(አዲሱ አረጋ ቂጤሳ)
27ኛዉ የኦህዴድ ምስረታ በዓል በአዳማ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በፓናል ዉይይት ተከብሯል፡፡ በፓናል ዉይይቱ ወቅት በተነሱ ዋና ዋና ጥያቄዎች ላይ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕረዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ ምላሽና ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል፡፡
በፓናሉ ማጠቃለያ ፕረዝዳንቱ የደረጉትን ንግግር የተወሰነ ክፍል ዋና መልዕክት ተርጉሜ አቅርቤላችኋለሁ፡፡ መልካም ንባብ!
———–
“በዚህ ሥራ ውስጥ እስካለን ድረስ የህዝብ ተልዕኮ እስካለን ማየት ያለብንን ነገር ያለምንም መሰልቸት ቢያመንም ደጋግመን መነጋገር በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ጥያቄ የጠየቃችሁ ሰዎች ባነሳችሁት ጥያቁ ላይ ልዩነት የለኝም፡፡ 27 አመታት ቆይታችን፤ በዚህ 27 ዓመታት ውስጥ መድረስ የነበረባችሁ ቦታ ደርሳችኋል ወይ ብላችሁ የጠየቃችሁ በሀገሪቱ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት የሚፈጠሩ ለውጦችን ይህ ድርጅት እያየ በመሄድ ላይ ነው ወይ ብላችሁ በጠየቃችሁት ላይ በነዚህ 27 ዓመታት ደጋግመን እየተነጋገርን ያለነው ይህ ድርጅት ብዙ ለውጦችን አምጥቷል፡፡ ይህ አይካድም፤ አይደበቅም ተጨባጭ በመሆኑ፡፡ እንደ ዕውነት በትኩረት ካየን ደግሞ 27 ዓመታት ብዙ ጊዜ ነው፡ መንግስት ሆኖ ሀገር በማስተዳደር 27 ዓመት አይደለም በ7 ዓመት ፣ በ7 ወር ብዙ ነገር ስለሚሰራ ነው፡፡”
———–
“27 ዓታት ወደኋላ ተመልሰን ዛሬ የደረስንበትን ደረጃ ስናይ በእውነት ከወሰድነው ጊዜ ጋር ስናነፃፅር መስራት ያለብንን ሥራ በእውነት ሰርተናል ወይ ብለን ብናይ፣ አልሰራንም፡፡መስራት ያለብንን ሥራ ሰርተን ብንገኝ ኖሮ ህዝቡ ለምን ያኮርፋል? ለምን ይነሳብናል? ለምን ይቆጣል ማመስገን ሲገባው? ስላልሰራን ነው ይህ አያጠያይቅም፡፡ የቤት ሥራችንን ስላልሰራን ነው፡፡ 27 ዓመት ብዙ ጊዜ ነው፡፡ እያየን እዚህ ውስጥ ነው የተወለድነው፣ ልጅነትና የወጣትነት ጊዜያችንን ጨርሰን እያየን አረጀን፡፡ ብዙ ጊዜ ነው እርግጥ ነው የሰራናቸውን ሥራዎች እንደብቅ ማለት አይደለም፣ ለራሳችን እማኝ ከመሆን ይልቅ ህዝቡ እማኝ ይሁንልን፡፡ እኛ የምንሰራው ሥራ ለህዝብ ነው፡፡ እማኛችን ህዝብ ነው፡፡ ይህ ህዝብ ደግሞ እንኳን ብዙ ሥራ ሰርተን ይቅርና በሰራነው ጥቂት ሥራ እማኝ ሊሆነን ችግር የለበትም፡፡
እኛ እንደ አንድ ፖለቲካ ድርጅት 4 ሚሊየን አባላት እንዳሉት ድርጅት እንደ 40፣ 50 ሚሊየን ህዝብ እና ሰፊ ክልል እንደሚያስተዳድር ድርጅት ራሳችንን ስናይ ከትላንቱ ጋር አፈፃፀማችንን ነው ማየት ያለብን፡ ዛሬ ላይ ሆነን ከደርግ፣ ከኃ/ስላሴ ሥርዓት ጋር ራችንን ማወዳደር አለብን ወይ; በዚህ ራሳችንን የምንገመግም ከሆነ ግምገማው ትክክል አይደለም፡፡ ደርግ 17 ዓመት ነው ያስተዳደረው እኛ 27 ዓመት ነው ያስተዳደርነው፡፡ ከዚህ ጋር በምንም መመዘኛ ልናወዳድር አይገባም፡፡ ጊዜዉም የተለያየ ነው፡፡ ብዙ ነገር ተቀይሯል፡፡”
———–

