Editor’s note: የተቃዋሚ አክቲቪስት የሆነው አበበ ገላው በግንቦት 2004 የቀድሞው ጠ/ሚኒስተር መለስ ዜናዊ የተገኙበት ስብሰባ ላይ የተቃውሞ ጩኸት ካሰማ ከወራት በኋላ፤ ከግንቦት ሰባት ድርጅት መሪ ከዶ/ር ብርሀኑ ነጋ የበለጠ ትኩረት ስቧል በሚል ከኢሳት ገለል እንዲል ተደርጎ በነበረበት ወራት በግል ያደረጋውን ንግግር የድምጽ ቅጂ፤ HornAffairs ከታማኝ ምንጮች አግኝቷል፡፡
የአበበ ገላውን ኑዛዜ የHornAffairs ብሎገር የሆነው ከበደ ካሣ እንደሚከተለው አቅርቦታል፡፡
**************
(ከበደ ካሣ)
ይህን የ11 ደቂቃ የተቀረፀ ድምፅ ጋብዣችኋለሁ፡፡ ከየት አመጣኸው እንዳትሉኝ፡፡ ዊክ ሊክስ ወይም ስኖውደን ብቻ ናቸው እንዴ አፈትልኮ የወጣ መረጃ የሚያሰረጩት? በመረጃው ትክክለኛነት ላይ ተማምናችሁ ዝም ብላችሁ ኮምኩሙት፡፡
እንደኔ እንደኔ ሙሉውን ቅጂ ብታዳምጡት መልካም ነው፡፡ በደካማ ኢንተርኔትና በጊዜ ማጣት የተነሳ ሙሉውን ማድመጥ ካልቻላችሁ ግን ሙሉ መረጃው በዚህ ፅሁፍ ቀርቦላችኋል፡፡ ልዩነቱ ይሄኛው በፅሁፍ ሲሆን ያኛው በድምፅ መቅረቡ ነው፡፡ ታዲያ ልክ እንደ አበበ ገላው እዚህም እዚያም መዝለል እንዳይሆንባችሁ ታዲያ ሙሉ ንግግሩ በሶስት አበይት ርዕሶች ተደራጅቶላችኋል፡፡ ሲያስፈልግ ደግሞ ንግግሩ እንደወረደ በጥቅስ ምልክት ውስጥ ተቀምጧል፡፡
በርግጥ ያመንከው ሰው ሲከዳህ ወይም የተማመንክበት ሰው ከንቱ መሆኑ ሲነገርህ ሁኔታውን መርምረህ እውነቱን ከመቀበል ይልቅ የወዳጅህን ጉድ ያጋለጠብህን ሰው ማጥላላት የማህበራዊ ድረ-ገፆቻችን መገለጫ ከሆነ ሰንብቷል፡፡ እና ቢሆንም እንዲህ አይነት አመል ያላችሁ ቢያንስ ለዚች ጉዳይ ብቻ አደብ ገዝታችሁ እንድታመዛዝኑ እጠይቃችኋለሁ፡፡
1. አበበ ገላውና የተቃውሞው ጎራ
በሀገር ውስጥ ባለው የተቃዋሚ ጎራ መካከል የይስሙላ ካልሆነ በቀር የአላማ አንድነት እንደሌለ በተደጋጋሚ በተፈፀሙ ድርጊቶች ተጋልጧል፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በውህደት ድርድር የሚያሳልፉትን ጊዜ ያክል በፍቺ ድርድር ላይም ያሳልፋሉ፡፡ ከመዋሃዳቸው በፊት ርስ በርስ የሚደናነቁትን ያክል ርስ በርስ ለመነቃቀፍም ፋታ አይወስድባቸውም፡፡ እድሜውን አንዱን በመቀበልና ሌላውን በመሸኘት እየገፋ ያለው ‹‹መድረክ›› (በረጅሙ – ‹‹የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ››) ለዚህ ህያው አብነት ነው፡፡ ተጨማሪ ዐብነት ካስፈለገ የ1997ቱን ቅንጅትን መመረቅ ይቻላል፡፡ በዚህ በኩል የማይታማው ሰማያዊ ፓርቲ ብቻ ነው፡፡ እድሜው አጭር ቢሆንም ራሱን ተራራ አሳክሎ ሌሎቹን በንቀት ቁልቁል ስለሚያያቸው በቀላሉ የሚዋሃዱት አይሆንም፡፡ እንትፍ ትፍ፤ ከአይን ያውጣህ ብያለሁ፡፡
