በጥንት ዘመን ምናልባት BBC በ DNA ጥናት አረጋግጨዋለሁ እንዳለው የዛሬ 3 ሺ አመት ገደማ ከአሁኗ ሌባንት/ሶሪያ አካባቢ(የመን አይደለም) ወደ ኢትዮጵያ የተደረገ ፍልሰት ነበረ፡፡ በሌሎች ሰነዶች መሰረት በዚህ ወቅት ባህር ተሻግረው ከአሁኗ ኢትዮጵያ ወይም ኤርትራ የሰፈሩት ነገዶች ስም ሀበሣትና አግዓዚያን ይባሉ ነበር፡፡ (ሸ ፊደል በጥንታዊ የኢትዮጵያ ሴሜቲክ ቋንቋዎች አልነበረም፡፡ ሀበሻ መባል የተጀመረው ሸ፣ቸ፣ጨ፣ኘ፣ . . . .የመሳሰሉ ፊደላት ከኩሽቲክ ቋንቋዎች የሴሚቲክ ቋንቋዎችን ከተቀላቀሉ በኋላ ነው፣ ሀበሻ የተባለውም ከዚያ በኋላ ነው)፡፡
እነኚህ ሁለት ነገዶች ልክ አሁን ሜጫ እና ቱለማ እንደምንላቸው የኦሮሞ ንዑስ ጎሳዎች የተለያየ ስም ይያዙ እንጂ በቋንቋ፣ በባህል፣ በማንነት፣ በዘር ፣ ተመሳሳይ ነበሩ፡፡ እነኚህ መጤዎች ቀይባህርን ከተሻገሩ በኋላ ራሳቸውን ጠብቀው ከመኖር ይልቅ በአካባቢው ይኖሩ ከነበሩ ነባር ህዝቦች ጋር መቀላቀል ነበር የጀመሩት፡፡ ነባር ህዝቦች ማለት በወቅቱ ኮንቴክስት ኒሎሰሃራ፣ ኦሞቲክና ኩሽቲክ ቋንቋ ተናጋሪዎችን ማለታችን ነው፡፡ በመሆኑም ሀበሻ የአንድ ብሔር ስም ሆኖ ያገለግል የነበረው መጤዎቹ ከነባሮቹ ጋር እስከሚቀላቀሉ ባለው ጊዜ ድረስ ብቻ ነበር፡፡ ከተቀላቀሉ በኋላ ስያሜው የሁሉም የጋራ መጠሪያ ነበር የሆነው፡፡
ይህ የቃሉ መሰረተ ታሪክ ነው፡፡
በሀገሪቱ እስካሁን ቅርስ የሚገኝለት የስልጣኔ ታሪክ የሚገኘው ከነዚህ ህዝቦች መምጣት በኋላ ነው፡፡ ያ ማለት ግን የአክሱም ስልጣኔ ባለቤቶች ሴማውያኑ ብቻ ናቸው ማለት አይደለም፡፡ አክሱም ሲዳከም ስልጣን የያዘው የዛጉዌ ስርወ መንግስት ከአክሱም ግዛት የተነሳ አማፂ እንጂ መጤ ወራሪ አይደለም፤ ያ ማለት ኩሻዊዎቹ አገዎች የአክሱም ስልጣኔ አካል ነበሩ ማለት ነው፡፡ በወቅቱ የአክሱም ስርወ መንግስት የነበሩ ኩሻውያን አገዎች ብቻ ናቸው ወይስ የደቡብ ኩሻውያንን እና ኦሞቲኮችንም ያካትት ነበር የሚለውን በእርግጠኛነት አላውቅም፡፡
በግራኝ አህመድ ወረራ እስከ ባሌ ይደርስ የነበረውን የያኔውን የክርስትያን ግዛት የሀበሻ ግዛት ነበር የሚሉት፡፡ የግራኝ ዘመቻንም ታሪክ ፀሀፊው ሐበሻን የማቅናት ዘመቻ ነበር የሚለው፡፡ በዛኔው ትርጓሜ መሰረት ከሶማሊ፣ አፋርና ሀረሪ በመለስ ያለው የኢትዮጵያ ግዛት ሐበሻ ነው የሚባለው (ያኔ መደወላቡ የመሸገው የኦሮሞ ጦር በሁለቱም ስር አልነበረም)፡፡
በጀምስ ብሩስ ዘመንም ሀገሩና ህዝቡ በዚሁ ስም ነበር የሚጠራው፡፡