“ዛሬ ከ27 ዓመት በኃላ በምንም መመዘኛ ደርግ ይህን አድርጓል ኃ/ስላሴ ይህን አድርጓል እኛ ይሄን አድርገንልሃል ብለን የምንነግድበት ሸቀጥ በእጃችን የለም፡፡ እንደ ፖለቲካ ድርጅት ህዝብ እንደሚያስተዳድር ድርጅት፤ ራሳችንን የምናይ ከሆነ እንደ ምሣሌ የሚታዩ ሀገሮች በ30 ዓመት ጊዜ ውስጥ ለምሳሌ የኤዥያ አገሮችን ብንወስድ ዛሬ በአለም ላይ በዕድገት የሰማይ ጥግ የደረሱ አገሮች ታሪካቸው የ20፣ የ30፣ የ40 ዓመታት ዕድሜ ነው፡፡ ሌላ ታሪክ የላቸውም፡፡ በዚያ ነው ራሳችንን መመዘን ያለብን እንጂ ወደቄየ ተመልሰን ሞቶ አፈር ከለበሰው ጋር ራሳችንን ዝቅ አድርገን ማወዳደር፣ በዚያ ራሳችንን ማሞኘት ይሆናል፡፡ ከዚህ ተነስተን ስናይ መስራት ያለብን፤ መድረስ ያለብ ደርሰናል ወይ ብላችሁ የጠየቃችሁ አልደረስንም፡፡ አልደረስንም ሣይሆን ትንሽ ነገር ነው የሰራነው ብዙ ነገር ይቀረናል ብለን ራሳችንን መመዘን አለብን፡፡ ብዙ ነገር ይቀረናል፡፡ ለምንድነው እዝያ መድረስ ያቃታን መሮጥ፣ መሄድ ሲገባን ለምን አዘገምን ብዙ ችግር ስላለብን ነው፡፡ ያንን በተሃድሶአችን ደጋግመን ስላየን አልደግመውም፡፡ እንናገራለን እንጂ የምንናገረው ነገር በሽታው ያለበት ሥፍራ የሚያክ አይደለም፣ በሽታው ያለበትን ሥፍራ የሚያድን አልነበረም፡፡”
———–
“እርግጥ ነው ንግግራችን ትልቅ ነው፡፡ ከይቅርታ ጋር ምላሳችንን አርዝመን ብዙ ተናግረናል፡፡ የምላሳችንን ያህል እጃችን ሊደርስ አልቻለም፡፡ የችግሩን ሥፍራ አላየንም አልነካንም፣ አልወጋንም፤ እንጂ እራሳችንን ማየት ቀርቶብን አይደለም፡፡ እርስ በርስ መገማገም ተጨካክነን እርምጃም መውሰድ ቀርቶብን አይደለም፤ መውጋት ያለብንን ሥፍራ አልወጋንም፡፡ ለዚያ ነው ዛሬ ስራችን ጎዶሎ የሆነው፡፡ መንገድ ላይ የቀረነው ብዙዎቻችን ነን፡፡ ትላንት ያሰብነው ለህዝብ ተቆርቋሪነት አጥተን ረስተን መንገድ ላይ ጥለን ያለፍን አውላላ ሜዳ ላይ የቆምን ብዙዎቻችን ነን፡፡
አንዳንዱ የራሱን ጌታ ፈጥሮ የሚሰግድለት አለ፡፡ ጌታ መፍጠር ለምን ይመጣል? ለምን አስፈለገ? ለምን ተፈለገ? ለሰላም? የድርጅታችን መስመር ይህን ስለሚል? ህዝቡ ይሄን ስለሚፈልግ? አይደለም፡፡ በእርግጥ የድርጅታችን ችግር ነበር ወይ? የድርጅታን ችግር ነበር እውነት ነው፡፡ አንድ የሚያመን ሥፍራ እዚህ ጋር ነበር መደባበቅ ስለሌለብን ነው፡፡ ለምንድን ነው ተመልሰን የምንባላው? አንድ ህዝብ ነው ያለን፣ አንድ ሀገር ነው ያለን፣ አንድ አላማ ነው ያለን፡፡ ይህ ከሆነ ለምን እንከፋፈላለን? ለምን እንባላለን? ለምን ደባና ሸር አንደኛችን በሌላኛችን ላይ እንፈፅማለን?”
———–
“የህዝባችን ችግር ሳይሆን የግል ጥቅም ችግር ስላለ ነው፡፡ ከህዝብና ከሀገር ጥቅም የግል ጥቅም ስላለ ነው፡፡ ሌላ አይደለም ሌላ ፍች የለውም ራስን ማስቀደም ስላለ ነው:: የራስ ጌታ ሲፈጥር ደግሞ በሄደበት ሁሉ ጉልበቱ ይብረከረካል፡፡ ወንበር ላይ መቀመጥ እንፈልጋለን ወንበር ላይ መቀመጥ ለስም መሆን የለበትም፡፡ በተቀመጥንበት ወንበር ላይ ወንበሩ የሚፈልገውን ሥራ መስራት ካልቻልን ወንበሩ የሚፈልገውን ውሳኔ መስጠት ካልቻልን ለስም ወንበር ላይ መቀመጥ ዋጋ የለውም፡፡ ስለዚህ የዚህ ዓይነት ችግሮች ስላሉብን ነው ከ27 ዓመት በኋላም መድረስ የሚገባን ሥፍራ ሳንደርስ ታግለን ለታገልንለት ህዝብ ጋር የተቃቃርነው ለዚህ ነው፡፡ ለዚህ ነው የተጨካከነው ሌላ አይደለም፡፡
አሁንም ህዝቡ የመጨረሻ እድል ሰጥቶናል በእውነት ሁሉ ነገር ድኗል ሁሉ ነገር ምላሽ አግኝቷል ሁሉ ነገር አልቆለታል ብለን የምናስብ ከሆነ ሞኝነት ነው፡፡ ራሳችንን ማሞኘት የለብንም ሀገር ሰላም ነው አዎ ሀገር ሰላም ነው፡፡ ግን ሰላም አይደለም፡፡ አጭር ዕድል ነው የሰጠን እንጂ ህዝቡ ሰላም አይደለም፣ እድል ሰጥቶናል የመጨረሻ ዕድል፡፡ እነዚህ ሰዎች ምን እንደሚሰሩ እንይ ብሎ እድል ሰጥቶናል፡፡ ይህን ማወቅ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ በደንብ ማጤን በጣም አስፈላጊ ነው፡፡”
———–
