(አስፋው ገዳሙ ([email protected]))
1/ መግቢያ
የኢትዮጵያ ክልሎች አወቃቀር ሁሉንም ኢትዮጵያውያን አብረውና ተከባብረው እንዲኖሩ የሚያስችል ቢሆን ደስ ይለኝ ነበር፡፡ በተለያዩ ወቅቶች ኢትዮጵያን ያስተዳደሩ ገዢዎች ለህዝቡ ምቾት ሳይሆን ለራሳቸው በሚመች መልኩ ሃገሪቱን ሲስተዳድሩ እንደነበር ይታወቃል፡፡ የአሁን መንግስትም ለራሱ በሚመቸው መልኩ እያስተዳደራት ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን ብዙ ሰዎች፣ በተለይም የጎንደር ተወላጆች በደርግና በአጼ ሃይለስላሴ ወደ ነበረው አከላለል ካልተመለስን እያሉ ይገኛሉ፡፡ ይህ ጥያቄያቸው እንደ ድሮው ቋንቋው አማርኛ፣ ሰንደቅ ዓላማው ልሙጡ አረንጓዴ፣ ብጫ፣ ቀይ እንዲሆን ይፈልጋሉ፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ግን ወልቃይትና ፀገዴም ወደ ጎንደር ካልተካለሉ እያሉ ይገኛሉ፡፡ ጥያቄው የተነሳበት ቦታ፣ ታሪካዊና ነባራዊ ሁኔታ ግን አሁን ካለው አከላለል አንፃር ወደ መግባባት ሳይሆን ወደ ንትርክ የሚያመራ ነው፡፡ ወልቃይት በአማራ ክልል ስር ስለነበር ወደ አማራ ክልል ይመለስ የሚሉት ጥያቄ በዚህ የሚያበቃ አይመስለኝም፡፡ ቤንሻንጉል ጉሙዝም ወደ አማራ ካልተካለለ ሊባል ይችላል፡፡ ሲጀመርም የጌቶች ትእዛዝ እንጂ የህዝብ ጥያቄ ነው ለማለት ይከብዳል፡፡
ሁለት እረኞች ራቅ ብሎ በሚገኘው አንድ ትልቅ ቋጥኝ ላይ የሆነ እንስሳ አሻግረው ያያሉ፡፡
አንዱ፡- እዛጋ ያለው እንስሳ ምንድነው?
ሁለተኛው፡- እኔ እንጃ፤ ግን አሞራ ሳይሆን አይቀርም፡፡
አንዱ፡- እንዴ! አሞራ ትላለህ እንዴ? ባክህ ጅብ ነው፡፡
ሁለተኛው፡- ኧረ ተው አሞራ ነው የሚሆነው፤ ጅብ ከመቼ ነው ቋጥኝ ላይ የሚወጣው?
አንዱ፡- በል ወደድክም ጠላህም ጅብ ነው፡፡
በዚህ የተነሳ አሞራ ነው፤ የለም ጅብ ነው እየተባባሉ ከቆዩ በኋላ ሁለተኛው እረኛ እሺ እንግዲህ ወደዛው ሄደን እናረጋግጥ ይላል፡፡ ሄዱ፡፡ ቋጥኙ አጠገብ ሲደርሱ እንስሳው በረረ – እውነትም አሞራ ነበርና፡፡ አንደኛው እረኛ ምን ቢል ጥሩ ነው? ‹‹ይኽ እንስሳ ቢበርም ጅብ ነው››፡፡ የወልቃይት ጥያቄም – በእኔ እይታ ጥያቄ ሳይሆን ትእዛዝ ነው – ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ ወልቃይት መሬቱም ሆነ ህዝቡ ትግራዋይ ቢሆንም አማራ ነው የሚል ትእዛዝ፡፡ በዚች አጭር ፅሑፍ ይህን እንድል ያስቻሉኝን ምክንያቶች እንደሚከተለው አቀርባሎሁ፡፡
2/ የታሪክ መዛግብት ስለወልቃይት ምን ይላሉ?