በውጭ ያለው የተቃውሞ ሃይልም አንድ የሚያደርገው ፅንፈኛነቱና ጭፍን ጥላቻው ብቻ እንጅ የአላማ አንድነትም ሆነ እርስ በርስ የመተማመን ባህል እንዳልፈጠረበት ፊት አውራሪው አበበ ገላው በራሱ ቃል እንዲህ ሲል አጋልጧል፡፡
“ወደፊትም ትግሌን እቀጥላለሁ በተዘዋዋሪ መንገድ፡፡ ይሄ ግን ከተቃዋሚ ጋር ሆኖ መስራት አያዋጣኝም፡፡ ቤትሬይ {betray} ነው የሚያረግህ፡፡ አንደኛ ተቃዋሚዎቹ ራሳቸው ቅንነት የጎደላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ስም በማጥፋት ምናምን ቶሎ ይሰማራሉ፡፡ አንድ ኢሹን {issue} አድሬስ {address} ከማድረግ ይልቅ፡፡ እኔ አሁን ኮንሰርኔን {concern} እንደ ጓደኛ አድርጌ ሬይዝ {raise} ያደረግሁላቸው ሰዎች በጣም ነው የታዘብኳቸው፡፡ ያንን ነገር በቁም ነገር ከመውሰድ ይልቅ እኔ ራሴን ታላቅ አድርጌ እንደገመትኩ አርገው ያልሆነ አይነት ተራ ወሬ ጀመሩ፡፡”
ለዚህ ሁሉ ምክንያቱ ደግሞ ሁሉም ራሳቸውን ትልቅ አድርገው የማየት ችግር ስላለባቸው መሆኑን አበበ ይጠቅሳል፡፡
“አንድ ነገር ስታነሳበት ዲስቶርት {distort} አድርጎ ያስበዋል፡፡ አንዳንዱ ደግሞ የራሱ የሆነ ችግር ስላለበት የከለልከው የሚመስለውም አለ፡፡ ሳትከልለው፡፡ ለምን? ራሱ በቃ፤ ራሳቸውን ከፍ አድርገው ስለሚያዩ በዚህ ሌቭል /level/ አንዳንድ ኢሹዎች ስታነሳ በቃ ያንን የተጋፋህ የሚመስላቸው አሉ፡፡”
እንደ አበበ ገለፃ ይህ ችግር የአባሎቹ ብቻ ሳይሆን የአመራሮቹም ነው፡፡ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋን ጎሸም ባደረገበት ንግግር መሪዎቹ እየተቃወሙ ሳይሆኑ የራሳቸውን ኑሮ እያመቻቹ ነው ብሏል፡፡
“ደሞ አንዳንዶቹ ኤግዛጅሬትድ ፊሊንግ {exaggerated feeling} ነው እንጅ ያላቸው እየታገሉ አይደለም፡፡ ኦነስትሊ ስፒኪንግ {honestly speaking}፡፡ አንዳንዶቹ የድርጅት መሪ ስለሆኑ ራሳቸውን እንደ ታላቅ፡፡ ኢጎ {ego} ማለት ያ ነው እንደውም፡፡ ትንሽ ሰርተህ ራስህን እንደ ታላቅ ስትገምት ነው ኢጎ ችግር የሚፈጥርብህ፡፡ አንዳንዶቹ ኢጓቸው የጋረዳቸው ሰዎች እየታገሉ አይደሉም፡፡ የራሳቸውን ላይፍ {life} ነው እየኖሩ ያሉት፡፡”
2. አበበ ገላውና ኢሳት ቴሌቪዥን
በጥቅል ፅንፈኛ የተቃውሞ ሃይሉና ኢሳት ቴሌቪዥን በተለይ ደግሞ አበበ ገላውና ኢሳት ቴሌቪዥን ምንና ምን እንደሆኑ ለናንተ መንገር ለቀባሪ እንደማርዳት ነው የሚሆንብኝ፡፡ በአጭሩ እጅና ጓንት ናቸው ብሎ መግለፅ ይቀላል፡፡ እርስ በርስ ሲወዳደሱ ለሰማቸው የጫጉላ ሽርሽር /honeymoon/ ላይ ያሉ ሙሽሮች ነው የሚመስሉት፡፡ አበበ ለኢሳት ጀግናው ነው፤ ኢሳትም ለአበበ ድምፁ ነው፡፡ ኢሳት አበበ ገላውን <የአመቱ /2012/ ምርጥ ሰው> ሲል ሰይሞታል:: አበበም ኢሳትን የህዝብ ድምፅ ብሎታል፡፡
