የኢትዮ-ሶማሌ የፓርቲና የክልል አመራሮች የተፈናቃዮች መልሶ ማቋቋም ውሳኔ አሳለፉ

(አብዱረዛቅ ካፊ)

የኢትዮጵያ ሶማሊ ህዝብ ዴሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሩና የክልሉ ካቢኔ አባላት የክልሉ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አብዲ መሀሙድ ኡመርና የኢ.ሶ. ህ.ዴ.ፓ ሊቃመንበር አቶ መሀመድ ረሺድ ኢሳቅን ጨምሮ ከኢትዮጵያ ሶማሌና ከኦሮሚያ ክልሎች የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቄያቸው የሚመለሱ ውሳኔ አሳልፏል።

ወሳኔው የተላለፈው ዛሬ ቅዳሜ ኢትዮጵያ ሶማሊ ህዝብ ዴሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራርና የክልሉ ካቢኔ አባላት ዛሬ  ቅዳሜ ባካሄዱት ስብሰባ ላይ ነው።

በውሳኔው መሰረት፤ ከኦሮሚያ ክልል የተፈናቀሉ የሶማሌ ወገኖች በራሱ በክልሉ መንግስት ወደ ቄያቸው የማስመለስ ሥራ ከወዲሁ እንደሚጀመር እና ከሶማሌ ክልል የተፈናቀሉ ኦሮሞ ወንድሞች በተለይ በጅግጅጋና በሌሎች አከባቢዎች በተለያዩ ንግድ ሥራዎች ተሰማርቶ የነበሩ የኦሮሞ ወንድሞች ወደ ክልሉ የሚመለሱበት ስራ እንደሚሰራ  አስታውቋል።

ኦሮሞ ወገኖቹ ወደ ክልሉ በሚመጡበት ጊዜ ደማቅ የወንድማማችነት አቀባበል እንደሚደረግላቸው ክልሉ አስታውቋል።
ይህ ደግሞ ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጎች በአገራቸው በፈለጉት አከባቢ  ለመኖር እኩል ህገመስግስታዊ መብት ስላላቸው ነው ብሏል የክልሉ መንግስት።

መጨረሻም የክልሉ ህዝብ፣ የክልሉ መሪ ድርጅት ኢ.ሶ. ህ.ዴ.ፓ እና የክልሉ መንግስት፤ ከክልሉ የተፈናቀሉ  ኦሮሞ ወንድሞች በተለይ በተለያዩ የንግድ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው የነበሩ ኦሮሞ ወገኖች  ወደ ቀዬያቸው እንድመለሱ ጥሪ አቀርቧል።

********

Guest Author

more recommended stories