ስለ ታሪክ ጠቃሚነት ሲወራ ሁሌም ቀድሞ የሚጠቀሰው የሮማ ትልቅ የህግ አስተማሪና ፈላስፋ እንደነበር የሚነገርለት ማርቁስ ቱልየስ ሲሰሮ ነው፡፡ሲሰሮ አንድ ሰው ከመወለዱ በፊት ያለውን ታሪክ ካላወቀ ዕድሜ ልኩን ህፃን ሆኖ እንደሚቀር ያትታል፡፡
‹‹To be ignorant of what occurred before you were born is to remain always a child. For what is the worth of human life, unless it is woven into the life of our ancestors by the records of history?›› ~Marcus Tullius Cicero(106-43 BC)
የእኛ ሃገር ታሪክ ግን የታሪክ አፃፃፍ ህጎች ተከትሎ ስለማይፃፍ ሃገራችን እኛ ከመወለዳችን በፊት የነበራት ምስል ጥርት አድርጎ ከማሳየት ይልቅ ያደበዝዘዋል፡፡ የታሪክ ፀሐፊዎቹ አንዴ መለኮታዊ ያደርጉታል አንዴም በዘመኑ ለነገሱ ሰዎች ሲባል እየቆራረጡ ያቀርቡታል…መፃፍ የነበረበት ሳይፃፍ ይቀራል፤ ያልነበረም ይጨመራል፡፡ በዚህ መክንያት የታሪክ መዛግብ የሚሉትን እንዳለ ከመጠጣት ይልቅ ነባራዊ ሁኔታዎችን ማገናዘብ ተመራጭ ይመስለኛል፡፡
ቢሆንም ግን ተክክለኛው ታሪካችን እስኪፃፍ ድረስ ያለውን እየጠቃቀስን መወያየት እንጂ ሌላ አማራጭ የለንም፡፡እንትና የተባለ ፈረንጅ የሚለው ትርክት እየመረረንም ቢሆን እንጠቀምበታለን፡፡
ስለወልቃይት ከተነሱት በመጠኑም ቢሆን ሚዛናዊ የሚመስል አፃፃፍ የተከተለው ዘ-አዲስ በሚል የብዕር ስም የተሰራጨው ፅሑፍ ነው፡፡ የፅሑፉ ዓለማ ወልቃይት ለሺህ ዓመታት ከትግራይ አስተዳደር ውጪ እንደነበር ለማሳየት ይሞክራል፡፡ ሆኖም ግን ሆን ብሎም ይሁን በስሕተት የዘለላቸው እውነታዎች አሉ፡፡
ዶክተር ገላውድዮስ አርኣያ በርባዳስ የተባለ ፅሐፊን ጠቅሰው የትግራይ ግዛት እስከ ሌማሊሞ ተራሮች ሊደርስ እንደሚችል ፅፈዋል:: ከቪኦኤ ባደረጉት ቃለ መጠይቅም ተናግሯል፡፡
‹‹[Tigray]…the kingdom has near circular shape; unless we wish to extend, as some maintain should be done, as far as the Lamalmon mountain range.››[1]
ሆኖም ግን የበርባዳስ ፅሑፍ ለትርጉም ክፍት ስለሆነ የህዝቡንና የአከባቢውን ባሕልና ቋንቋን መሰረት አድርጎ በተደረገው የክልሎች አወቃቀር ወልቃይት በትግራይ ክልል ውስጥ መሆኗን ሊገርመን አይገባም ይላሉ፡፡
‹‹All I have argued was that Wolkait, a Tigrigna entity, by all measure, would not be surprising if it becomes part of Tigray.>> [2]
የዶክተር ገላውድዮስ ፅሑፍ በዘመነ መሳፍ(17ኛ ክፍለ ዘመን) ሽረ ማእከላቸውን ያደረጉ ደጃዝማች ገላውድዮስ ወልቃይትና ሰራዬን(የኤርትራ ግዛት) ጠቅልለው ያስተዳድሩ እንደነበር ያወሳል፡፡በዘመነ ደጃች ውቤም ወልቃይት በትግራይ አስተዳደር ስር እንደነበር ይጠቅሳሉ፡፡በተጨማሪም ራስ ሚካኤል ስሑል ትግራይና ጎንደርን ጠቅልለው ያስተዳድሩ እንደነበር ይታወቃል…ዶክተር ገላውድዮስም በግልፅ አስቀምጠውታል፡፡