የግራኝ አህመድ(አህመድ ገረዌ ይሉታል ሶማሌዎቹ) ወረራን ማክተም ተከትሎ ኦሮሞ የምስራቁንም ሙስሊም፣ የሰሜኑንና የምዕራቡን ክርስትያንም እየገፋ ሲስፋፋ እንደጥንቶቹ ሀበሣትና አግዓዚያን ሁሉ ራሱን ከመጠበቅ ይልቅ በየደረሰበት ሁሉ ተቀላቅሎ መኖርን ነበር የመረጠው፡፡ በዚህም በሂደት በኦሮሞ ህዝብ መካከል የባህል፣ ሀይማኖትና አኗኗር ብቻ ሳይሆን የመልክና ቁመና ልዩነት ሳይቀር እንዲፈጠር ነበር ያደረገው፡፡ የሸዋው ከሰሜኑ ክርስትያን ጋር ተመሳስሎ ሲኖር፣ የምዕራቡ(ወለጋና ጅማ) ደግሞ ከአካባቢው ህዝብ ጋር ተቀላቅሎ በሂደት የራሱን ፊውዳሊዝም ማዳበር ጀምሮ ነበር፣ የምስራቁ(ሐረርጌ) ደግሞ ከሶማሌዎች ጋር የስነልቦናና ሀይማኖት አንድነትን ያለው ሲሆን፣ የደቡብ ኦሮሚያና አጎራባቾቹ ደግሞ ከሞላ ጎደል ጥንታዊ ማንነታቸውን አስጠብቀው ቀጥለዋል፡፡ የሚኒልክ መስፋፋት ከጥቂት ሺ የሰሜን ኬንያ ኦሮሞዎች በስተቀር ሁሉንም ኦሮሞዎች ከነልዩነታቸው በአንድ ሀገር ጥላ ስር አሰባሰባቸው፡፡
በ1960ዎቹ ብቅ ያለው የሶሻሊስት ትውልድ ብሔርተኝነትን ሲያቀነቅን ነው ሀበሻ የሚለው ቃል ጥያቄ የበዛባት፡፡ አንዳንድ ኤርትራውያን ሀበሻ አይደለንም ማለት ጀመሩ፡፡ የተወሰኑ የትግራይ ብሔርተኞችም አግዓዚያን ነን በሚል የተለዬ ማንነትን ህዝቡ ላይ ለመጫን ጥረት ማድረግ ጀመሩ፡፡ ይህ ጥረት በደበዘዘ ሁኔታ እስካሁን የቀጠለ ቢሆንም እየተሳካላቸው ግን አይመስልም፡፡ ሀበሻነት ከኤርትራዊነት፣ ከትግራዋይነት ፣ ወይም ከኦሮሞነት ጋር የተደረበ ማንነት መሆኑ መገንጠልን ጨምሮ የትኛውንም ፖለቲካዊ አላማ የሚከለክል ባይሆንም የያኔዎቹ ፖለቲከኞች ግን ለመገንጠልም፣ ብሔርተኝነትን ለማጠናከርም ሆነ ፖለቲካዊ ድጋፍን ለማግኘት ልዩነት ላይ ማተኮር ስለሚፈልጉ ነው፡፡
ለምሳሌ የኦሮሞ ብሔርተኞች የመገንጠል አላማቸውን ለማሳካት እንደ ትግራይና ኤርትራ ተገንጣዮች የቪክቲምሁድ ፖሊቲክስን በስፋት በማራገብ፣ ህዝቡ የተለየ ህዝብነት ስሜት እንዲያዳብር የጋራ ባህሎች፣ እሴቶችና ሀይማኖትን በማጥቃት ላይ ሰፊ ስራ ሰርተዋል፡፡
በዚህ ወቅት ነበር ሀበሻ ማለት ሴማውያንን ብቻ የሚወክል ቃል እንደሆነ ተደርጎ አዲስ ትርጓሜ የተሰጠው፡፡ ይህ ዘመቻ ኤሊቶችንና ጠረፍ አካባቢ የሚኖሩ ኦሮሞዎችን በተወሰነ ደረጃ ሲማርክ የመሀል አገር ኦሮሞዎች ላይ ግን በቀላሉ ሊሰርፅ አልቻለም(በምዕራብ ያለውን ሁኔታ አላውቅም)፡፡ አሁንም ህዝቡ የአገር በቀል ምርቶችን የሀበሻ ጎመን፣ የሀበሻ ጥድ፣ የሀበሻ ዶሮ፣ . . . . ወዘተ እያለ ነው የሚጠራው፡፡
በዚህም አሁን ድረስ የአስተሳሰቡ አራማጆች በሶሻል ሚዲያዎች ጭምር ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሀበሻን የሴሜቲኮች ብቻ ስም እንደሆነ አድርጎ የማስረፅ ስራ እየሰሩ ነው፡፡ በዚህም ሀበሻ የጋራ ማንነት ስያሜ መሆኑ እንዲቀር ጥረት ያደርጋሉ፡፡