“እንደ ድርጅት፣እንደ መንግስት እያንዳንዳችን ከገባንበት ጓዳ ውስጥ አንገታችንን ይዞ አውጥቶ የፈለገውን ነገር ሊፈጽምብን እንደሚችል እንዲህ አይነት እርምጃ ሊወስድብን እንሚችል አይተናል፡፡በፊልም ሣይሆን በተጨባጭ ውስጥ ኖረን አይተናል ይሄ ቲያትር አይደለም፡፡ ጎበዝ ሌላ አማራጭ የለንም፡፡ ወዲያና ወዲህ የምናይ ሰዎች ካለን ሌላ አማራጭ የለንም፡፡ የእኛ ጌታ ህዝባችን ነው፡፡ ለየክልላችን ህዝብ ነው፡፡ ሌላ ጌታ የለንም፡፡ ለሌላ ጌታ መስገድ የለብንም፡፡ ትልቅ ድርጅት አለን 4 ሚሊየን አባላት አሉን፡፡ አራት ሚሊየን ማለት በጣም ትልቅ ነው፡፡ በአለም ላይ አራት ሚሊዬን አባላት ያሉት ድርጅት ውስን ነው፡ እንደነ ቻይና ያሉት ካልሆነ በስተቀር ውስን ነው፡፡ በቁጥር አይደለም እንዲሁ በስም ብንናገር 50 ሚሊየን ህዝብ ነው እኮ ያለን፡፡ ይህን ይዘን ለምን እግራችን ብርክርክ እንደሚል ለምን እንደምንፈራ ለምን ወደ ጓዳ ተመልሰን አንገታችንን ደፍተን እንደምናጉረመርም አይገባኝም፡፡”
———–
“አሁን ያለን ምርጫ አንድና አንድ ብቻ ነው፡፡ ደጋግመን ስንል እንደነበረው ማዳመጥ ያብን ማየት ያለብን ይሄንን ህዝብ ነው፡፡ ይሄ ህዝብ ሌላ አራማራጭ የለውም፡፡ እንደ ሥራው ክብደትና ድካም እያንዳንዱ ተቀብሎ ይሞክር ብለን አስረክበን ብንወጣም ደስ ይለን ነበር፡ ዛሬ እንደዚህ አይነት ምርጫ አለን? እስቲ ይቅርብን ሌሎችም ይሞክሩት፡፡ ሰባት አመት ሣይሆን 27 ዓመት የለፋንበት ስለሆነ፡፡ አንዳዶችን እንዲያውም ሰውነታችን የዛለ በመሆኑ ፡፡ ሌላው እስኪ ይየው ብለን እንደዚህ መቀባበል ቢቻል እንላለን፡፡ በዚህ መልኩ የተዘጋጀ ነገር ቢኖር ደስ ባለን ነበር፡፡ እውን በዚህ ደረጃ ይህ አለ ወይ ብለን ብንጠይቅ የለም፡፡ ራሳችንን ማታለል የለብንም፡፡ እኛም ደግሞ መሆን ያለብንን ሳንሆን ቀርተን እየተዉረገረግን በመሄድ፣እንዲሁ አስመስለን በመጓዝ ብቻ ረጅም መንገድ መሄድ እንችላለን ወይ ብለን ብንጠይቅ አንችልም፡፡መስቀለኛ መንገድ ላይ ነዉ ያለነዉ፣ራሳችንን ብቻ ሳይሆን ሀገርንም ልናጠፋ ስለምንችል፡፡ ሀገርንም ልናፈርስ እንችላለን፡፡ ሀገር እንደ ድንገት ሲፈርስ ደግሞ አይተናል ሩቅ ሳንሄድ ከጎረቤት ሀገር፡፡ በዕቅድ የሚፈርስ ሀገር የለም፡፡ ስለዚህ ያለን ምርጫ ቆም ብለን አሁንም ደጋግመን ስንል እንደነበረው ጥርሣችንን ነክሰን ከዚህ ህዝብ ጋር ሆነን ለህዝቡ መሥራት ነው ሊያዋጣን የሚችለዉ፡፡ ”
———–
“ከዚህ በኋላ ትግሉ እጅግ መራር ነዉ፡፡ እኛ ታጋዮች ማወቅ ያለብን ምንድነዉ መራር የሚያደርገዉ የሚለዉ ነዉ፡፡ አንደኛ የተሰጠችን ጊዜ አጭር ናት፡፡ ሁለተኛ እኛ እንዳሻን ስንሠራ ዝም ብሎ ተኝቶ የሚያየንና የሚሰማን ህዝብ አይደለም ያለው፡፡ ህዝብ ማለት እኛ የምንቀመጥበት ዝምብሎ እንዲሁ ተሸክሞን የሚውልና የሚያድርንበር ሣይሆን ከሥር እሳት ያለው የሚፋጅ ወንበር ነው፡፡ እዚህ ወንበር ላይ ውለን ማደር የምንችለው ከሠራን ብቻ ነው፡፡ ካለበለዚያ በቁማችን ያቃጥለናል፡፡ ምንም አማራጭ የለንም፤ ስለሆነም ከእንግዲህ ወዲያ የምናደርገው ትግል መራርና ከባድ ነው ለዚያ ደግሞ ራስን አሳልፎ መስጠት ያስፈልጋል፡፡ ዝም ብለን መሥመር ውስጥ ገብተን ስለቆምንና ስለተጓዝን የሚያዋጣን አይመስለኝም፡፡ መራር ስለሆነ፡፡”
———–
“ሌላው ሊታይና መገንዘብ የሚያስፈለገው እዚህ ሀገር ላይ የፌደራሊዝምን ሥርዓት ከመሠረቱት ውስጥ እኛ ትልቅ ድርሻ አለን፡፡ አንዳንዴ የፌደራሊዝም ሥራዓቱ ይቅርና በሀገር ምስረታ ያለንን ድርሻ ዘንግተን የሠራናቸውን ሥራዎች የምንተውበት ጊዜ አለ፡፡ ይህቺ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር እንድትፈጠር ይሄ ህዝብ (ኦሮሞ) ትልቅ ድርሻ አለው፡፡ ይሄንን የፌደራል ሥረዓት በመፍጠር ረገድም ሚና አለውው፤ በፌደሬሽኑ ውስጥ የሚገባንን ለማግኘት መታገል ማለትም ይሄው ነው፡፡ሥርዓቱን መፍጠር ብቻም ሳይሆን የፈጠርነው ሥርጭት ለህዝባችን የሚጠቅም፣ የሚበጅ ማድረግ ይኖርብናል፡፡ ይሄንን ስንል በዚህ ፌደራሊዝም ሥርዓት ውስጥ ምንም አይነት ችግር አይገጥመንም ሁሉንም ነገር ቤታችን ውስጥ ተቀምጠን ይመጣልናል ብለን የምንጠብቅ ከሆነ ስህተት ነው፡፡ የጥቅም ግጭቶች ይኖራሉ፡፡ ይህም በፌደሬሽን ውስጥ ተፈጥሯዊ ነው፡፡ ለጥቅማችን ታግለን ተከራክረን የዚህን ህዝብ ጥቅም ማስጠበቅና ማስከበር አስፈላጊ ነዉ፡፡ ይሄን ማለት ሌላ ነገር መሆን ማለት አይደለም፡፡
