(ይታገሱ ዘዉዱ)
ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ጄኔራል ሆነው በመመረጣቸው ደስ በሎኛል፡፡ ለምን ቢባል የአገሬ ሰዉ ናቸዉ…………. ኢትዮጲያዊ …… ወዲህም ጥቁር አፍሪካዊ! የደስታየም ምክንያት ጥቁር አፈር ያበቀላቸዉ የጥቁር ህዝብ ልጅ በመሆናቸዉ ብቻ ነዉ ፡፡ ጥቁር በአለም መድረክ ላይ ከፍ ከፍ ሲል ደስ ይለኛል፡፡
ነጮቹ እንደሚሉት የጥቁር ዘረኛ (Black-ish ) የመሆን ጉዳይ አይደለም ፡፡ ጥቁር ህዝቦች ለበርካታ ዘመናት ግፍ ተፈጽሞባቸዋል …….በባርነት ተግዘዉ በደምና በላባቸዉ ባቆሙት አገር ላይ ዛሬም ድረስ ከዉሻ አንሰዉ በየአደባባዩ በዘረኛ ነጮች ደማቸዉ ይፈሳል፡፡ ጥቁር አፍሪካዉያን በቅኝ ተገዝተው በገዛ መሬትና ሃብታቸዉ ላይ ነጭ እንዳሻዉ ሲጭን ሲጋልብቸው ኖሯል፡፡
ዛሬ በመላዉ አፍሪካ ላለዉ አስከፊ ድህነት፣ ማህበራዊ ቀዉስ፣ ዘረኝነት፣ የስነ-ልቦና መዳሸቅ፣ የስነም-ግባር መዘቀጥት፣ አንባገነናዊ ስርዓት መፋፋት፣ ማባርያ ለሌለዉ የእርስ በርስ ጦርነት፣ አዋራጅ ስደት፣ ስፍር ቁጥር ለሌለዉ የጥቁር ህዝብ ስንክ ሳር ከቀኝ ገዥዎች ሰንኮፍ (colonial legacy) ቀድሞ ሊጠቀስ የሚችል ነገር ከቶ ምን ሊኖር ይችላል?
ስለሆነም ጥቁር በአለም አደባባይ የፊት ገጽ ላይ በመልካም ስም እና ስብእና በመዓረግ ሲገለጽ ደስ ይለኛል! እንኳንስ ለአገሬ ሰዉ ሊያዉም በግሌ ትህትናዉ ለሚማርከኝ ኢትዮጵያዊ ይቅርና፣ ለማላዉቀዉ ለማያቀኝ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ አሸናፊነት እንደ አቡነ ተክልዬ በአንድ እግሬ ተተክዬ አድሬያለሁ፡፡
ለሌላ ለምንም ሳይሆን ……. የጥቁር ሰዉ ድል ድሌ ስለሆነ ነዉ ያን ማድረጌ፡፡ በዶ/ር ቴድሮስ አሸናፊነት ኢትዮጵያ አገሬ እንኳን ደስ አለሽ! አፍርካዬ እንኳንም ደስ አልሽ! አንባቢ ሆይ ይህን በማለቴ ግን ስልጣን ላይ ያለዉ መንግስት ደጋፊ አድርገህ እንዳትፈርጀኝ አበክሬ አሳስባለሁ!