ሌሎችስ?
-እስከሀያኛው ክፍለዘመን ሁለተኛ አጋማሽ ድረስ ማህበራዊ፣ ታሪካዊ ትስስር ያላቸው የሰሜንና ማዕከላዊ ህዝቦች ራሳቸውን ሀበሻ ብለው ይጠራሉ፡፡ ለዘመናት ከሰሜኑ ጋር በክፉም በበጎም ተሳስረው የኖሩት ሴማውንና የሸዋ ኦሮሞዎች፣ አገዎች፣ቅማንቶች፣ ኢሮቦች፣ . . . .ወዘተ ሀበሻን የጋራ መጠሪያ አድርገው ሲጠቀሙበት ኖረዋል፡፡
-የኦሞቲክ ህዝቦች ራሳቸውን በሀበሻነት አይደንቲፋይ ያድርጉ አያድርጉ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ከግራኝ አህመድ ወረራ በፊት ግን የሐበሻ ግዛት አካል ነበሩ፡፡ በመሀል አገር ያሉት የደቡብ ተወላጆች ግን ሀበሻነትን ሁሉም የሚጠቀምበት ኢትዮጵያዊነትን እንደሚተካ ቃል እንጂ የተወሰኑ ብሔሮች መጠሪያ አድርገው አይደለም የሚጠቀሙበት፡፡
-እኔ እስከማውቀው ድረስ ፖለቲከኞች ብለውት ሳይሆን በራሱ ጊዜ እንደህዝብ ሀበሻ አይደለሁም የሚል ብሔር ሶማሊ ነው፡፡ ምስራቅ ኢትዮጵያ ውስጥ በሶማሊዎች ዘንድ ሀበሻ ትርጉሙ ከሴሜቲኮችም ጠቦ የአማራ መጠሪያ ተደርጎ ነው የሚያገለግለው፡፡ አማርኛ ቋንቋ በመደበኛ የሶማሊኛ መድረኮች (በሚዲያዎችም ጭምር) ብዙ ጊዜ አፍ-ሀበሽ ነው የሚባለው፡፡
-ጋምቤላዎችና ቤኒሻንጉሎችም ራሳቸውን ሀበሻ ብለው አያውቁም፡፡
-በሌላ በኩል ሴማዊ የሆኑት ሀረሪዎች ራሳቸውን ሐበሻ ነን አይሉም፡፡
-አረቦች ደግሞ መላውን ኢትዮጵያ ሀበሽ ብለው ነው የሚጠሩት፡፡ በሚዲያ ኢትዮጵያ የሚለውን ቢጠቀሙም ህዝቡ ግን ሀገሪቱንና ዜጎቿን ሀበሽ ነው የሚለው፡፡
አሁን ሁሉም መረዳት እንደሚችለው ኢትዮጵያዊነት ከሀበሻነት የሰፋ ነው፡፡ ግን ደግሞ ሀበሻነት ከሴማዊነት የሰፋ ነው፡፡ ሴሜቲክ ሳይሆኑ ራሳቸውን ሀበሻ ብለው የሚጠሩ በርካቶች ናቸው፡፡ እነኚህን ሴማዊ የሆኑት እና ያልሆኑት በጋራ ራሳቸውን ሀበሻ ብለው የሚጠሩት አንዱ ሌላው ላይ ማንነቱን ስለጫነ ሳይሆን ቀድሞውንም የጋራ ማንነት እንደነበረና አሁንም ድረስ በሁለቱም ወገን ያሉት ህዝቦች ሀበሻ እኔ ብቻ ነኝ ወይም እሱ ብቻ ነው የሚል አስተሳሰብ እንደሌለባቸው እናውቃለን፡፡
ሆኖም አሁን በተያዘው አካሔድ የብሔርተኛ ኤሊቶች ያላሰለሰ ጥረት ወደህብረተሰቡ ከሰረፀ ሀበሻነት የሴማውያኑ ብቻ መጠሪያ መሆኑ ላይቀር ይችላል፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ ፖለቲከኞቻችን የህዝቡ አስተሳሰቦች፣ ባህልና እሴቶች አጥንተው በዛ ላይ የተመሰረተ ፕሮግራም ከመቅረፅ ይልቅ የራሳቸውን ስሜቶች ህዝቡ ላይ መጫን የሚፈልጉ መሆናቸው በተደጋጋሚ ያየነው ነገር ነው፡፡