ለነገሩ ኢሳትን ነፃና ገለልተኛ የህዝብ ድምፅ ነው ብለው የሚያስቡ፤ ባያምኑትም የሚሰብኩለት ሌሎችም ሞልተዋል፡፡ እውን ግን ኢሳት ደጋፊዎቹ እንደሚያወሩለት ነው? እነኚህ ደጋፊዎች አበበ ገላው <<እኛ ነፃ ጋዜጠኞች ነን፤ ኢሳትም ገለልተኛ ሚዲያ ነው>> ሲላቸው ያመኑትን ያክል አሁን ጥያቄው <<አይ እኔ ብቻ ነኝ እንጅ ሌሎቹ ጋዜጠኞች ለጥቅማቸው ያደሩ ናቸው፤ ኢሳትም የግንቦት 7 ሎሌ ነው>> ቢላቸው ያምኑት ይሆንን? የሚለው ነው፡፡ አበበ ኢሳትን በተመለከተ እንዲህ ይላል፡፡
“በኢሳት ላይ ያለኝ አንዱ ትልቅ፤ እኔ ብዙ ቅሬታ የለኝም ግን የድርጅት ልሳን ሆኖ ለድርጅት ሎሌ መሆን ደግሞ አልፈልግም፡፡ እኔ በበኩሌ፡፡ ይሄ ሲሪየስ {serious} የሆነ ኢሹ ነው፡፡ እኔ ይሄ ሚዲያ ኢንዲፐንደንት ራን {independently run} መሆን አለበት፡፡ ይደብርሀል – ራሱ መስራቱም ማገልገሉም፡፡ እኔ ማገልገል የምፈልግው ማንን ነው? ግንቦት ሰባትን አይደለም ማገልግል የምፈልገው፡፡ ወይም ግንቦት ዘጠኝን አይደለም ወይም ግንቦት 20ን አይደለም፡፡ እኔ ሰርቭ {serve} ማድረግ የምፈልገው የኢትዮጵያን ህዝብ ነው፡፡”
አበበ ምን ያህል የህዝብ አገልጋይ ነው የሚለው ሌላ ጥያቄ ሆኖ፤ የግንቦት 7 ሎሌ ሆኖ ማገልገል እንዳስመረረው ግን ተናግሯል፡፡ ኢሳት የግንቦት 7 አፈ ቀላጤ ለመሆኑ በአብነት ያነሳው ደግሞ የሚዲያውን የአመስተርዳም ስቱዲዮ ዘገባዎች ነው፡፡
“አሁን ከዜና አቀራረብ ጀምሮ አመስተርዳም የሚሰሩ ዜናዎች መዓት ችግር ነው ያለባቸው፡፡ እነ መሳይ [ከበደ] ዝም ብሎ ኳሊቲ {quality} የሌለው ነገር ነው ፕሮዲውስ {produce} የሚያደርጉት፡፡ በነሱ በኩል ደግሞ የሚመጡ፣ ድርጅት ኢንቮልቭ {involve} የሚያደርግባቸው ነገሮች ደግሞ ብዙ ደካማ የሆኑ ነገሮች ነው ያሉት፡፡”
አበበ ግን ለምን እንዲህ መረረው ከተባለ መልሱ የጥቅም ግጭት /conflict of interest/ ነው ፡፡ እሱ ከጥቅም አንፃር ሁለት ጉዳዮችን ነው የሚያነሳው፡፡
“አንደኛ ገባህ ቤተሰብ አስተዳድራለሁ፡፡ አንድ አመት ሳክሪፋይስ {sacrifice} ልትከፍል ትችላለህ፡፡ በማይረባ ሲቾሺን {situation} ውስጥ እየሰራህ ማለት ነው፡፡ ከዛ በላይ ግን ልትሄድ አትችልም፡፡ ሁለተኛ ደግሞ ማነው ሴኩሪቲህንና ሴፍቲህን {security and safety} ጋራንቲ {guarantee} የሚያደርግልህ? ዱ ዘይ ሪሊ ኬር {do they really care?} አንተ ነገ ብትሞት ኬር የሚያደርግ ሰው አለ?”
