የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ም/ፕሬዝዳንትና ዋና ፀሐፊ ተነሱ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዛሬ በጠራው አስቸኳይ ስብሰባ የፌዴሬሽኑን ዋና ጸሀፊ አቶ አሸናፊ እጅጉ ከስልጣናቸው እንዲነሱ ወስኗል፡፡Ethiopia Football Federation logo

የኢትዮጵያ ብሄራዊ እግር ኳስ ቡድን በብራዚሉ የ2014ቱ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ላይ ከቦትስዋና ባደረገው ጨዋታ ላይ ሁለት ቢጫ እያለው በስህተት የተሰለፈውን ተጫዋች ምክንያት በማድረግ ሶስት ነጥብና ሶስት ጎል ተቀንሶበታል፡፡

ይህንንም ምክንያት በማድርግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በቅርቡ በሰጠው መግለጫ ችግሩን ለማጣራት እንደሚሰራ መግለጹን ተከትሎ በጠራው አስቸኳይ ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ጸሀፊ አቶ አሸናፊ እጅጉን ከስልጣናቸው አንስቷል፡፡

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ብርሃኑ ከበደ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ያቀረቡት ጥያቄ ስራ አስፈጻሚው አጽድቆታል፡፡

ጠቅላላ ጉባዔው እንደቀጠለ ነው፡፡

***********

Source: ERTA – June 24, 2013, titled “የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ጸሀፊ ከስልጣናቸው ተነሱ”.

Recommended: የፌዴሬሽኑ ቅሌት

Daniel Berhane