———–
አንዳንዶቻችን እየተሳሳትን ያለነዉ እንዲያዉም እያሽቆለቆልን ማንነታችንን እየዘነጋን መጥተን ዬት እንደደረስን ታውቃላችሁ? ስለ ኦሮሞና ኦሮሞነት ማንሳት እንደ ወንጀል መታየት ጀምሯል እኮ፡፡ እንደ ጥፋት እንደ አውሬ እንደ ሌላ ነገር መወሰድና መታየት ጀምሯል፡፡ እኛ ለዚህ አይደለም የታገልነው፡፡ ምንግዜም ቢሆን በየትኛውም መድረክ ላይ ፊትለፊት ወጥተን መናገር ተገቢ ነው፤ ይገባናል፡፡ እኛ ካልተናገርን ማን ይናገርልናል? እኛ የዚህ ህዝብ ተወካይ ነን ካልን እኛ ካልተናገርንለት ማነው የሚናገርለት? ትግል ይሄ ነው? አንዳንዴ ችግር ያልሆነ ነገር እንደችግር የተወሰደ ይመስለኛል፡፡ ደግ ሴት ከወንድሟ ታረግዛለች እንደሚባለው አይነት ነገር ለመፍጠር እየተጓዝን ያለ ይመስለኛል፡፡ We don’t have to be shy! ለዚህ ህዝብ መብት ቆመን መታገል አለብን ካልን መታገል መቻል አለብን፡፡
ደጋግመን ተናግረናል መታገል ምንድነው ትርጉሙ? የህዝቡን ኑሮ መለወጥ ነው፡፡ ሌላ ነገር የለውም፡፡ የመልካም አስተዳደር ችግር ወዘተ አለ፡፡ የግል ባለሀብቶቻችንን ዘንግተናቸዋል፡፡ መቼ ወደ እኛ መጥተው ያውቃሉ? መች አቅርበናቸዉ፣አደራጅተናቸዉ እናውቃለን? በክልላችን የኢኮኖሚና የልማት ሥራ ራሳቸዉንመ ጠቅመው ሀገራቸውንም እንዲጠቅሙ፣ እንዲለዉጡ አድርገን እናውቃለን? እንደዚህ አይነት ዕቅድስ አለን? ብዙ ነገር ግን እናወራለን፡፡ እንደዚህ አይነት ነገር ሠርተን በተጨባጭ ካለን መሬት ላይ የት አለ? ስለዚህ ባለሀብቶቻችንን የግል ጥቅማቸውን ብቻ ሣይን ሀገርንም መጥቀም አለብን በሚል ዕምነት ከዝህ በኋላ በልማት ሥራዎቻችን ውስጥ አሣትፉን መሥራት አለብን፡፡ ያ ሲሆን ነው ኢኮኖሚ የሚቀየረው፡፡
———–
እኛ በዕውቀታችን ሁሉ ነገር አሟልተን አይደለም ሀገር እየመራን ያለነው፡፡ በዕውቀት መታገዝ እና መረዳት አለብን፡፡ በአዲስ ሐሳብና በአዲስ ጥናት መደገፍ አለብን፡፡ በየጊዜዉ እየተቀያየረ በሚሄድ አለም ውስጥ እኛ ራሳችን መለወጥ የሚያቅተን ለምንድነው? ቶሎ ከዚያ ጋር ተላምደን እየተቀያየረ የሚሄደውን ሁኔታ ተረድተን መሥራት የሚያቅተን ለምንነው? በምሁራኖቻችን ስላልተደገፍን ነው፡፡ የእኛ ምሁራን፣ አዋቂዎችና ሐሳብ አፍላቂዎች ሊያግዙን ይገባል፡፡ ለእኛ ብለው ሳይሆን የዜግነት ግዴታ ስላለባቸው፡፡ ለዚያ ደግሞ እኛ በራችን ክፍት መሆን አለበት፡፡ ስለዚህ እነሱን ጋብዘን ድርሻቸውን ሊወጡ የሚችሉበትን መድረክ፣ ሊረዱንና አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ የሚችሉበትን አጋጣሚ መፍጠር መቻል አለብን፡፡ ይሁንና እነሱም ማዶ ተቀምጠው እኛን መውቀስ ብቻ ሳይሆን ማዶ ተቀምጠው ጉድለቶቻችንን ቆጥረው እኛን ማውገዝ ሳይሆን እኔስ ምን ሰራሁ ብለው ራሳቸውን ጠይቀው እኛን መደገፍና መርዳት አለባቸው፡፡
——
የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ፕረዝዳንት ክቡር አቶ ለማ መገርሳ በኦህዴድ 27ኛ የምስረታ በዓልን በማስመልከት በተዘጋጀ የፓናል ዉይይት ያደረጉትን ንግግር እና ቀጣይ አቅጣጫዎች በሶስት ክፍሎች አቅረቤላችሁ ነበር፡፡ የንግግራቸዉ ክፍልየመጨረሻዉ ክፍል እነሆ!
