(ሰይፉ አለምሰገድ)
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምንያህል ተሾመ ሁለት ቢጫ ካርድ አይቶ ሳለ ሰኔ 1/2005 ከቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ጋር በተደረገው ጨዋታ መሰለፉ ስህተት እንደሆነ አመነ፡፡
ፌዴሬሽኑ ብሄራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ አቻው ጋር ከመጫወቱ በፊት ችግር ስለመፈጠሩ ፊፋ አሳውቆት እንደነበር ገልጿል፡፡
ሆኖም ይህ ችግር በቡድኑ ተጫዋቾችና በደጋፊዎች ላይ ያልተፈለገ የመንፈስ ጫና እንዳይፈጥር በመስጋት መረጃውን ይፋ ሳያደርግ ቆይቷል፡፡
ፌዴሬሽኑ በፈጠረው ችግር ዙሪያ ዛሬ ሰኔ 11/2005 ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ መሰረት ፊፋ ተጫዋቹ ሁለት ቢጫ ካርድ በማየቱ የተነሳ ከቦትስዋና ጋር በተካሄደው ጨዋታ እንዳይሰለፍ የሚገልፅ ደብዳቤ ለፌዴሬሽኑ ልኳል፡፡ ይሁንና የፌዴሬሽኑ አመራሮችና አሰልጣኝ ይህን የፊፋ ውሳኔ በመዘንጋታቸው ተጨዋቹን አሰልፈውታል፡፡
የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለችግሩ ተጠያቂ ያላቸውን ግለሰቦች ዝርዝርም ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ መሰረት የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንትና የብሄራዊ ቡድኑ ቡድን መሪ አቶ ብርሀኑ ከበደ፣ ዋና አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው፣ አሰልጣኝ ስዩም ከበደ፣ የቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ፣ የስራ አስፈፃሚ አባልናየቡድን መሪ የነበሩ አቶ አፈወርቅ አየለ እና የፌደሬሽን ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አሸናፊ እጅጉ በጥፋተኝነት ተፈርጀዋል፡፡
በፊፋ ህግ መሰረት ተገቢ ያልሆነ ተጨዋችን ማሰለፍ በጨዋታው የተገኘውን ነጥብ የሚያሳጣና ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣትም የሚያስጥል ነው፡፡
በዚህ መሰረትም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን 3 ነጥብና 6 ሺህ ስዊስ ፍራንክ እንደሚቀጣ ፊፋ ያስታወቀ ሲሆን በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን እስከ ሰኔ 14/2005 ዓ/ም ምላሽ እንዲሰጥም በፃፈው ደብዳቤ አስታቋል፡፡
አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በተፈጠረው ስህተት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው ጳጉሜ 2/2005 ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ለሚካሄደው ጨዋታ ከወዲሁ መዘጋጀት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በዚህ ጨዋታ አሸንፈን ወደ መጨረሻው የአለም ዋንጫ ማጣሪያ እንደምናልፍ እርግጠኛ ነኝ ብለዋል አሰልጣኙ፡፡ለዚህም የቡድኑ አባላት ዝግጁ መሆናቸውን አሰልጣኙ አረጋግጠዋል፡፡
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝደንት አቶ ሳህሉ ገብረወልድ በበክላቸው በአሰራር ክፍተት የተፈጠረው ችግር አሳዛኝና ሊከሰት የማይገባው ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የፌደረሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጥፋተኞቹ ተገቢውን ቅጣት ማግኘት እንደሚገባቸው የተስማማ መሆኑን በመግለፅ በአጭር ጊዜ ውስጥ የቅጣት ውሳኔውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል፡፡
ፌዴሬሽኑ በተፈጠረው ችግር ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ገልፆ ለኢትዮጵያ ህዝቦችም ይቅርታ ጠይቋል፡፡
*************
Source: ERTA – June 18, 2013, titled “ፌዴሬሽኑ የፊፋን ክስ አመነ”.
Poor conspiracy. You must be one of the clown who always try to associate something with Ethnic politics. What is wrong if someone in Dedebit has been given to represent his country? Those players who made us to celebrate are from this club and insulting the club is nonsense. We need few more strong clubs like Dedebit.
