-
“በሚኖሩበት አካባቢ የእርሻ ቦታ በማጣታቸውና የተሻለ ሥራ ፍለጋ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ ከአማራ ክልል ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያሶ ወረዳ ተዘዋውረው የከተሙ በርካታ ሰዎች በወረዳው ባለሥልጣናትና ፖሊሶች፤ ሰብአዊ መብታቸው ተጥሶ ከቀያቸው መፈናቀላቸውን…ገለፁ፡፡
የያሶ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ሻምበል ዳኛ በበኩላቸው ‹‹ከየትኛውም ክልል የሚመጡ ሰዎች ለወረዳው ካላሳወቁና ካላስፈቀዱ ሕገወጥ በመሆናቸው ወደ የመጡበት እንዲመለሱ ስምምነት ላይ ደርሰናል›› ብለዋል፡፡ ቅሬታ አቅራቢዎቹ እንደሚሉት፤ ካለፉት ስምንት ዓመታት ጀምሮ ይኖሩበት ከነበረው ክልል የመሸኛ ደብዳቤ አምጥተው በያሶ ወረዳና በየቀበሌዎቹ የነዋሪነት መታወቂያ ስለተሰጣቸው ጎጆ ቀልሰው ይኖሩ እንደነበር ይናገራሉ፡፡” (ሙሉውን ለማንበብ – በቤንሻንጉል ክልል የሰፈሩ ዜጐች “ሕገወጥ” በሚል ተባረሩ – click here)
ተመሳሳይ ጭብጥ ያላቸው ዘገባዎች በተለያዩ ሚዲያዎች በተለያየ አቀራረብ የቀረቡ ሲሆን፤ እንደተለመደው ኢሳት ጉዳዩን አንድ ደረጃ ከፍ በማድረግ 59 የተፈናቀሉ ሰዎች በጉዞ ለላይ ሞቱ ብሏል፡፡ ይሁንና የመኢአድ (የኢንጅነር ሀይሉ ሻውል ፓርቲ) ሀላፊዎች ስለሞት መረጃ እንደሌላቸው ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡
በአሜሪካ ሀገር የሚገኝ በአማርኛ የሚተላለፍ የኢትዮጲያውያን ሬዲዮ (Ethio-Civility forum) ጉዳዩን አስመልክቶ ከቤንሻንጉል/ጉሙዝ ክልል ፕሬዚዳንት አሕመድ ናስር ጋር ቃለ-ምልልስ ከትላንት ወዲያ አድርጓል፡፡
ወደ 30 ደቂቃ ከወሰደው ቃለ-መጠይቅ ውስጥ በርዕሰ-ጉዳዩ ላይ ከሰጡት ምላሾች የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
ከተሞችን አስመልክቶ፡-
ከከተማ የተፈናቀሉ ሰዎች ስለመኖራቸው መረጃ የላቸውም፡፡ ሊፈፀም የሚችልበት አግባብም የለም፡፡ የአካባቢው ተወላጅ በሆቴልና መሰል ንግዶች መሠማራት ባህል እንደሌለው እና ባለስልጣኖቹ ራሳቸው በመሀል ሀገር ሰዎች ንብረት በሆኑ ሆቴሎች እንደሚጠቀሙ ጠቁመዋል፡፡ ‹ችግሩ› በገጠር እንጂ በከተማ የለም ብለዋል፡፡
ገጠሩን አስመልክቶ፡-
– በክልሉ ከማጂ ዞን ባለ አንድ ወረዳ 1700 ሰዎች እንዲነሱ እንደተደረጉ መረጃ እንዳላቸው ገልፀዋል
– የሞተ ሰው የለም/መረጃ የለኝም/ ካሉ በኋላ፤ እንዲያውም ከወረዳው ባገኙት መረጃ መሠረት ተወያይተውና ሕገወጥ መሆናቸውን ተማምነው፣ ከ 20-25 ቀን ጊዜ ተሰጥቷቸው ምርታቸውን ሰብስበውና ራሳቸው መኪና ተከራይተው እንደሄዱ ነው ብለዋል
– ጉዳዩን ያስፈፀመው የወረዳው መስተዳድር መሆኑን፤ ‹ክፍተት› መኖሩን እና ሰው ልከው ማጣራታቸውንና ያም ሰው አጠናቅቆ ሐሙስ እንደተመለሰ ገልጸዋል
– በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር የአማራ ክልል <ጓዶች> መምጣታቸውን፤ አርብ መረጃ መለዋወጥና ውይይት እንደሚጀምሩ ጠቁመዋል፡፡
– የተነሱት ሰዎች አማራ ብቻ ሳይሆኑ ኦሮሞዎችም ጭምር ናቸው (ሌሎችም ብሔሮች ሊኖሩ ይችላሉ)፤ ዞኑንም የሚዋሰነው ከኦሮሚያ ክልል ጋር ነው ብለዋል፡፡
– አላግባብ የተፈፀመ ነገር ካለም ማስተካከያ እንደሚደረግ እና በአጥፊ ሀላፊዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀዋል፡፡
– በተጨማሪም ከ4 ዓመት በላይ የኖሩ፣ መታወቂያ የተሰጣቸው ሰዎች ተፈናቅለው ከሆነ እሱን ማስተካከል ይገባል ብለዋል፡፡
እንደአጠቃላይ የገጠሩን ሁኔታ አስመልክቶ ሲናገሩም፡-
– ከሌላ አካባቢ ሰዎች የሚመጡበት 2 ዋነኛ መንገዶች መኖራቸውን፤ እነርሱም፡- ‹‹ጉልበት ሽጦ›› ለመኖር ተቀጥረው የሚመጡ ወይም ጫካ መንጥረው በእርሻ የሚሠማሩ መሆናቸውን የተናገሩ ሲሆን፤