ፖለቲከኛ ማለት ግን የራሱን የጥበት፣ የጥላቻ፣ የትምክህት፣ . . .ወዘተ ስሜት ብዙሀኑ ህዝቡ ላይ የሚጭን ወይስ የብዙሀኑን ህዝብ ስሜት ተረድቶ ከዚያ አንፃር የሚንቀሳቀስ . . . . . . የእኔ አውቅልሀለሁ ሶሻሊስታዊ አስተሳሰብ ከነሰንኮፉ ወጥቶልን ህዝቡንና ስሜቱን/ ፍላጎቱን የምናከብረውና የምናገለግለው መቼ ይሆን?
**********
የኔ ወንድም ብዙ መዘባረቅ አያስፈልግም ወይ ኢትዮጵያዊ ነህ ወይ አይደለህም! ሐበሻ ፈላሻ ዓጋዘን ምን አመጣው? ሐበሻ የሚለው ቃል መሰረቱ ኢትዮጵያዊ
ሳይሆን ከደቡብ አረብ ነው። በአንዳንድ የአረብ ሃገሮች ውስጥ ትርጉሙ ድቅል ወይም ክልስ እንደማለት ሲሆን ሌሎች መረጃዎች ደግሞ ሐበሻት የሚባል ጎሳ ከየመን ወደ ኢትዮጵያ ፈልሶ ከኢትዮጵያውያን ጋር በመደባለቁ ሐበሻ የሚባለው ቃል የመጣው ከዛ ጊዜ ጀምሮ ነው ይላሉ። የአክሱም ነገሥታት ድንጋይ ላይ በቀረጹት ፅሁፋቸው እራሳቸውን የአክሱማውያን ሲሉ በሚገዙዋቸው ጎሳዎች ስም የኖባ ንጉሥ፣ የብሌሚ ንጉሥ፣ የሐበሻ ንጉሥ እያሉ ጽፈዋል።
በአሁኑ ዘመን ግን ሐበሻነት ፀረ-ኢትዮጵያዊ ideology እንጂ identity አይደለም አንዳንድ እውቀት ያነሳቸው enlightened ያልሆኑ inferiority complex የሚያጠቃቸው ወገኖች ከጥቁርነታቸው(ኢትዮጵያዊነታቸው) ለመሸሽ ሐበሻ የሚለውን ቃል በኢትዮጵያዊነት(ኩሻዊነት) ፋንታ ለመተካት ሲፍጨረጨሩ ይስተዋላሉ። የዛሬ ፫ሺሀ አመት የተደረገውን የዘር መዳቀል እያነሳ ዲቃላ ነኝ ሴማዊ ነኝ እያለ የሚፎክር ህዝብ ከኛው በቀር የትም ቦታ አይገኝም! ትላንት ከኬንያዊ አባት እና ከነጭ እናት የተወለደው ባራቅ ኦባማ እንኳን በጥቁርነቱ የሚኮራ ነው ዓለምም የሚያውቀው በጥቁርነቱ ነው። ለምን ቢሉ “ኩሻዊ ቁርበቱን ነብር ዥንጉርጉርነቱን ፍፁም አይለውጥም” ብሏል ነብዩ ኤርሚያስ።
የኛዎቹ “ሴማውያን” ግን ወደ እውነተኞቹ ሴማውያን ሃገር ሲሄዱ ነው ማንነታቸውን የሚረዱት። አረብ ሃገር አቢድ(ባርያ) እየተባለ ወንዱና ሴቱ የሚደፈረው ተዘቅዝቆ የሚገረፈው ይባስ ተብሎ ይህ ውርደት በቪድዮ ተቀርፆ online የሚለጠፈው ያው የኛው ጉድ ነው። እስራኤል ውስጥ ያሉት አይሁድ ነን የሚሉት ፈላሻዎች እንኳን “ኩሺም”(የኩሽ ዘሮች) እየተባሉ ነው የሚጠሩት። ቁጥራቸው እንዳይጨምር
ሴቶቻቸውን clinically sterilize ማድረግ የእስራኤል መንግስት የተለመደ ተግባር ነው።