“እኛ በዕውቀታችን ሁሉ ነገር አሟልተን አይደለም ሀገር እየመራን ያለነው፡፡ በዕውቀት መታገዝ እና መረዳት አለብን፡፡ በአዲስ ሐሳብና በአዲስ ጥናት መደገፍ አለብን፡፡ በየጊዜዉ እየተቀያየረ በሚሄድ አለም ውስጥ እኛ ራሳችን መለወጥ የሚያቅተን ለምንድነው? ቶሎ ከዚያ ጋር ተላምደን እየተቀያየረ የሚሄደውን ሁኔታ ተረድተን መሥራት የሚያቅተን ለምንነው? በምሁራኖቻችን ስላልተደገፍን ነው፡፡ የእኛ ምሁራን፣ አዋቂዎችና ሐሳብ አፍላቂዎች ሊያግዙን ይገባል፡፡ ለእኛ ብለው ሳይሆን የዜግነት ግዴታ ስላለባቸው፡፡ ለዚያ ደግሞ እኛ በራችን ክፍት መሆን አለበት፡፡ ስለዚህ እነሱን ጋብዘን ድርሻቸውን ሊወጡ የሚችሉበትን መድረክ፣ ሊረዱንና አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ የሚችሉበትን አጋጣሚ መፍጠር መቻል አለብን፡፡ ይሁንና እነሱም ማዶ ተቀምጠው እኛን መውቀስ ብቻ ሳይሆን ማዶ ተቀምጠው ጉድለቶቻችንን ቆጥረው እኛን ማውገዝ ሳይሆን እኔስ ምን ሰራሁ ብለው ራሳቸውን ጠይቀው እኛን መደገፍና መርዳት አለባቸው፡፡”
——
“የግል ባለሀባቶቻችንን ዘንግተናቸዋል፡፡ መቼ ወደ እኛ መጥተው ያውቃሉ? መች አቅርበናቸዉ፣አደራጅተናቸዉ እናውቃለን? በክልላችን የኢኮኖሚና የልማት ሥራ ራሳቸዉንመ ጠቅመው ሀገራቸውንም እንዲጠቅሙ፣ እንዲለዉጡ አድርገን እናውቃለን? እንደዚህ አይነት ዕቅድስ አለን? ብዙ ነገር ግን እናወራለን፡፡ እንደዚህ አይነት ነገር ሠርተን በተጨባጭ ካለን መሬት ላይ የትአለ? ስለዚህ ባለሀብቶቻችንን የግል ጥቅማቸውን ብቻ ሣይን ሀገርንም መጥቀም አለብን በሚል ዕምነት ከዚህ በኋላ በልማት ሥራዎቻችን ውስጥ አሣትፉን መሥራት አለብን፡፡ ያ ሲሆን ነው ኢኮኖሚ የሚቀየረው፡፡
——
“የመጨረሻዉን ዕድል ሰጥቶን እንየዉ ብሎ ከሁሉም በላይ ይህንን በአል በዚህ መልኩ ተቀምጠን እንድናከብር ትልቁ ባለ ድርሻና ይህንን ሰላም ለሰጠን ህዝባችን ያለኝን ክብርና ምስጋና በናንተ ፊት ላቀርብ እወዳለሁ፡፡ ይህንን ሰላም ያጎናጸፈን መሳርያችን ወታደሮቻችን ወይም መዋቅራችን አይደለም:: ህዝባችን ነዉ ዕድሉን የሰጠን፡፡ ከሁሉም በላይ ይህንን ማወቅ ይገባናል፡፡ ለሰጠን እድል ደግሞ እውቅና ልንሰጠዉ ይገባናል፡፡ የሰጠን ዕድል ደግሞ የመጨረሻዉ ነዉ፡፡ የተለያየ ካርድ አይተናል፤ ቢሆንም ግን አሁንም የመጨረሻዉን ዕድል ሰጥቶናል፤ ይህ ትልቁ ዕድል ነዉ፡፡ በዚህ ዕድል ደግሞ አዉቀን መጠቀም የኛ ድርሻ ይሆናል፤ ቢሆንልንና ብዙ ነገር ብናወራ ጥሩ ነዉ፤ የሚድን ከሆነ አንዴ የወሰዱት መድሃኒት ነዉ የሚያድነዉ፤ ላለፉት ስድስት ወራት ብዙ ያወራን ስለሆነ በዚህ ሁኔታ ተደጋግፈን ተረዳድተን የምንሰራ ከሆነ እንለውጠዋለን የማይለወጥ ነገር የለም፡፡ “
——
“እኛም ድርጅት የተባልነው ለለውጥ ነው እንጂ ለሌላ አይደለም፤ መታገል ያስፈለገን ለለውጥ ነው፡፡ ከሰራን እንለውጣለን፤ ከተቀመጥን እንጠፋለን፤ ሀገር እናጠፋለን፤ አሁንም ህዝባችን ያለዉ ችግር ብዙ ነዉ፡፡ እዉነት ነዉ ያስመዘገብነዉ ዉጤት አለ፤ በህዝባችን ዉስጥ ብዙ ችግር አለ፤ ብዙ የሚያሳፍሩን ነገሮች አሉ፡፡ ነገር ግን አንድ ቀን ለዉጥ ያመጡልኛል ብሎ ነዉ በተስፋ የሚጠብቀን፤ ስለዚህ ቁመን እንስራ፡፡ ትናንት ቃል እንደ ተገባባነዉ ቃል መገባባትና መማማል በቂ አይደለም ሰርተን መታየት ነዉ ያለብን፡፡ ሰርተን ተጨባጭ ለዉጥ አምጥተን ነዉ ማሳየት ያለብን፡፡ ይሄ ከሆነ ህዝባችን ማክበር ብቻ አይደለም በትከሻዉ ይሸከመናል፡፡ በታሪካችን ውስጥ አይተነዋል እስቲ 27 ዓመታት ወደ ኋላ ተመልሳችሁ አስታውሱ በሶስትና አራት ዓመታት ውስጥ ጥሩ ነገር ስንሰራ ሕዝባችን ምን ያህል እንዳከበረን እናውቃለን፡፡ ይህንንም በተግባር አይተናል፡፡ አጣጥመን የማናውቀው ነገር አይደለም ከመስመራችን ወጥተን ማንቀላፋት ስንጀምር ደግሞ ምን ይህል እንደሚቀጣን አይተናል፡፡ ከዚህ በላይ ትምህርትና ልምድ የሚሆነን ነገር የለም፤ ስለሆነም ኑሮአችሁን በአቋራጭ የመለወጥ ፍላጎት ያላችሁ ሰዎች ካላችሁ ከአሁን ወዲያ ይህ ቦታ በዚህ የሚመረጥ ቦታ እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል፡፡ ሁኔታው ለዚህ ምቹ አይደለም፡፡”
——
“ስለሆነም ይህንን በዓል ስናከብር የሕዝባችንን ችግር በማሰብ፤ ትናንት የነበርንበትን ጨለማና ችግር በማስታወስ ድክመታችንን በማስታወስና ከአሁን በኋላ የዚህን ሕዝብ ኑሮ እንዴት መለወጥ አንችላለን በማለት እያንዳንዳችን ምን መስራት እንዳለብን ትኩረት ሰተን ካየነው በዓላችን መልካም በዓልና በሚቀጥለው ዓመት ደግሞ ፈጣሪ ረድቶን ስኬታማ የሆነ ሥራ ሰርተን አንገታችንን ደፍተን በአዳራሽ ውስጥ ተሰብስበን ሳይሆን ከሕዝባችን ጋር ሜዳ ላይ ወጥተን ጨፍረን የምናከብረው ይሆናል፡፡ ስለሆነም በዚህ መልኩ እንስራ ከሰራን ደግሞ ለውጥ እናመጣለን፡፡ ለውጥ አስመዝግበን የምናውቅ ስለሆነ ይህንን በመስራት የዛሬውን ቀን በዚህ መልኩ በማስታወስ ሁላችንም ማለትም ሕዝባችንም በለሃብቶችም ምሁራንም የሀገር ሽማግሌዎችም አባገዳዎችም ተረዳድተን የህዝባችንን ኑሮ እንለውጥ እላለሁ ጥሪአችንን አክብራችሁ ጊዜአችሁን ሰጥታችሁን ስለተገኛችሁ አመሰግናለሁ፡፡”
——
ቸር እንሰንብት!
