የኢትዮ-ሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት በወቅታዊ ችግሮች ላይ ሕዝብ አወያዩ

(አብረዛቅ ካፊ)

የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት ከተለያዩ ህብረሰብ ክፍሎች ጋር በወቅታዊ ክልላዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ተወያዩ።

በኢትዮጵያ ሶማሌና ኦሮሚያ አዋሳኝ አከባቢዎች የሚፈጠሩ ግጭቶችን ከመነሻው ለመፍታት የመሰረተ ልማት አቅርቦት ችግር ለማስወገድ ትኩረት ሰጥቶ መስራቱን የክልሉ ፕሬዚዳንት ተናገሩ፡፡

የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መንግሰት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አብዲ መሀሙድ ኡመር እና የክልል ምክር ቤት አፈጉባኤ ክቡር አቶ መሀመድ ረሽድ ኢሣቅ ከአገር ሸማግሌዎች፣ ከንግድ ማህበረሰብ አባላት የመንግስት አመራሮችና ሰራተኞች የተገኙበት መድረክ በጅግጅጋ ከተማ አካሄደዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የክልሉ ርእሰ መስተዳደር ክቡር አቶ አብዲ መሐሙድ በሰጡት መብራሪያ የኢትዮጵያ ሶማሌና በኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አከባቢዎች ለተፈናቀሉ ዜጎች መንግስት ከሚያደርግላቸው የምግብ፣ የመጠሊያና የህክምና ድጋፍ ጎን ለጎን የህብረተሰቡ ተሳትፎ አስፈላጊ ነው፡፡

Photo - Ethio-Somali president public discussion

ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ ለማሰባሰብ መላው የክልሉ ነዋሪዎች እና የዲያስፖራ አባላት ተሳትፎ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል፡፡ ተፈናቃዮችን መልሶ ለማቋቋም ልዩ ድጋፍ በማድረግ ከጎናቸው መቆም ከሁሉም ህብረተሰብ ክፍል እንደሚጠበቅ ነው የተናገሩት፡፡

ተፈናቃዮችን በዘላቂነት መልሶ ለማቋቋም ክልላዊ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ በመድረኩ የተመረጠ ሲሆን ለድጋፍ አገልግሎት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና በሀዋላ አካውንት መከፈቱንም ገልጸዋል፡፡

ክቡር ፕሬዝዳንቱ እንዳብራሩት አዋሳኝ የኢትዮጵያ ሶማሌና የኦሮሚያ ክልሎች ነዋሪዎች ለአመታት የነበረባቸው መሰረታዊ ልማት እጥረት ምክንያት ሲፈጠር የቆዩ ግጭቶችን ለማስወገድ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ በርካታ የገጠር መንገዶችና ድልድዮች በእነዚሁ አካባቢዎች መገንባታቸውን ነው የተናገሩት፡፡

የክልሉ ፕሬዚዳንት ባለፈው ሳምንት በጀረር፣ ቆራሓይና ዶሎ ዞኖች ያካሄዱትን ግዙፍ የውሃ ፕሮጅክቶች ምረቃ የህዝቡ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡና የአርብቶ አደሩን የውሃ ችግር በእጅጉ ያስወገዱ መሆናቸውን አብራርተዋል።

በዚህም የክልሉ መንግስት የውሃ እጥረትን ለመቅረፍ ባለፈው ሳምንት ሦስት ዞኖች የሚያስተሳስርና ከመነሻው ቢርቆድ፣ ጉነገዶ፣ ዲግ፣ መርስንና ጋሻሞ ወረዳዎች በማገናኘት 250 ኪሎ ሜትር ጥልቅ ጉድጓዶችና የውሃ ቧንቧ የተዘረጋ ሲሆን በየ5ኪሎ ሜትሩ የእንስሳት ውሃ መጠቀሚያ ገንዳና ማህበረሰቡ ውሃ የሚያገኝበት 36 ቦኖዎች ተገንብቷል፡፡

በጀረር ዞን ጋሻሙ ወረዳ በተፈጥሮ መሬት አቀማመጥ ምክንያት በቅርብ ርቀት ውሃ የማይገኝባቸው አከባቢዎች መካከል ባን-ሀጉጋ፣ ኤልበሓይና በሊ-ጀኖ ጋሻሞ ከተማ 150 ኪ.ሜ.ርዝመት ለሚገነቡ የውሃ ፕሮጀክቶች በርእሰ መስተዳደሩ የመሰረት ድንጋይ ተቀምጠዋል፡፡

የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ለተፈናቃዮች መልሶ ለማቋቋም ለሚደረገው ድጋፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ቃል ገብቷል፡፡

የተፈናቃዮች ችግር የወገኖቻቸው ችግር በመሆኑ የራሳቸው አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚያደርጉት ቃል ገብተዋል፡፡ የክልሉ መንግስት ዘርፋ ብዙ የልማት፣ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል፡፡

*********

Guest Author

more recommended stories