ከዶ/ር ቴድሮስ አሸናፊነት ባሻገር ግን በጽሞና ሊጤን የሚገባዉ አደገኛ ሁኔታ በፖለቲካዉ መስክ ሲስተጋባ ሰንብቷል አዲስ ክስተት ባይሆንም ፡፡ ጉዳዩ ከሃገር ዉጪ የሚኖሩ ኢትዮጲያዊያን እና ትዉልደ ኢትዮጲያዊያን ብቻ የሚመለከት የባህር ማዶ ሰዎች ግርግር ተደርጎ መወሰድ ያለበት አይመስልም፡፡ በሃር ማዶ የተከካዉና የተቦካዉ ኢትዮጵያ ምድር ላይ ሲጋገር በተደጋጋሚ የሚስተዋል ፖለቲካዊ እዉነታ ነዉ ፡፡
በተለይም በቋንቋና በብሄር ተቧድኖ ለተቀዋሞ እና ለደጋፍ መሰለፍ የዘዉጌ ዋልተኝነትን (ethnic polarization) በማጦዝ የማንወጣዉ የእርስ በርስ ጥላቻና ቀውስ ዉስጥ እየዘፈቀን መሆኑ ልብ ሊባል የሚገባዉ አደገኛ ሂደት ነዉ፡፡ እንዴት ነዉ ነገሩ፣ መጨረሻችን ምን ሊሆን ነዉ የሚያስብል ይመስለኛል፡፡
ጎበዝ ትንንሽ ክስተተቶች ናቸዉ እየሰፉ ሄደዉ የቀዉስና የእልቂት ምክንያት የሚሆኑት፡፡ የጥላቻዉ እና የመገፋፋቱ ስሜት ከምህዋረ ዜና እና ከማሃበራዊ ሚዲያዉ አልፎ በስፖርት ማዘዉተርያዎች መጸባረቅ ጀምሯል፡፡ ከጥቂት ሳምንታት በፊት መቐለ ላይ የተከሰተዉን የኳስ ሜዳ ግርግር ማስታወሱ በቂ ይመስለኛል፡፡
ግነት በሌለበት እዉነታ የኢትዮጵያዉያን የዘዉግ ክፍፍል (ethnic fractionalization) ከግለሰብ አስተሳሰብ አልፎ ወደ ቡድናዊ ስሜት በከፍተኛ ደረጃ አድገዋል፡፡ አገራዊ ማንነት በዘዉጌ ስሜት ተለዉጣል፡፡ ይህ ባይሆን ሁላችን ልኮራበት የሚገባ ጉዳይ በዘዉግ ማንነት ተመዝኖ አስደንጋጭ በሆነ አከኋን ኢትዮጵያዊነት በአለም መድረክ ባልተዋረደ ነበር፡፡
ይህ እንዲሆን በርግጥም ኢትዮጵያን የሚያስተዳድራት ገዥ ሃይል በአላማ ሰርቷል ……. ተሳክቶለታልም፡፡ ከ 26 ዓመታት በኋልም ከተጓዘበት አገርን አደጋ ላይ ከሚጥል የተሳሳተ የፖለቲካ መስመር ለመዉጣት ፍቃደኛ የሆነ አይመስልም፡፡ ገዥዉ መንግስት ኢትዮጵያዊነት የሚል ስሜትን አጥብቆ ይፈራል፡፡
ለዚህ ቀልል ማሳያ ሚሊዮኖች በፍቅር የሚከተሉትን፣ ኢትዮጵያዊነትን የሚያከብር እና የሚዘክርን የጥበብ ሰዉን (ድምጻዊ ቴድሮስ ካሳሁን) ቃለ-መጠይቅ በዘዉጌ ማንነት አልተቃኝም በማለት መንግስት በሚቆጣጠረዉ ምህዋረ ዜና ለህዝብ እንዳይተላለፍ ከልክሏል፡፡ ይህ አይነቱ አሰራር የሚያሳፍር ብቻ ሳይሆን እቺ አገር የማናት የሚስብል ጥያቄን ያጭራል፡፡ ይህን የመሳሰሉ ክስተቶች ናቸዉ ተከማችተዉ ወደ አልተፈለገ ዉዝግብና መገፋፋት የሚያመሩት፡፡
ከገባንበት አዙሪት፣ ሊመጣ ከሚችለዉ አደገኛ የእርስ በርስ ግጭትና ቀዉስ ለታደገን የሚችለዉ በህዝቦች መካከል እኩልነት፣ ፍትህ እና እዉነተኛ ፍቅር መኖር ሲችል ነዉ፡፡ የህዝቦች መስተጋብር እና ደማቅ ፍቅር የሚመሰረተው ከቂም በቀል በጸዳ ልቦና መቀራረብ ሲቻል ነዉ ፡፡
ለዚህ መሳካት በቅድምያ እዉነተኛ የእርቅ መንፈስ በህዝቦች መካከል ሊሰፍን ይገበዋል፡፡ የስርአቱ ባለቤቶች ለ26 ዓመታት ከቀለዱት “ማን ከማን ተጣላና እናስታርቅ” ይሉት አይነት አሰልቺ ኩሸት ተላቀዉ የኢትዮጵያን ለማዳን ሲባል በህዝቦች መካከል እርቀ ሰላም እንዲወርድ ማደረግ ይኖርባቸዋል፡፡
መንግስት ከህዝብ ጋር እልህ መጋባቱን ማቆም ይኖርበታል፡፡ የመንግስት ሰዎች ከእያንዳንዱ ፖለቲካዊ ክስተት ተገቢዉን ትምህርት ወስደዉ ተገቢዉን የእርምት እርምጃ ማስከተል ይኖርባቸዋል፡፡ ካለ ቅጥ እየተለጠጠ የመጣዉ የዘዉጌ ዋልተኝነት አገር የሚያጠፋና የህዝብን እልቂት የሚያስከትል አደጋን አዘሎ እየተከተለን መሆኑን ልንስተዉ አይገባም፡፡