*********
People are really listening to you and hoping to adhere to your thoughts, personality, I accept100% support what you said about the elite and attracting investors. It is Time to buckle up and start working with the hardest stamina and challenge at hand. But change needs to happen if you are serious enough to eradicate fear, surpass the greed and boost national feelings. Your regional administration has always taken up new initiatives that is easily adopted to others. I hope your speech will inspire other regions to think differently. Wishing you success to your administration. I love your positive spirit, your energy and putting thing on the table, your boldness. May God support you and I wish you health, inner peace andand balanced judgment. I hope to support the region in my capacity.
Let me add few points .your choice of this interesting name“ dergu temelese ”correct because it precisely represents your personality and shamed for you for keeping your loyalty for already dead dergue regime and dictator mengistu. The fate of Eritrea was not in hands of meles (eprd) but mengistu. Eritrra got its freedom and got rid of dergue regime seven days before EPRDF had controlled Addis Ababa. Meles by no means should be responsible for Eritrean separation. What only he did was he legalized the process and thanks for that he has saved the rest of the country from disintegration. The main reason that allowed Eritrea for its separation from Ethiopia was mengistu,s incapability and his dysfunctional leadership .you must not forget those prominent senior generals those slaughtered by mengistu . Thanks for mengistu the country lost More than thirty its most senior and experienced military commanders .without counting other officers the number of massacred generals was around thirty. So you can judge how would our soldiers could continue fighting without commander. If somebody to be blamed for losing Eritrea it is mengistu without question.
mr.dergu temeles! it is not EPRDF that shoulm be blamed for separation of eritrea,but mengistu for his wrong handling of the ertrean people,s question and his dysfunctional leaderhip and selfish behaviour.Meles by allowing eritrean freedom saved the integrity of ethiopia for dismantling.
There is a British saying. “If wishes were horses, beggars would ride them.” I Wish Emperor Tewodros was born again to unite Ethiopia.But, it is impossible. We can not deny history. Although Mengistu is a dictator, he had exerted all his efforts to protect the territorial integrity and unity of our motherland. Thanks to the support rendered by CIA and MI6, EPLF and TPLF have controlled the the Ethiopian political power. Look, ELF was the first Established guerrilla group to separate Eritrea from Ethiopia. Because of its Arabic ideology, CIA dismantled it. I can mention names of many liberation movements languished by the CIA. So long as the TPLF serves the interests of CIA believe me, it can stay in power for a long period of time. If I were you, before I start my struggle, I would assess the political environment and set the right tactic and strategy to defeat my enemy. Emotional struggles engulf the lives of innocent citizens.