እንዲህ የመሰለ ስሕተት እንዴት ሊፈጸም እንደ ቻለ መገመት ቀላል ነው። ኮ/ል አወል አብዱራሂም የደደቢት ክለብ መሥራችና ባለቤት ናቸው። ምን ያህል ተሾመ በየነ የደደቢት ቡድን ተጫዋች ነው። ለብሔራዊ ቡድን ከሚሰለፉት አብዛኛዎቹ ከደደቢት ነው። ኮ/ል የህወሓት አባልና ታጋይ ናቸው። ደደቢት ክለብ ማለት ገንዘብ ማለት ነው። ፌዴሬሽኑና የመንግሥት አካላት በሙስና ለመዘፈቃቸው ምንም ማስረጃ ማቅረብ አያሻኝም። ሯጮቻችን ለአገራቸው እንደ መሮጥ ለአረብ አገሮች የሚሮጡት ፍትሓዊ አመራረጥና ድልደላ ስለሌለ ነው። አመራሩ ላይ የተሰየሙትን ባለሥልጣኖች ስም ይመልከቱ። ቁልፍ ቦታ ላይ የተሰየሙት በብቃት ሳይሆን ከትግራይ ስለሆኑ ነው። በፌዴሬሽኑ ሆነ በመንግሥት ዘንድ የኮ/ል ተሰሚነት እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነው የሚሉ ቢኖሩ ወይ አታላዮች ናቸው ወይም ጅሎች ናቸው። አሁን የሚደረገው ሙከራ የምንያህል ስም ስለ ተቀያየረ አሳስቶ ነው ለማሰኘት ሙከራ እየተደረገ ነው። የአገርን ያህል ክብርና የሕዝብን ሞራል ሥራቸውን በግል ጥቅም በለወጡ ሰዎች ማበላሸት ማለት ይኸው ነው። ገና ምኑ ታይቶ? እስካሁን ያልተከሰቱ ስንት አሉ? ሕዝብ ዝም ብሎ ማለፍ የለበትም። ጥያቄው እስኪመለስ በዚህ ጉዳይ በንዝህላልነት ይሁን አውቀው በደል የፈጸሙ በሕግ መቀጣት ይኖርባቸዋል። ሕዝቡ በሹማምቱ መውረድ ብቻ መወሰን የለበትም። የተመዘበረ ገንዘብ ይፋ መሆን ይኖርበታል። ገንዘቡ እኮ የሕዝብ ነው። አሠልጣኝ ሰውነት ጫና ተደርጎባቸው ነው እላለሁ። ጥሩ ውጤት ማስመዝገባቸውን ያልወደዱ ወዲያኛው ሳምንት ይልቀቁ ሲሉ ነበር። የራሳቸውን ሰው ሊተኩ ማለት ነው። ለዚህም ነው እንደ ሚሚ ዓይነቶቹ ማንም ይሳሳታል። ይልቅ ከዚህ ስሕተት ተምረን ወደሚቀጥለው እንለፍ እያሉ ያሰለቹናል። ጥቅማቸው ሊቀር ነዋ! ሌቦች ሊጋለጡ ነዋ! የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ ነቃባቸው ረስተዋል። ሲያወናብዱን የኖሩት ጠ/ሚ መለስ መሞታቸው ተሸፋፍኖ የቆየውን ገለጠው እኮ! እርሳቸው በሕይወት ሳሉ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድናችን ከመንደር ሊወጣ አልቻለም። አሁን ዓለም አቀፍ ደረጃ እየያዘ ነው። እግዚአብሔር እንዴት ባያድላቸው ነው ይህን ድል ሳያዩ የሞቱት? ከንግዲህ ወደ ኋላ ሊመልሱን ውስጥ ውስጡን የሚሠሩትን ማባረር ያሻል።
This is a sad situation. But mistakes give us the opportunity to learn and be cautious for the future. The lesson is: if we are planning to go international we need to have systems and procedures in place that meet our target. In fact it is good we identified our gap at the beginning of our journey. Thumbs up for the football federation ,the players and all responsible for being open and accountable . We are happy and proud of your efforts. Continue to make us proud , not only by winning games , but by working hard to put international standard procedures and systems.
all those who are working around football ie. 1.the football federation and members,managers coaching stuff players are the most behind this mistake ,if it is surely a mistake
2nd those sport jornalists on fm radios should be responsible because even if it is good to know the life style length and history of players of england spain… players and managers it was also their good duty to look at the website information and to help the ethiopian team as it is very clearly putted on each match report.
finally i would imagine there is or was some one in the federation who is hiding this paper from fifa but it is un acceptable if mr sewenet say the only source of his information is that paper rather he should search from the websites that is his most clear mistake.
my final recomeendation abouth the punishiment is because it is the case which affects players moral and other stuffs moral we have to first pray foor them to do their best for the next match and will see the punishement then.
ይቅርታ ጥሩ ነው ይቅር ብለናችኋል፡፡ ይህን መሰል አሳዛኝና ቅስም የሚሰብር፣ ተስፋ የሚያስቆርጥና የብዙዎችን ድካም ፍሬ የሚያሳጣ ስህተት ላለመፈጸም ጥንቃቄ ይደረግ፡፡
በሚቀጥሉት ጨዋቃዎች ፌደሬሽኑ፣ አሰልጣኙና ተጫዋቾች ሕዝቡን ለመካስ የበለጠ ጥረትና ዝግጅት ያድርጉ፡፡ ስህተቱ የአንድ፣ የሁለት ወይንም የአምስት ሰው አይደለም፡፡ ከፌደሬሽኑ ጀምሮ እስከ እያንዳንዱ ተጫዋች ድረስ ሁሉም ስህተት ሰርተዋል የሚል ግምት ነው ያለኝ፡፡ ምክንያቱም ሁሉም በዚህ ሰርክል ውስጥ ያሉ ሁሉ ምንያህል ሁለት ጊዜ ቢጫ ካርድ ማየቱን ዘንግተዋል ብሎ ለመቀበል ይቸግራል፡፡ ሆኖም ለካሳ ተዘጋጁ፣ የተደከመበትም ሥራ ያለ ውጤት እንዳይቀር ተገቢው ሁሉ ይደረግ፡፡