ስለሆነም መንግስት የዶ/ር ቴድሮስ አሸናፊነትን ከግንቦት 20 ማድመቂያነት ባለፈ የተስተዋለዉን ተቀዋሞም አጢኖ የመግባባትና የመቀራረብ ስራዎችን ለመስራት ቢችል ባህር ማዶ ያሉ ወገኖች እና አክቲቪስት ነኝ ባዮችን ከጠርዘኝነት መስመር ወደ መሃል ለመሳብ ይችል ይሆናል፡፡
ይሄ የሚሳካዉ ግን ከዘዉግ ባሻገር በኢትዮጵያዊነት ለማሰብ የሚችል አቅም ያለዉ የመንግስት ሃይል ሲኖር ብቻ ነዉ፡፡ አሁን ያለዉን አገራዊ ቀዉስም ሆነ መጪዉን አደገኛ ሁኔታ መታገልና ማሸነፍ የሚቻለዉ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ ጫፍ እስከ ምዕራብ ዳርቻ ያሉ ህዝቦችን በኢትዮጵያዊነት መፈስ ማስተሳሰርና በእኩልነት ማሰተዳዳር ሲቻል መሆኑን አበክሮ መረዳቱ ቁልፍ ጉዳይ ነዉ፡፡
ያኔ ሃቀኛ ዴሞክራሲያዊና እኩልነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያ ደምቃ ትታያለች፡፡ ያኔ በአለም መድረክ የሚገኝ ድል የጋራ ደስታችን፣ ሽፈታችንም የወል መከራችን ይሆናል፡፡ ለዚሁሉ መሳካት ግን ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ማስቀደም ሆናል!
*************
I don’t think this is a word racing. It should be sharing of ideas. It should not be like this. Just it is better to read and know your differences. You know what, most of the comments written are a reverse of their predecessor comments. And i don’t think anyone will change his mind with the comments written. Do you know why? Because we have a lack of information gathering. For sure you all might argue me that you know what you exactly have written. But let me tell you this there is no 100% genuine social media in this country. Not all but most the social media of this country are racist. So it is better to see in different angle.
Dear Fnini, I wish if I don´t reply to your second comment. But I have to remind you that I am not ignorant as you assumed. I would say I know what I know regarding the overall political crisis we are in and specific challenges that we are passing through every day. Of course, I am not braving by pinpoint a halt solution to calm down the waves of the nation. Nevertheless, I understand that to the minimum, ensuring socio-economic equality, promoting tolerance, maintaining a sprint of brotherhood and cultural integrity would be a rescue lifeboat to pass the current hazards and possible future disasters. These all possible under the flagship of Ethopinaizm. If you don´t buy this idea, we can agree to disagree.
Remain safe!
