ኢትዮጵያና ታንዛንያ ለኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ ድርድር ስምምነት ልትፈጽም ነው።

ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2018 ፤ 250 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል ለታንዛንያ ለመሸጥ የሚያስችል ስምምነት ልትፈጽም ነው።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የውጭ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ምስክር ነጋሽ ፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ሽያጩን ለማደረግ የሚረዳ ድርድር በመጪው መጋቢት ወር ይከናወናል ብለዋል።

አቶ ምስክር ፥ ለሱዳን 100 ሜጋ ዋት ሃይል ለመሸጥ የሚያስችል ስምምነት መፈረሙንም አክለዋል።

በ2017ም ፤ 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትክ ሃይል ለኬንያ ለመሸጥ የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፊያ እየተገነባ ይገኛል ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ ለጁቡቲ በምትሸጠው 50 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል በየወሩ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር እያገኘች መሆኑንም ተናግረዋል።

*********
ምንጭ፡- ፋና – የካቲት 15 ፣ 2006፣ ‹‹በኤሌክትሪክ ሀይል ሺያጭ ኢትዮጵያና ታንዛኒያ ሊደራደሩ ነው››

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

more recommended stories