መቼስ የሃገሬ ሰው ነጮች የፃፉት ነገር ሁሉ እንደ ሙሴ ፅላት ከሰማይ የወረደ ነው የሚመስለው።Nilo-Saharan Semitic Cushitic የሚል መደብ ያመጡት አውሮፓውያን ሊንግዊስቶች ከ ፩፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ነው። አውሮፓውያን ደግሞ ማንኛውንም ነገር ሲሰሩ ጥቅማቸውን ከእውነትም በፊት ቢሆን ያስቀድማሉ፤ አይፈረድባቸውም አንድን አህጉር ለመግዛት ታሪክን ማንሸዋረር ህዝብን ባለ በሌለ ነገር መከፋፈል ግድ ነው። ነገ ከየሃገሩ የተውጣጡ የአፍሪካ ምርጥ ምሁራንና ሊንግዊስቶች ታሪካችን፣ ቋንቋዎቻችን ላይ አዲስ ጥናት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
የአውሮፓውያን ሊንግዊስቶች ጥናት በአብዛኛው biased እና deliberately የተሳሳተ ነው። ለምሳሌ በዚህ አመዳደብ የሚያምኑ ኦሮሞዎች፣ሶማሌዎች….ቋንቋቸው
Cushitic ሰለተባለ ኩሻዊነት ለነሱና በነሱ ምድብ ላሉት ብቻ የተወሰነ ይመስላቸዋል። ነገር ግን በቅዱስ መፅሃፍ እና አያሌ ጥንታዊ መዛግብት የተጠቀሱት ኩሻውያን ነገሥታት ከ Nilo-Saharan ቋንቋ ተናጋሪዎች የሚመደቡ የዛሬዋ ሱዳን ተወላጆች ነበሩ። ሌላ ምሳሌ:- Semitic የሚባሉት የዕብራይስጥና አረብኛ ቋንቋዎች መሰረታቸው ሙሉ በሙሉ cannanite (ከነዓናዊ) ሲሆን ማንም እንደሚያውቀው ደግሞ ከነዓናውያን የካም ዘሮች ነበሩ። ዛሬ አውሮፓውያን የሚጠቀሙበት ፊደል ላቲን፤ ሮማውያን ከግሪኮች ግሪኮች ደግሞ ከከነዓናውያን የተዋሱት ካማዊ ፊደል ነው።
ኢትዮጵያን የሚያህል ትልቅ ስም ሐበሻ በሚል ተራ የውርደት ስም ሊተካ አይችልም
ሊዛባ አይችልም። ኢትዮጵያዊነት ፈጣሪ የለኮሰው የማይጠፋ እሳት ነው! ኢትዮጵያዊ በ፺፬ ሚሊዮን የሚወሰን ህዝብ አይደለም። ኢትዮጵያዊነት ኩሻዊነት ነው፤ ጥቁር ህዝብም ሁሉ የኩሽ ዘር ነው። ኢትዮጵያ የሚለው ቃል መስረቱ ግሪክ ትርጉሙም “ጥቁር ሰው” ማለት ሲሆን ግሪኮች የተለያዩ ቋንቋና ባሕል ያላቸውን ጥቁር አፍሪካውያንን በሙሉ Aethiop ብለው ሲጠሩ እነሱ የሚኖሩበትን የአፍሪካ ክፍል በሙሉ Aethiopia በማለት ይጠሩ ነበር። ሰባው ሊቃውንት በፕቶሎሚ ትዕዛዝ ብሉይ ኪዳንን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ ሲተረጉሙ ኩሻውያን የሚለውን “ኢትዮጵያውያን” የኩሽ ምድር የሚለውን “ኢትዮጵያ” ብለው ተርጉመውታል።
ድሮስ መፅሃፍ የገለጠ ሰው ይሀን ሁሉ መቼ አጣው፤ ሥልጣኔስ ከተባለ የኩሽ ልጆችን ማን ይቀድማቸዋል በ ናይል ቫሊ ብቻ ሳይሆን በኤፍራጥስ ዳር mesopotamiaን፣ ነነዌን፣ ኤላምን የገነቡት እነማን ናቸው? የዛሬ 7500 ዓመት በ ta-seti የነገሡ በሰው ልጅ ታሪክ የመጀመሪያዎቹ ነገሥታት እነማን ነበሩ? የሴም ዘሮች ከብት ሲጠብቁ የያፌት ዘሮች