ዶክተር ገላውድዮስ ‹‹ትግሬ እንጂ ትግራይ ተከዘን ተሻግሮ አያውቅም›› የሚሉት መፈክር ከላይ ከተጠቀሱት ታሪኮች በተጨማሪ እንደሚከተለው ውድቅ አድርገውታል፡፡በዚሁ መረጃ መሰረት እንኳን ወልቃይት ቤገምድር(የቤጃ ምድር)ና ዋግ በትግራይ ይተዳደሩ እንደነበር ተጠቅሰዋል፡፡
‹‹Tigray, the most northerly province of Ethiopia; Almeida, who described it as in ancient times ‘the foundation and head’ of the entire Ethiopian monarchy, considered it still the ‘best part’ of the country, while Ludolf later described it as ‘the best and most fertile’ part of it.
The province began, Almeida says, at the twin Red Sea ports of Massawa and Hergigo, and extended south-eastwards along the coast as the tiny harbor of Defalo. Inland the province was bordered, from east to west, by the Dankali ‘Kingdom’, Angot, Doba, Begemdir and Semen. [Beckingham and Huntingford, Some Records of Ethiopia, pp. 14-15; J. Ludolf, A New History of Ethiopia, London, 1682, p. 13.8]>>
Both Beckingham and Ludolf do not say that Tekezze is the Western frontier of Tigray, and Ludolf especially, who had made extensive studies on Ethiopia, and who is credited as the founder of Ethiopian Studies, put Wag as one of the 27 prefectures (districts or regions) of Tigray.›› [3]
በተጨማሪም በራስ ወልደ ስላሴ(ሕንጣሎ ወይም እንደርታ ማእከላቸውን አድርገው ትግራይ የገዙ ነበር) ዘመን ትግራይ ክብ ሳይሆን የአራት መአዘን ቅርፅ(ትራፒዝዮም) እንደነበራትና ግዛትዋም እስከ ሰሜን ይደርስ እንደነበር ዶክተር ገላውድዮስም ሆነ ዘ-አዲስ በጠቀሱት መፅሐፍ ውስጥ ተዘግቧል፡፡
‹‹The kingdom of Tigre is bounded by the Belka, Boja, Takue, and several wild tribes of Shangalla on the north; by the mountains of Samen on the west; and by the Danakil, Doba, and Galla, on the east and south; comprehending and extent of about four degrees in latitude, and about the same in a longitudinal direction, and forming in shape the irregular figure of a trapezium.›› [4]
