ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2018 ፤ 250 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል ለታንዛንያ ለመሸጥ የሚያስችል ስምምነት ልትፈጽም ነው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የውጭ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ምስክር ነጋሽ ፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ሽያጩን ለማደረግ የሚረዳ ድርድር በመጪው መጋቢት ወር ይከናወናል ብለዋል።
አቶ ምስክር ፥ ለሱዳን 100 ሜጋ ዋት ሃይል ለመሸጥ የሚያስችል ስምምነት መፈረሙንም አክለዋል።
በ2017ም ፤ 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትክ ሃይል ለኬንያ ለመሸጥ የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፊያ እየተገነባ ይገኛል ነው ያሉት።
ኢትዮጵያ ለጁቡቲ በምትሸጠው 50 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል በየወሩ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር እያገኘች መሆኑንም ተናግረዋል።
*********
ምንጭ፡- ፋና – የካቲት 15 ፣ 2006፣ ‹‹በኤሌክትሪክ ሀይል ሺያጭ ኢትዮጵያና ታንዛኒያ ሊደራደሩ ነው››