አውሮፓውያን የሰው ሥጋ ሲበሉ የኩሸ ዘሮች በዙፋን የተቀመጡ ህግ፣ መንግሥትና አስተዳደር የነበረን ሥልጡን ህዝቦች ነበርን። ወደፊትም ዓለምን የሚያስደንቅ ሥልጣኔ ከኛው ይወጣል ዋናው አንድነት ነው። እኔ ቤተሰቦቼ አብዛኛዎቹ አማራ(ጎንደሬ) ሲሆኑ ጉራጌ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬም አለብኝ ሐበሻነትን ግን ነፍሴ ተቀብላው
አታውቅም ለኔ ስድብ ነው ኩሻዊነት ግን ክብሬ ነው። በኦሮሞ፣ በአማራ፣ በሐበሻ ሳይሆን ኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያን እጅ ስትገባ ያኔ መልካም ቀኖችን እናያለን!
Hello Addis! You tried your best to solve one big issue and question of Most Ethiopian Ethnic groups but your analysis looks simple logic rather than base of evidence originated from facts, because you didnt used any of references which is not expected from 21 century writers!! Any way I understood your wish of united satate of Ethiopias,but the problem is you didnt considered the diversified cultural, social, economical and political background of each Ethnic groups of our country when you are trying to put them under one single umbrella by name of “habesha” for this we have no evidence to do so and one of the identity of Omotics or kushetic peoples were not shown exactly under big name “habesha” all in all culture, social, cultural and political wind of semetics were/are mobilized entirely even now a days!! As me it doesnt represent kushtics dont mix things as you wish! Accept all Ethnic groups with their own identities with great respect unless you are doing ever lasting mistakes like other some Ethiopian past foolish intellectuals did to split Ethiopians