በተጨማሪም ራስ ወልደ ስላሰ ወልቃይትና ዋልድባን ያስተዳድሩ(ያስገብሩ) እንደነበር እንደሚከተለው መስከሯል፡፡
“Above Temben, to the westward of Axum, is situated the province of Shire, which forms a pretty sharp angle with the Tecazze in the latitude of 14º; and on the opposite side of the river extend still farther westward, the districts of Waldubba and Walkayt, both of which continue to pay tribute to the Ras”. [5]
ስለዚህ፣ በሆረን አፌርስ ዘአዲስ በሚል የብዕር ሰም ‹‹ወልቃይት ላለፉት ሺህ ዓመታት በትግራይ ስር ተዳድራ አታውቅም – የታሪክ ማስረጃዎች››“ [6] የሚለው ሙግት ተአማኒነቱ አጠያያቂ ነው፡፡ለምሳሌ፣ ላስታ በትግራይ ግዛት ውስጥ ነበር፡፡አሁን ግን ወደ አማራ ክልል ተካልለዋል…የአከባቢው ሕዝብ የሚናገረው አማርኛ ስለሆነ፡፡ወልቃይትም እንዲሁ ወደ ትግራይ ቢካለል ነውር ያለው አይመስለኝም፡፡
‹‹Lasta is also classed with Tigre. This province which has also given its name to the kingdom, of which it now forms part, is bounded on the west by the Tchera-Agous, on the north by the Ejjon-Gall, on the south-east by Angot, and on the north by Bora and Ouofila›› (Routes in Abyssinia, page 187). [7]
ዘ-አዲስ ጎጃምን የአማራ ግዛት ነበር ቢልም ፀሐፊው ዋቢ ያደረገው መፅሐፍ ግን ጎጃም የአማራ እንዳልነበር ነው የሚናገረው፡፡
‹‹Amhara, properly so called, extends between the Rivers Ouahet and Bachelot, it is bounded on the west by the Nile, which separates it from Gojam, and on the east by Lasta and Ingot›› (Routes in Abyssinia, page 189). [8]
ናይል(አባይ) አማራና ጎጃምን የሚዋሰኑበት ወንዝ ከሆነ አማራና ጎጃም አንድ አይደሉም ማለት ነው፡፡ በተጨማሪም ይኸው መፅሐፍ ወሎም አማራ እንዳልነበር ይናገራል (በገፅ 17፣103፣139-144፣174)፡፡
ዞሮ ዞሮ ግን ሚዛናዊነቱ አጠያያቂ ከሆነው ታሪክ ይልቅ በአሁኑ ሰዓት መሬት ላይ ያለው እውነታ ሚዛን ይደፋል፡፡ ህዝብን ለመሳደብ የሚዳዳቸው ሰዎች ‹‹ትግሬ እንጂ ትግራይ ተከዘ ተሻግሮ አያውቅም›› የሚሉት መፈክር በአሁኑ ሰዓት ያለው የአለማችን ሁኔታ ያላገናዘበ ስሜታዊነት ነው፡፡ የስደተኞች ሃገር እየተባለች የምትጠራው አሜሪካ የቀይ ህንዳውያን ስለነበረች የአሁኖቹ አፍሪካውያን፣ አውሮፓውያንና ኤዥውያን ሊኖሩባት አይገባም ማለት ጅልነት ነው፡፡ አውስትራልያም ቢሆን በአብዛኛው በአውሮፓውያን የተያዘች ነች…ለአቦርጅኖች ሲባል ግን እነዚህ አውሮፓውያን መኖር የለባቸውም ማለት አይቻልም፡፡ ወይም አቦርጅኖች እንጂ አውሮፓውያን መሆን አይችሉም ማለት አንችልም፡፡