ለአዲሱ የክልሉ ሪእሰ -መስተዳድር ለክቡር አቶ ለማም ሆነ ለሌሎች ጥቂት አስተያዬቶችን መስጠት አፈልጋለሁ፡፤የአሁኑ አማራር ማለትም አቶ ለማ የችግሩን ምንጭ እየደረሳችሁበት ያላችሁ ይመስለኛል፡፤ ለድክመቶች ሰበብ መፍጠርና በሌላ ማላከክ እንደማያስከድ የተገነዘባችሁ ይመስላል፡፡ ያለፉትን ጥረቶችና የክልሉ ህዝብ የጎናጸፈዉን የልማት ትሩፋት እዉቅና መስጠት ተገቢ ነዉ፡፤ለሃያ ስድስት ዓመታት ሲሰራ የቆየዉን ግዙፍ ስራ በማጣጣል ከዜሮ መጀመር አይቻልም፡፡ቀደም ሲል የተሰሩትነ እዉቅና ሰጥቶ የጎደለዉን ለማሟላት መጣሩ ብልህነት ነዉ፡፡ ሁለተኛ ኦሮሚያ ዉስጥ የነገሰዉ የተዛባ አመለካከት ሆን ተብሎ የፈጠራ ታሪክ እየተወራ ለሌሎች ህዝቦች መልካም አመለካከት እንዳይኖር እየተደረገ ያለዉ አካሄድ በመሰረቱ መቀየር አለበት፡፤የትግራይ ህዝብና ድርጅቱ (ህወኃት)የኦሮሚያ ህዝብና መሪ ድርጅቱ (ኦህዴድ)ላይ ጫና እንደሚያደረግ ተደርጎ የሚናፈሰዉ አሉባልታን መታገል ይጠበቅቦታል፡፡ የኦህዴድ አመራሮችን የአመራር ድክመት በህወኃት ማላከክ አዋጭ ፖለቲካ አይደለም፡፤ በተመሳሳይ መልኩ ያልነበረ የሃሴት ታሪክ አየተፈበረከ ከጭቁን የአማራ ህዝቦች ጋር ደም ለማቃባትና በጠላትነት እንዲተያይ ለማድረግ ታስቦ እየተደረገ የቆየዉን አደገኛ ዘመቻ ሎቆም ይገባዋል፡፡ ሌላዉ የኦሮሚያ ህዝብ እንዲያዉቀዉ ማድረግ የሚገባዎት በኦሮሚያ ክልል ብቻ አስካሁን የተሰሩት የልማት ስራዎች በመላዉ አገሪቱ ባሉ ሌሎች ክልሎች በድምር ከተሰራዉ የበለጠ እንጂ የሚያንስ እንዳልሆነ ነዉ፡፤ህዝቡ አስካሁን የተሰራዉን አምኖ ለመቀበል የዳገተዉ ልማቱ በተጨባጭ ስላልነበረ ሳይሆን እጅግ አስቀያሚ የሆነ ዝርፊያና የመልካ አስተዳደር ዕጦትና የመብት መደፍጠጥ ስለሚደርስበት ነዉ፡፡ህዝቡ በክልሉ አስተዳደርና በፌዴራል መንግስቱ እምነት እንዲኖረዉ ማድረግ ይገባል፡፡ ንጹህ አይምሮና ንጹህ እጅ ያላቸዉ በርካሽ ፖለቲካና በጥቅም ያልጎደፉ ደፋርና አድርባይ ያልሆኑ የክልሉን ወጣት ምሁራንን ከየቦታዉ በወረንጦ እየለቀማችሁ አሰባስባችሁ ልትጠቀሙባዉ ይገባል፡፡ ጠባብ አመለካከት የተጠናወታቸዉ አንዳንድ በድርጅቱ ዉስጥ መሽገዉ የሚገኙ የእነ ጃዋርና የአነ ዳዊድ ወክሎችን መንጥራችሁ ማዉጣት ካቻላችሁ ክልሉም ሆነ መላዋ ሀገራችን ሰላም አይኖራቸዉም፡፡አዳዲስ የልማት እቅድ (የኢኮኖሚ አብዮት) ስትነድፉ ለለዉጥ ፈቃደኛ ያልሆኑና ለዉጡን ሊመሩ የማይችሉ ግትር የቀድሞ አመራሮችን በአዲስና ለለዉጥ ቁርጠኛ በሆኑት ካልተካችሁ አብዮት ያላችሁት ነገር መሳካቱ አጠራጠሪ ነዉ፡፡ ይህን ካልኩ በኋላ በኦሮሚያም ሆነ በቀሩት የሀገራችን ክልሎች የመልካም አስተዳደር እጦትና ለሀገሪቱም ደህንነት ስጋት እንዲፈጠር እያደረገ ያለዉ አሁን በሀገራችን እየተሰራበት ያለዉ የክልሎች ያልተመጣጠነና ከፍተኛ ልዩነት ያለዉ የቆዳ ስፋት መኖር ይመስለኛል፡፡ እጅግ የተለጠጠ ሰፊ ክልል ይዞ ቀልጣፋ የሆነ የአስተዳደርና የልማት ስራ ለመስራት አዳጋችነቱ ግልጽ እየሆነ የመጣ ይመስለኛል፡፡ ለየክልሉ ህዝብም ቢሆን አመቺነት ያለዉ አይደለም፡፡ስለዚህ አሁን ያለዉ የክልሎች የቆዳ ሰፋት ጠበብ እንዲል ተደርጎ ቀልጣፋ አስተዳደር መፍጠር ይገባል፡፤ በዚሁ መሰረትም አማራ ክልል ሶስት ቦታ፤ኦሮሚያ አራት ቦታ፤ሶማሊ ክልል ሁለት ቦታ፤ ደቡብ ህዝቦች ሁለት ቦታ አፋር ክልል ሁለት ቦታ፤ ትገራይ ሁለት ቦታ እንዲከፈል ሆኖ በድምሩ ተጨማሪ ዘጠኝ (9)አዳዲስ ክልሎች እንዲፈጠሩ ይደረጋል ፡፡በየክልሉ የነበረዉ ህዝብም በአዲሶቹ ክልሎች መካለሉ ካልሆነ በስተቀር እንደ ድሮዉ በራሱ ቋንቋ ራሱን እንዲያስተዳደር ስለሚደረግ ህዝቡ የሚያጣዉ ነገር አይኖርም፡፡ዋናዉ ቁምነገር ቀልጣፋ አስተዳደር ለመመስረትና ልማቱነ ለማጣደፍ እንዲሁም የደህንነትና የጸጥታ ችግሮችን በተሻለ ለመቅረፍ ማስቻሉ ነዉ፡፡አላስፈላጊ ወጭ በመቀነሱ ረገድም ጠቀሜታዉ የጎላ ነዉ፡፡ ከዚያ ዉጭ ህዘቡ የሚያጣዉና የሚጎድልበት ነገር አይኖርም፡፡ከፌዴራላዊ ስርአቱ ጋርም ቢሆን አንዳችም የሚያጋጭ ወይም የሚቃረን ነገር የለዉም፡፡ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ ምሁራን አስተያየት ቢሰጡበትና ሃሳቡ እንዲዳብር ቢደረግ ፍላጎቴ ነዉ፡፡
Really it was interesting speech if he try to put every points that he mentioned above on the ground, his people living condition will be changed. The other regions can also take lesson from his great speech to motivate their people to do more to alleviate development problems. Let God help you to realize your dream for your people!!!!