አበበ እዚህ ላይ እውነት ተናግሯል፡፡ ይሄ ራስን የመጥቀም እንጅ ድሆችን የማበልፀግ ትግል አይደለም፡፡ ይሄ የራስን ደህንነት አስተማማኝ የማድረግ እንጅ የዜጎችን ሰላም የማስጠበቅ ትግል አይደለም፡፡ ይሄ በምቹ ሀገር እየኖሩ በህዝብ የመነገድ እንጅ ባልተመቸ ቦታ ሆኖ ራስን ለለውጥ መስዋዕት የማድረግ ትግል አይደለም፡፡ ታዲያ ለምንና ለማን ብሎ ራሱን መስዋዕት ያደርጋል? ለምንስ ብሎ በአነስተኛ ክፍያ ይሰራል?
“እኔ በኮዙ {cause} ስለማምንበት ነው እንጅ የራሴን ገንዘብ ሰብሲዳይዝ {subsidize} እያደረግሁ ነው የኖርኩት፡፡ በፋሚሊ ሴቪንግ {family saving} ነው እኛ የኖርነው፡፡ እነሱ በሚከፍሉኝ አይደለም የኖርኩት፡፡ እነሱ የሚከፍሉኝ የቤት ኪራይ ሊከፍልልህ ይችላል፡፡ እንደው የተወሰነ ወጭ ሊሸፍን ይችላል፡፡ ሁለት ልጅ ሲኖርህ ፤ ቤተሰብ ሲሮርህ ግን ወጪህ ከዛ በላይ ነው፡፡ ኤክስፔንሲቭ {expensive} ነው ዲሲና አካባቢው መኖር፡፡”
“በሙሉ ፍላጎትና በቅን ስሜት ልሰራ የምችለው ያ ነገር ኢንሹርድ {insured} መሆኑን ሳይ ነው፡፡ እነሱ የራሳቸው የሆነ ኮምፕሌክስ ስትራክቸር {complex structure} አዋቅረው ለዛውም ደግሞ ቴክ ኬር {take care} አያደርጉም፡፡ ዱ ዘይ ቴክ ኬር አባውት ሚ፤ አባውት ዘሪስክ ዛት ዩ አር ፌሲንግ? ዘይ ዶንት {do they take care about me, about the risk you are facing? They do not.} ብዙ ሪስክ አለው፡፡”
3. አበበ ገላውና የደህንነት ሰጋቱ
አበበ ገላው ዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደው የቡድን 8 ስብሰባ ላይ <<መለስ ዲክታተር>> ብሎ ከጮኸ በኋላ ራሱን የነፃነት አርበኛ አድርጎ ይቆጥራል፡፡ መለስ ዜናዊን እኔ ነኝ የገደልኩት ብሎ ስለሚያምንም ቅጠል በተንኮሻኮሸ ቁጥር እንደደነገጠ ነው፡፡ አይዞህ በአንተ ቂም ይዞ የሚበቀልህ የለም የሚሉትንም አይሰማም፡፡ ስለሆነም አሁን የሱ ዋና ስጋት በሰላም ወጥቶ በሰላም የመግባት ጉዳይ ነው፡፡ እንደውም ከንግግሩ መረዳት የሚቻለው ከፅንፈኛው ሃይል ጋር አጣብቆ ያቆየው ይሄው ስጋቱ ብቻ ነው፡፡
“የኔ ኮንሰርን የሴኩሪቲ ኮንሰርን {security concern} ነው፡፡ ሌላ ነገር አይደለም፡፡ ያ የሴኩሪቲ ኮንሰርኔ ደግሞ ሪል {real} ነው፡፡ ሪል ነው፡፡ በጣም በጣም ሪል ነው፡፡ ለነሱ ላይታያቸው ይችላል፡፡ እኔ ግን የጉዳዩ ባለቤት ስለሆንኩ አውቀዋለሁ፡፡ ኤቭሪዴይ ፔይናንስ {everyday penance} አደርገዋለሁ፡፡ ከአንድ ቦታ ተነስቼ አንድ ቦታ እስከምሄድ ድረስ የሚያጋጥመኝ ሰው ግማሹ በመልካም አይን ነው የሚያየኝ ግማሹ ደግሞ ቢገለኝ ደስ ይለዋል፡፡ እኔ ብቻዬን ነኝ፡፡ አንድ ሰው፡፡ በዛ ሌቭል {level} በርካታ ጠላቶች ካሉህ እንዴት ብለህ ኮንፍሮንት {confront} ታደርጋለህ? ያንን በርካታ ጠላትህን፡፡”
እሱ እንደሚለው በዚህ የተነሳ ያጋጠመው ጉዳት ከመኖሪያ መንደሩ እስከ መራቅ ይደርሳል፡፡ ችግሩን ይባስ ያከፈው ደግሞ መፍትሄውን ያለማወቁና አማራጮቹም ውስን መሆናቸው ነው፡፡ ቃል በቃል እንደሚናገረው አሁን የሚያስጨንቀው የኢሳት ፖለቲካ ሳይሆን የራሱ ህይወት ነው፡፡