የመጀመሪዎቹን በተመለከተ መብታቸው መሆኑን አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ ‹‹ጉልበቱን ሸጦ የሚኖር ካለ፤ ዛሬም ነገም ይኖራል: ከወጣም ይገባል›› ብለዋል፡፡
ሁለተኛውን ዓይነት ማለትም ‹‹ጫካ መንጥረው በእርሻ የሚሠማሩ›› ያሏቸውን በተመለከተ የሰጡት አስተያየት ሲጠቃለል፡-
‹‹ፖሊሲው›› የሚለው ሰፈራ በየክልሉ ውስጥ ብቻ እንደሚካሄድ፤ ክልሎች ለሰፈራ ያዘጋጁት መሬት ካለቀ እና ከክልል-ክልል ሰፈራ አስፈላጊ ከሆነ የሚመለከታቸው ክልሎች ተነጋግረው የሚያስፈጽሙት እንደሚሆን ከጠቀሱ በኋላ፤
እስካሁን በተለያየ መንገድ (ሕጋዊ ባልሆነም መንገድ) ገብተው የቆዩና በነዋሪነት የሚታወቁትን በተመለከተ የሚስተናገዱበት መንገድ እንደሚፈለግ፤ ለቀጣይ ግን ይህ ቋሚ አሠራር ሊሆን እንማይችልና እንዲያውም ማበረታታት እንደሚሆን፤ ይህም ለሰዎቹ ለራሳቸውም ለክልሉም ጥሩ እንዳልሆነ ሀገር ይወቅልን ብለዋል፡፡
——
ማስታወሻ፡- ይህ ጭማቂ ሙሉውን ቃለ-መጠይቅ ዳውንሎድ (Download) ማድረግ ለሚቸግራቸው አንባቢያን ለመርዳት፤ በችኮላ የተጻፈና ቁንጽል በመሆኑ፤ ሙሉውን ቢያዳምጡት ይመከራል፡፡
* Download here (link) – የፕ/ት አሕመድ ናስር ጋር ቃለ-ምልልስ (size: 9.4 mb)
* For a better quality – listen here (link).
———
My comment:
What I gather from the Benishangul regional state President Ahmed Nasir’s interview about the recent evictions is that:
1/A scenario what political scientists call “local tyranny” – Wereda officials deciding matters of this scale and the President referring to their report as self-evident truth
2/Typical case of a higher official saying “I didn’t know” (Ethiopian bosses everywhere love this excuse)
3/A huge deficit of common understanding on the issues at stake
4/The absence of sufficient policy & legal framework, though we have been hearing about this kinds of issues for more than a year.
The bottom line: While the regional officials seem to be confusing federalism with separate statehood, it is the federal government who should provide sufficient legal framework to enable Ethiopians settle in any region they like – as long as they fulfill clearly stated legal requirements.
********
Thanx Shenkut.
1/He didn’t say which policy. But I think he is referring to policy documents on Agriculture and settlement.
2/He said there are also Oromos, when the journalist asked him whether Amhara was the target.
it”s difficult time for ethiopians. pls put our effort to deter this evil act……………
What does ‹‹ፖሊሲው›› የሚለው ሰፈራ በየክልሉ ውስጥ ብቻ እንደሚካሄድ፤
The Ethiopia Constitution is the governing law of the policy. If the policy contradict with the constitution the constitution need to be implimented. however, the issue is not about legal action.