እውነት የትግራይ ሰው ይህን ያህል ያስፈራል 6% እንዴት ብሎ 96% መቆጣጠር ይችላል። በቁምህ ትቃዣለህ፣ ትግራይ ሲባል ኣንተ እንድትወለድና እንዳትወለድ እንደመልኣክ ፍርድ የሚሰጥ ኣመሰልከው። ለነገሩ ስዩመ እ/ር ትእዛዝ ተቀብሎ ኣሜን ብሎ የኖረ ኣባትህ፣ ትግሬዎች እምቢ ብሎ ደም ከፍለዋል ብሎ እንደነገረህ እርግጠኛ። ኣትቃዥ ንቃ። ኦሮሞ ትናንትም ኦሮሞ ዛሬም ኦሮሞ ነገም ኦሮሞ ኣምነህ መቀበል ኣለብህ። ኩሩ ህዝብ። ኢ/ያ ያለ ኦሮሞ ህዝብ ምንም ጣፋጭነት የላትም። የሻገተ የትምክህት ኣስተሳሰብ ፋቅ በቁምህ እንዳትሰምጥ። Never again Emperors in the heart of Ethiopia. Find your place may be in USA.
የኦህዴድም ሆነ የሌላው ኢህአዴግ ፓርቲ ችግር እንደ መዥገር ተጣብቀው የድርጅታቸውን ደም የምመጡትን አድር ባዮችን ያለማስወገዳቸው ነው። እነዚህ ግለሰቦች መሰሪ በመሆናቸው አካሄዳቸውን ለማወቅ በጣም አስቸጋሪ ነው።ሌላው የኦህ ዴድ ችግር በአንድ ወረዳ ወይም ዞን ውስጥ ወሳኝ ቦታ የሚቀመጡት የአንድ ቤተሰብ ሰወች በመሆናቸው በግምገማ ወቅት ተደራጅተው ሌላውን ስለምመቱ መልካም አስተዳደር ማስፈን አይቻልም። ለምሳሌ እኔ ስኖርበት በነበረው አንድ የኦሮሚያ ወረዳ አስተዳደሩ፣ የፖሊስ አዛዡ፣ የመዘጋጃ ቤት ሀላፊና ዋና የፍርድ ቤት ዳኛ የስጋ ዘመዳሞች በመሆናቸው ሁላቸውም የሚሰሩት የቤተሰብ ጥቅም ለማስከበርና አልፎም የተፈጠሩበት ማህበረሰብ(ጎሳ) ጥቅም ብቻ ነው የሚያስጠብቁት። ይህ በመላው የኦሮሚያ ዞኖች እንድያውም ከክልል እስከ ወረዳ ያለውን መዋቅር በአንድ ቤተሰብ እስከ መያዝ የተደረሰ ነው። አሁንም ብሆን የኦሮሚያ ክልል ችግር በቀላሉ የምፈታ አይመስለኝም። የኔ ስጋት የህዝብ አመጽ እንደ ገና ከተቀሰቀሰ እንደ ሶርያ እንዳንሆን ነው።
መፍትሄው በሁሉም የኢህአዴግ የአስተዳድር መዋቅሮች the right person at the right place የሚለውን ስለት መጠቀም ነው። እውቀት አጠር ሰወችን አምጥተን ያለአቅማቸው ስልጣን ማሸከም ማቆም አለብን።
ኢህአዴግ ይህንን እስካላደረገ ድረስ መንገዳገዱ አይቀሬ ነው። ከቡር አቶለማ መገርሳ ያሉት ነገር በትክክል የምተገበር ከሆነ ሀገሪቱ ከገባችበት ማጥ በፍጥነት እንደምትወጣ ሙሉ ተስፋ አለኝ።
!!እ/ር ሀገራችንን ይባርክ
ዘመን ተሻጋሪ ንግግር። እ/ር ይርዳህ ክቡር ፕረዚደንት ለማ መገርሳ። እውነት ግዜ የለም ፍጠኑ ምድረ ዲያስፖራ ኣይናችሁ ለማጥፋት ሽርጉድ እያለ ነው። ብዙ ሊፈነዳ የተቃረበ ችግር ኣለ መድሃኒት ኣበጁለት።
Your excellency if you are not regret, I want to add some point which is always disturbing me. That is the relation of Oromo people with others.
Besides economical issues there are a lot of tasks you are supposed to do. The most important and urgent issue is to repair and renew the already spoiled and broken historical relation with other nations. The OLF leaders and other devil advocates like jawar had done a lot for decades. With your bravely and wise leadership and by mobilizing the broad oromo people (the youth) without any doubt oromia will sparkle and the brotherly and tight cohesion of oromo people with the rest of Ethiopian people will strengthen. It is not for its large population or size of land that oromia should be known, but being example for its best achievements in all aspects of developments. Let god help you!
BRABO president Lema! I think the great OromO people finally got its true leader.What a great historical speech where the great oromo peaple openly praised as founder & builder of our beloved country,Ethiopia.your speech is really a bomb shell for separatist,narrow minded terrorist group , OLF leaders who where dreaming 4 decades 2 dismantle our great nation.it is great courage to recognize the previous mistakes.But u must acknowledge as well to some successful achievements of previous administrations. Descrditing all the previous good deeds may pose you easly for early disapproval.It is a great blow for those accustomed 2 cover their weakness by blamming the already dergue regime for everything.you are blessed by God when chosen for this responsibility at this particular moment.without any doubt oromia will sparkle.let god help you!
fuck your mesferarya ye alemayehun ita siyasibulet zim blen yemnay ymeslihal indyawum yane bedenb defrso yteral dergu tebyewu
It seems good speech.However, believe me, unless u serve the interest of TPLF you will face the fate of Alemayehu Atomsa. Those TPLF cadres control 50% of the resource of Ethiopia while representing only 6% of the Ethiopian people (Tigrians). How on Earth TPLF officials who struggled to liberate Tigray from economic hardship see Oromos while using their own resources?