3/ ‹‹ወልቃይት እንኳን ህዝቡ መሬቱም ትግርኛ ተናጋሪ ነው፡፡››
ሀ. የወልቃይት ህዝብ ትግርኛ ተናጋሪ ነው – ትግራዋይ ነው፡፡
ይህን ያሉት የታሪክ ተመራማሪና ፀሐፊው መምህር ገበረኪዳን ደስታ ናቸው፡፡[9] የወልቃይት ህዝብ ትግርኛ ተናጋሪ ነው፡፡ ይህ ብቻ ግን አይደለም፤መሬቱ የሚናገረው ትግርኛ ነው፡፡
ጎንደር በነበረው ዓመፅ ‹‹ትግሬ እንጂ ትግራይ ተከዜን ተሻግሮ አያውቅም›› የሚል መፈክር ሲስተጋባ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ይህ ግን መሰረት የለውም፡፡ ስድብ ሌላ እውነታው ሌላ ነው፡፡
የሚከተለው ሰንጠረዥ እንደሚያመለክተው የወልቃይት፣ ፀለምቲና ፀገደ ህዝብ ትግርኛ ተናጋሪ ነው…ትግራዋይ ነው፡፡ የህዝቡ ቋንቋ ብቻም ሳይሆን ባህሉና አኗኗሩም ትግራዋይ ነው፡፡ ለዛም ነበር ወደ ትግራይ የተካለለው፡፡
እውነተኛ የህዝብ ጥያቄ ከሆነ ጥያቄው መቅረብ የነበረበት ለመንግስት እንጂ ለትግራይ ህዝብ መሆን አልነበረበትም፡፡ አሁን ግን የትግራይ ህዝብ ተጠይቆ መልስ አልሰጥም እንዳለ ተቆጥሮ ማንኛውም የትግራይ ተወላጅ ከአማራ ክልል እንዲወጣ ጥብቅ ትእዛዝ ተሰጥቶታል፡፡

የወልቃይት ተወላጁ አቶ መኮንን ዘለለውም ከኤስ.ቢ.ኤስ ሬድዮ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ የሚከተለው ምስክርነታቸውን ሰጥቷል፡፡ ‹‹መጀመርያ ማን ነበረ የሚለው ጥያቄ መልሱ ትግርኛ ነው፡፡ ወልቃይት ከመጀመሪያው ጀምሮ ትግሪኛ ተናጋሪ ነው፤ ወደ ወልቃይት የመጣው አማርኛ እንጂ ትግሪኛ አይደለም።አማርኛ የመጣው ደሞ በፖሊስ፣ በበለጠ ደሞ አዝማሪዎች መጥተው ነው ያስፋፉት፡፡››[10]
ለ. የወልቃይት መሬት ትግርኛ ተናጋሪ ነው፡፡
በወልቃይት ወረዳ የሚገኙ ጣብያዎች ስም ትግርኛ ነው፡፡ ትግርኛ የሚናገረው ህዝብስ ከትግራይ የፈለሰ ነው እንበል፣ የአከባቢው ስሞችስ ከየት መጡ? አከባቢውም ከትግራይ ፈልሷል ማለት ነው? የሄ ፈፅሞ ሊሆን የማይችል ነገር ነው፡፡ ህዝቡም ከባቢውም ትግራዋይ መሆኑን በግልፅ ትግርኛ እየመሰከረ ነው፡፡ህዝቡ እኛ ማንነታችንን እናውቃለን…ማንም እንዲነግረን አንፈልግም እያለ ነው፡፡ መሬቱም እንዲሁ ማይ ልሐም፣ማይ ፀብሪ፣ ማይ ጋባ፣ ማይ ሑመር፣ ማይ ጨዓ፣ ማይ ጥምቀት፣ ቓቓ፣ ዓዲ አርቃይ፣ ወዘተ. እባላለሁ እያለ ነው፡፡ ይህ ትግራዋይ ካልተባለ ሌላ ሊባል አይችልም፡፡

የሚከተለው ካርታ ደሞ 1971 ዓ.ም የነበረው የህዝብ አሰፋፈር ያመለክታል፡፡ ካርታው የተገኘው ከሆርን አፌርስ ድረ ገፅ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡

4/ የወልቃይት ጥያቄ መነሳት ያለበት የት ነው?