“እኔ ከዚያ ግዜ ጀምሮ ላይፌ ዲፈረንት {different} ነው፡፡ አሁን ለምንድን ነው ርቄ የምኖረው ከ[ዋሽንግተን] ዲሲ? ከኮሚኒቲዬ? ለእኔ እኮ ሎስ {loss} ነው፡፡ የራሱ የሆነ መጥፎ ኢምፕሊኬሽን {implication} ያለው ነው፡፡ ከኮሚኒቲህ ርቀህ ምናምን እስከመወሰን ካደረሰህ ሲሪየስ የሆነ ነገር አለብህ ማለት ነው፡፡ አሁን ትልቁ ኢሹዩ ኦነስትሊ ትልቁ ኢሹዬ ኢሳት ሳይሆን በአጠቃላይ በዛ አካባቢ መኖር የሴኩሪቲ ኢሹ ነው፡፡ እኔን መግደል የሚፈልግ መዓት ሰው አለ፡፡ ይህንን ማንም ሊነግረኝ አያስፈልግም፡፡ እኔ ራሴ አውቀዋለሁ፡፡ ይህንን ካወቅሁት ይሄንን በምን አይነት ሁኔታ ነው የምትቋቋመው? በመጋፈጥ ነው? ወይስ ሄጄ ሽጉጥ በመግዛት? ነው ወይስ ጫካ በመግባት ነው? ምርጫህ ሊሚትድ ነው፡፡”
<<አስተሳሰባቸው ጠባብ ነው፤ ስትራቴጂካሊ አያስቡም>> የሚላቸው ፅንፈኛ ፖለቲከኞ ተደላድለው ስለሚኖሩ የሱን ችግር እንዳልተረዱለትም ነው የሚገልፀው፡፡ በቡድን 8 ስብሰባ ላይ የነበረውን ምስል በኤዲቲንግ በማቀነባበር አበበ ገላው ሲያንባርቅ መለስ ዜናዊ እንደደነገጠለት ለማስመሰል ብዙ ተደክሟል፡፡ ይህ የአበበ ንግግር ግን የደነገጠው ራሱ አበበ ገላው መሆኑን፤ ከዛን እለት ጀምሮ ሁልግዜ በጭንቅ ውስጥ እንደሚኖር ነው የሚያሳየው፡፡
“አሁን እኮ እኔ የምልህ ወደድኩም ጠላሁም ፐብሊክ አይ {public eye} ውስጥ ገብቻለሁ፡፡ የዱሮው አበበ አይደለሁም፡፡ ፐብሊክ አይ ማለት ግማሹ አድማየር {admire} ያደርግሃል፤ ግማሹ ደግሞ ደምህን መጠጣት የሚፈልግ አለ፡፡ የከረረ ፖለቲካ ያለበት ሃገር ነው ወደድንም ጠላንም፡፡ እኔ ደግሞ፤ የነካሁት ሰው ደግሞ መለስ ዜናዊ ነው፡፡”
የተቀረፀው ድምፅ በዚሁ አብቅቷል፡፡ እኔም ፅሁፌን በዚሁ አበቃሁ፡፡
***********
[Editor’s note: የአበበ ገላውን ድምጽ የያዘውን ቴፕ ከታች ያሉትን አማራጮች በመጠቀም፡- እዚሁ ያዳምጡ ወይም ዳውንሎድ ያድርጉ]
Download: Leaked tape – Abebe Gelaw on Ginbot7, ESAT, diaspora opposition
Listen:
Dawit
in life there are ups and downs,Abebe is human,we all gossip in private,it is not unusual,do not try to make a big deal out of it.he gossip ESAT and Dictator Dr Berhanu,so what,you can not get your rotten evil leader Meles zenawi,he is burning in hell.
poor Abe, your own empty patriotic barking which was aimed to gain you admiration and a hero’s reception (I bet you don’t even know a real hero is like) is driving you crazier and crazier to confusion and death … You have already started paying for it… hey… sorry for ur children … sacrifice in vain ,,,
Ha ha ha…then poor Abe is already in the state of daylight fear and all night long insomnia. Who the hake will waste time and resource to get him away when the fear and guilt in him will do all the job by itself, slowly and painfully. Didn’t he say he received the “power” and “guidance” from St. Gabriel :) So why fear the “Walmart level pistol” when the big Angel can even deflect a missile….so funny!