ዝም ለማት ጊዜ አለው፣ ለማናገርም ጊዜ አለው…… የስደተኞቻችን (አክቲቪስትና ፖለቲከኞች ነን ባዮቹ) ችግር የህ ነው…….መቼ መናገር መቼ ዝም ማት እንደሚገባቸው ምንም አያውቁም…. ብስለቱም የላቸውም IMF WFP WHO …. የመሳሉት ድርጅቶችን የሚመሩ ሰዎች እንዴት እንደሚመረጡ …በዚህ ዙሪያ ያለው የሃያላኑ ስውርና ግልጽ ተጽዕኖ በፍጹም አልገባቸውም….. እስረኞችን ህክምና በመከልከል የሚቀጣ መንግስት ቁንጮ አባል የዓለም ጤና ድርጅት ኖሆ መመረጥ አሳዛኝ ቢሆንም የሳዑዲ ዓረቢያ የሴቶች መብት ጠበቃ ሆና ከመመረጧ ጋር ተያይዞ መከሰቱ የዚህ ዓመት አስገራሚ ክስተት ነው… ነግር ግን ይህን መሰል ክስተት ለዓለማችን አዲስ አይደለም….እናም በዚህን በሌላው ምክንያት የዶክተሩ ተቃዋሚዎች የሚሰሩትን ቢያውቁ ኖሮ አሁን ውሃ ውስጥ የገባች አይጥ ከመሆን በዳኑ ነበረ…..
Dear Yitagesu, I did not claim to have a formula for state formation in my comment to your article.let alone to push the country in to hell.Unless you want to put me in the same box with the government. Which I am not. So don’t be judgmental.
I do understand we are lIving in state of emergency like France and Belgium.I know, listing France and Belgium does not make our situation right. But also the situation we are in doesn’t help your argument to be right either.
I find it very bizarre though, that you use the word segregation to describe the situation in Ethiopia. It shows how far you are from understanding the situation really. Let alone to come up with a solution to the problem.
Let peace be with you
Dear Finin, your formula of state formation is leading the country to the hell. Don´t forget that Ethiopia today is governed under a state of emergency. Do you have a genuine justification why is that happening? The article (which you name it a “trash”) is just claiming to overcome the perpetuate ethnic based polarization and alarming hazards through promoting national unity and social consolidation. In the current Ethiopian context, a sustainable peace and territorial integration can be achieved by downplaying the ongoing ethnic hostility and segregation. Hence if you are willing to understand the spirit of the article from the host point of view, normatively it narrates to wake up and take action to prevent the likelihood of state fragmentation and the follow up possible humanitarian crises. For this end, the government is the primarily responsible agent. Of note, I love Ethiopia like Teddy Afro, Meaza Biru, and other several millions of Ethiopians love it. Loving Ethiopia and the concept of Ethiopianism never overlook the pre-existing ethino-linguistic heterogeneity and other cultural or religious diversity. The moral of the story the ethnic polarization in Ethiopia is becoming very intense and the threat is visible to cost us the country.
I wonder why you write this article? I assume you write it to look fair(if I am wrong for give me for my assumption).
But it is amusing that you can only see Dr.tedros’s colour and origin to support him like your diaspora friends ( except the diaspora use his origin to oppose him).while non of those who elected him for WHO see his origin or colour as merit. Except they were referring his track record as health minister of Ethiopia to support him.
I can’t comprhend why you try to blame the government for the faults of the diaspora. Every body should be responsible for its own action. It is like blaming somebody else for your rubbish article. If your article is rubbish it is only you to blame,if the diaspora community is preaching hate speeches day and night all over, it is them that you have to address not the government.
At last I want to ask you what is ethiopian and ethiopianism mean to you? The thing is the ethiopia I love is completely different to to the ethiopia you love (I am sure you love ethiopia ).The Ethiopia that Teddy afro try to depict in his music is long gone, for good. I am not fond of that ethiopia. My ethiopia which I love is different to the ethiopia of Meaza Biru, teddy afro…. and you (I am not trying to put you in the same basket).but it is ok for all of us to have different views of our country. It is natural because we are so diverse. It is as smilar as Trump’s and Obama’s view of America. Except in our case some are preaching hate and genocide(you can read taddios tantu’s new book). because some have different views than theirs.
So don’t be so hysterical that Teddy afro interview is not aired on EBS. He needs to be educated about the ethiopia that accommodates diversity. Because he is lost in some chauvinists history books.
Peace