የኮንሶ ህዝብ በደቡብ ክልል ነው የሚገኘው፤የልዩ ዞን አስተዳደር ይገባኛል ጥያቄ ያነሳውም በደቡብ ክልል ውስጥ ነው፡፡የቅማንት ህዝብ በአማራ ክልል ይገኛል፤ የልዩ ዞን አስተዳደር ይገባኛል ጥያቄ ያነሳውም በአማራ ክልል ነው፡፡ጥያቄው የተፈታውም በዛው…በአማራ ክልል ነው፡፡
የወልቃይት ህዝብ የሚገኘው በትግራይ ክልል ነው፤ የማንነት ጥያቄ እያነሱ ያሉት ሰዎች ግን ጎንደር ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ጎንደሬዎች የልቃይት ጥያቄን እንደ ሰበብ ተጠቅመው በትግራይ ተወላጆች ላይ የንብረት፣ የአካልና የሕይወት ማጥፋት ጥቃት ፈፅሟል፡፡ጎንደር ወስጥ ሰባት የትግራይ ተወላጆች እንደተገደሉ አልጀዚራ ዘግቧል፡፡ ቤት ለቤት እየዞሩም ‹‹እስከዚህ ቀንና ሰዓት ጎንደርን ለቃችሁ ካልወጣችሁ እንደነ እንትና በላያችሁ ላይ ጋዝ አርከፍክፈን ነው በእሳት የምናጋያችሁ›› እያሉ ሽብርና ጣራ የነካው መርዘኛ ጥላቻቸውን ሲረጩ ከርሟል፡፡[11]
አቶ ውብሸት ሙላት የሕገ መንግሥት ኤክስፐርትና ‹‹አንቀጽ 39›› የተሰኘ መፅሐፍ ደራሲ ናቸው፡፡ አቶ ውብሸት ወልቃይትን አስመልክተው የሚከተለውን ብሏል፡፡
‹‹የወልቃይት ጥያቄ የተፈጠረው በአማራ ክልል አይደለም፡፡ የወልቃይት ሕዝቦች የአማራ የማንነት ጥያቄ የተነሳው በትግራይ ክልል ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ አሁን ባለው ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ጥያቄው ሊፈታ የሚችለው በትግራይ ክልልና በፌዴራል መንግሥቱ ነው፡፡›› [12]
ሆኖም ግን የጎንደር ሽማግሌዎች ናቸው አስታራቂ መስለው ጥያቄውን ያቀጣጠሉት፡፡ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ጎንደር ውስጥ ከሽማግሌዎች(ሽማግሌ ከተባሉ) ጋር በተደረገው ስብሰባ ‹‹የወልቃይት ህዝብ የወልቃይት ብቻ ሳይሆን የመላው አማራ እንዲሆን ነው የምንፈልገው›› ብሎ ሲናገር ተሰብሳቢዎቹ በጭብጨባ ቢቱን ሲያደምቁት አይተናል፡፡ እኛ አማራ እንጂ ትግሬ አይደለንም የሚለው አዋጅ ያሰሙት በመቐለ ከተማ ሳይሆን በአማራ ክልል ውስጥ በጎንደር ከተማ ነው፡፡ሽማግሌዎቹ ‹‹አማራ ነን ብሎ ለመጣ እንቀበላለን›› ነበር ያሉት፡፡ ሲያጠቃልሉም የአማራነት ጥያቄ መቀጠል አለበት በማለት በሚል ነበር፡፡ ጠንክሩ እኛም ከእናንተው ጋር ነን፤ በጉልበት፣ በገንዘብ እናግዛችኋለን ብለዋቸዋል፡፡ እናም ጥያቄው የጎንደር፣ ብሎም የመላው አማራ ጥያቄ መሆኑን ታወጀ፡፡[13]
ይህ አካሄድ ራሽያ የዩክሬን ግዛት የነበረችው ክርሚያን ወደ ራሽያ ግዛት ለመጠቅለል የተጠቀመቸው ስልት ነው፡፡ይህ ስልት እየተጠቀሙ ያሉትም ጎንደሬዎችና የብአዴን አመራሮች መሆናቸው ግልፅ ነው፡፡የአማራ ክልል ልክ እንደ ሻዕብያ ትግራይን ለመውጋት ታጥቀው የተነሱ ሰዎችን ጥገኝነት እየሰጠ ነው፡፡እነ ኮሎኔል ደመቀም የልብ ልብ ስለሰጣቸው ወደ አመፅ አመሩ፡፡አመፁም የትግራይ ተወላጆችን የንብረት ውድመት፣ የአካል ጉዳት እንዲሁም ሰባት ሰዎች እንደተገደሉ እነአልጀዚራ ዘግቧል፡፡በተጨማሪም፣ የትግራይ ተወላጆች ከአማራ ክልል ጠቅልለው እንዲወጡ የግዜ ገደብ መስጠት ሆነ፡፡
5/ ማጠቃለያ
ወልቃይት፣ ህዝቡም ሆነ መሬቱ ትግርኛ ተናጋሪ መሆኑን መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡ይህ እውነታ የሆነ ፈረንጅ እንዲህ ብሎ ነበር፣ መፅሐፍ እንዲህ ይላል፣ እንዲሁም ህዝብን የሚያንቋሽሹ መፈክሮችን በማሰማት የሚቀየር ነገር አይደለም፡፡ይኼ ‹‹ቢበርም ጅብ ነው›› ዓይነቱ ክርክር ለሁላችንም የማይበጅ የጌቶች ትእዛዝ ስለሆነ ከወዲሁ ቢታረም የተሻለ ይመስለኛል፡፡ጎንደር ውስጥ ከሽማግሌዎች ጋር በተካሄደው ስብሰባ እንደ ተስማሙበት ጥያቄው መጀመርያ የጎንደር እንዲሆን ተስማሙ፤ የጎንድር ጥያቄ ደሞ የአማራ እንደሆነ ተስማምተው ነበር የተለያዩት፡፡የህም ጥያቄው የወልቃይት ሳይሆን የአማራ መሆኑን በግልፅ ተመልክተናል፡፡ሽማግሌዎቹም፣ በእነ ኮሎኔል ደመቀ የሚመራው ቡድንን ተበድላችኋል፣ ተጨቁናችኋል…ከጭቆናው ነፃ እናወጣችኋለን የሚል ሙሉ ድጋፍ ሰጥተዋቸዋል፡፡