Obviously, he seems to share the version of “fear of death” with his God Father, Mengistu H/Mariam. I wonder what he thinks about fathers and mothers who perished all along the way to bring the current Ethiopia into realization – I bet he knows that they too have kids, but they were real politicians – not a “Starbucks” one. What a crap and fearful boy we have around! Go hell!
Abebe spoke what he thought an injustice. The weird thing is how embarrased and humliated it had been that Meles got sick immediately and died. What Abebe described is the sentiment I share too. I don’t want to belong to any political groups (especially the existing ones). But also I don’t like EPRDF. They are playing for the wrong team. For sure, they are not for the people.
If EPRDF had ears, it had lots of chances to listen and yet is not willing to listen. I wanna be a voice like Abebe Gellaw. He just told it like it is. It doesn’t matter whether he talked to Dr. Berhanu Nega or Ato Sibhat Nega. But he told the truth. In a free and impartial audience, the truth is unbearable for Meles even, since he knows his deeds.
But for the others, learn from his mistake. Meles missed lots of good opportunities to be on the good side: like Mandela, and Menelik. If it was Menelik that lived in this age, he would have gotten Mandela’s type funeral (studded with world leaders). Meles didn’t. Because they have weighed him like feather.
Interesting audio leak.
This audio shows that Abebe is terrified and lives a very nightmarish life. He is looking behind his shoulder everywhere he goes. The so called opposition has betrayed him. He is desperate. It sounds that America is not a safe place for him. This teaches us a huge lesson. If you attack and insult a public figure, you will have lots of enemies, and also your so called opposition members can not protect you — you will be on your own!
