ዶ/ር አብይ አህመድ የኦህዴድ ሊቀመንበር ሆኑ

(OBN)

የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ዛሬ ባካሄደው ስብሰባው የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት፣ ተሳትፎ ለማጠናከር እና በክልል እና ሀገር ደረጃ የተጀመሩ ማሻሻያዎችን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ እንዲሁም ኦህዴድ እና የክልሉ ህዝብ የጀመረው ትግል አሁን ከደረሰበት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ሲባል የአመራር ምደባ ማስተካከያ ማድረጉን አስታውቋል።

በዚህም መሰረት ዶክተር አብይ አህመድን የድርጅቱ ሊቀመንበር እና አቶ ለማ መገርሳን ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡን ከኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።

Photo - OPDO chair and deputy, Abiy Ahmed and Lemma Megersa
Photo – OPDO chair and deputy, Abiy Ahmed and Lemma Megersa

የአመራር ምደባ ማስተካከያውም በኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ መፅደቁን ድርጅቱ አስታውቋል።

በዛሬው እለት (የካቲት 15/2010) የተመረጡት አመራሮችም የክልሉን እና የሀገሪቱን ህዝቦች ጥቅም የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ታምኖባቸዋል ብሏል ድርጅቱ።

በመሆኑም የኦህዴድ አባላት፣ ደጋፊዎች፣ የክልሉ እና መላው የሀገሪቱ ህዝብ ከኦህዴድ ውሳኔ ጎን በመሰለፍ በሀገር ደረጃ ሁለንተናዊ ለውጥ እንዲመዘገብ እንደ ከዚህ ቀደሙ ከድርጅቱ ጎን እንዲቆሙ ጥሪውን አቅርቧል።

*******

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

more recommended stories