In the mean time the president states that “ተፈናቃዮቹ ኦሮሞዎችም ናቸው “. What Does “ተፈናቃዮቹ ኦሮሞዎችም ናቸው ” mean? the whole issue is about Ethiopian citizens’ constitutional right. The question the Benishangul president asked was that do any Ethiopian citizens have the right in Benishangul region ?
በህገ መንግሰቱ መሰረት ወላጆቹ ወይም ከወላጆቹ አንዱ ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ነዉ/አንቀፅ 6/1/ ፡፡ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ደግሞ በህገ መንግሰቱ የተቀዳጃቸዉ መብቶች አሉት፡፡ እነሱም በህግ ይጠበቁለታል፡፡ እንደ ህገ መንግሰቱ ገለጻ ማለት ነዉ፡፡ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ ከፈቃዱ ዉጭ ዜግነቱ ሊገፈፍ አይችልም (አንቀጽ 33/1 )፡፡ ደግሞም ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ የኢትዮጵያ ዜግነት የሚያስገኘዉን መብት፤ ጥበቃ ና ጥቅም የማግኘት መብት አለዉ (አንቀጽ 33/2).፡፡ እንግዲህ የምናወራዉ ኅገመንግሽጹ በዜግነታቸዉ መብት ስላቀዳጃቸዉ ኢትዮጵያዉያን ዜጎችና መብታቸዉም በህገ መንግስቱ ስለሚጠበቅላቸዉ ዜጎች መሆኑን ለቅፅበት እንዳንረሳ፡፡
ህገ መንግስቱ ለማንኛዉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ የመዘዋወር ነፃነት በአንቀፅ 32 አጎናፅፎአል፡፡ አማራ ፤ ኦሮሞ ወይም ትግሬ ሳይል ስለመዘዋወር ነፃነት እንዲህ ይላል፡-ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ ወይም በህጋዊ መንገድ ሀገሪቱ ዉስጥ የሚገኝ የዉጭ ዜጋ በመረጠዉ የሀገሪቱ አካባቢ የመዘዋወርና የመኖርያ ቦታ የመመስረት እንዲሁም በፈለገዉ ጊዜ ከሀገር የመዉጣት ነፃነት አለዉ ፡፡ መቼም ግሩም ነዉ፡፡ እንኩዋን ኢትዮጵያዊ ይቅርና የሌላም አገር ዜጋ የመዘዋወር ነፃነቱ ተጠብቆለታል፡፡ እንዴዉም የኢትዮጵያዊዉን መብት የኢኮኖሚ የማህበራዊና የባህል መብቶች በሚልና በአንቀጥፅ 43 ስር እንዲህ አስፋፍቶ ያስቀምጥለታል፡-
o ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ በሀገሪቱ ዉስጥ በማንኛዉም ኢኮኖሚዊ እንቅስቃሴ የመሰማራትና ለመተዳደሪየዉ የመረጠዉን ስራ የመስራት መብት አለዉ (43/1)
o ሁሉም ኢትዮጵያዊ መተዳደሪያዉን ስራዉንና ሙያዉን የመምረጥ መብት አለዉ -43/2
o መንግሰት ለስራ አጦችና ለችግረኞች ስራ ለመፍጠር የሚያስችል ፖሊሲ ይከተላል -43/6
o መንግስት ዜጎች ጠቃሚ ስራ የማግኘት ዕድላቸዉ እየሰፋ እንዲሄድ ለማድረግ አስፈላጊ እርምጃዎችን ይወስዳል- 43/7
o ገበሬዎችና ዘላን ኢትዮጵያዉያን በየጊዜዉ እየተሻሻለ የሚሄድ ኑሮ ለመኖር የሚያስችላቸዉና ለምርት ካደረጉት አስተዋፅኦ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ተገቢ ዋጋ ለምርት ዉጤቶቻቸዉ የማግኘት መብት አላቸዉ፡፡ መንግስት የኢኮኖሚና የማህበራዊ የልማት ፖሊሲዎችን በሚተልምበት ጊዜ በዚህ መርህ መመራት አለበት-43/8
ታዲ በጥረታቸዉ ሀብት ያፈሩ ሰዎችን ፤ የዜግነት መብታቸዉን ተጠቅመዉ በሀገሪቱ ተዘዋዉረዉ ግብርናን ስራ አድርገዉ በመምረጥ በግብርና ላይ የተሰማሩ ዜጎችን ከሀገራቸዉ ማባረር ነዉ የሚገባዉ ወይስ በኢኮኖሚ እንዲጎለብቱ ፤ በባህል እንዲጠናከሩ በልዩልዩ ፖሊሲዎች መደገፍ ነዉ ተገቢዉ ህገ መንግስታዊ ትዕዛዝ?