Abebe: Please ask for forgiveness and return to Ethiopia. If you sincerely repent, I am sure Ethiopians will forgive you. Based on your description of your life, you are not fond of the Diaspora opposition groups, and you are afraid for your life, and the future of your family is at risk. Therefore, Ethiopia will be the only safe place for you.
I heard that Tamagne Beyene has been on ESAT payroll for a while and that he is paid a monthly salary. This has not been disclosed to the public, they are paying Tamagne under the table. When this is finally disclosed by a whistleblower, then ESAT will be gone.
Perhaps, is this payment issue the source of the fight among the opposition? Time will tell.
God please have mercy for this lost soul. God bless Ethiopia!
@blen,
Click on the Youtube video found at the right column
So where is the Audio
yetale? fetrachu mewashet jemerachu enantem???
እንደሚመስለኝ ይሄንን ያተማችሁት ሆን ብላችሁ ይሄንን አገር የከዳ መሪያችንን ያወረደ ወራዳ አሸባሪ ገለልተኛ ለማስመሰውል ነው። ግለሰቡ የኢትዮጵያ መንግስት የግንቦት ሰባት አመራር በመሆን ለሽብር ሲንቀስቀስ ተደርሶበት ፩፭ አመት ተፈርዶበታል። አሁንን እዚህ ያወጣች ሁት ግን ፍርድ ቤት በይፋ ያወጀውን የሚጻረር ነው። ይሄ ሆን ተብሎ መንግስት በፈጠራ ይከሰል የሚለውን የተቃዋሚ ዲስኩር የሚደግፍ ነው። ነቅተናል የወስጥ አርበኞች።
He is simply an individual of course he may have something but we don’t care about him.
ይህ የጠላት መወሻከት ነው። ግንቦት ሰባትም ሆነ ኢሳት የመልአክ ማሕበር አይደሉምና ስህተት ሊገኝባቸው ይችላል፣ ትችት ሊያስፈልጋቸው ይችላል፣ ቅሬታ ሊቀርብባቸው ይችላል፣ ተቃውሞም ሊገጥማቸው ይችላል። ደግሞም ይገባል። ግንቦት ሰባትንም ሆነ ኢሳትን ለማሳደግ የሚፈልጉ ሁሉ ከገንዘብና ከሌላው መዋጮ ጎን ለጎን ገንቢ ሃሳብና ማስተካካያ ያለ ምንም ማመንታት ለሲጡ ይገባል። ይህ የሚሆነው እንደ አቶ መለስ በስህተትና በአምባገነንትን በክተህ ወደ መቃብር ላለመውረድ ነው። አቶ ከበደ ካሣ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር አንተ ለዝባዝንኬ ፍርፋሪ ፍለጋ ብለህ የእብደት ስራ በመስራትህ ቀጥል። አንድ ቀን ግን ይነጋብሃል። ያኔ አንተን አያድርገኝ። ውሻም ሆነ አሳማ ለመሆን የቀዶ ጥገና ለውጥ ብታደርግ አታመለጥም በኩስህ መርምረን እንደርስብሃለንና!!!
kkkk antew rasih tsinfegna temeliseh tsinfegnochn tsinfegna tilaleh .hulachihum matrebu kento lehodachu mitnoru kahadiwoch nachu.
coming soon
So what is the big deal? Aye Weyane, the issue is that you are spying on key people in the opposition. Leboch
yhe sew abebe gellawe bzehe bltba tehufe ymghemte sew aydelme abebe ymnbten sertul wetatma new yhe astesasteb bzu godlo ngerche alte abebe rasun ymwke sew new btesbun bskedmem bserwe talke sera bhger bte btame ketga tesmnte alwe lelwe kerto melun face book profil adergen demsun yslke metery yaderge sew sefer kuter ylwme keberna mogse lesat en labebe gellaw
ay abebe gelebaw, no one thinks you killed meles… just relax, take a deep breath and raise your children, you’re too irrelevant to be followed around.
Where is the link to the voice recorded? Thanks