References
[1] Ghelawdewos Araia. Beyond Ethnocentric Ideology and Paradigm Shift for a Greater Ethiopian Unity, April 20, 2016
[2] Ibid
[3] Ibid
[4] Henry Salt. (1816). A Voyage to Abyssinia: And Travels into the Interior of that Country page 378 and 381
[5] Ibid
[6] ወልቃይት ላለፉት ሺህ ዓመታት በትግራይ ስር ተዳድራ አታውቅም – የታሪክ ማስረጃዎች፣ ሆርን አፌርስ፣ June 8, 2016.
[7] Routes in Abyssinia (printed in 1867 G.C):
[8] Ibid
[9] Memhir Gebrekidan Desta interview on Welkait-Tsegede, March 6, 2016.
[10] Interview with Mekonnon Zelelow – SBS Amharic, April 22, 2016.
[11] Ethiopia: Ethnic Tigrayans flee to avoid anti-government protesters, Al Jazeera English, , August 21, 2016.
[12] የተቃውሞ ሠልፎቹ ዘርፈ ብዙ ሥጋቶች፡ Ethiopian Reporter.
[13] Colonel Demeke Zewdu Addressing Welkait Committee Public Meeting in Gondar: , August 20, 2016.
*********
whoever write and said what s/he wishes, not only wolkayt but also, shire-endasilassie and the whole Tigray all belong to the Amhara. the Tigrians are migrant. How on earth, they demand a land on Ethiopia. They are writing about Sekota and Korem, Raya, they have never been part the so called Tigrians. Amhara respect human beings, and recognize the Tigrians and gave them the land to settle. But after so many years, they claim the whole Ethiopia.
I’m not From that area, but from what I observed and understood, the people in Gondar did not take to the streets until unidentified forces, allegedly from the Tigray region came to their town to forcefully abduct public figures who sympathize with the Amhara ethnic in wolkait, and their cause. Gondar is not asking for the land(Wikait) to be annexed back to it’s former province, they are merely asking Justice for their compatriots as every other Ethiopian should have. this has nothing to do with the land, the people’s voice should not be suppressed by force or any other way .. the case should run it’s constitutionally stated course … and if the land and the people belong to Tigray so be it , the Tigray regional government will resume it’s responsibility over administration of the land … other wise, if it deserves to re incorporated with the Amhara region , the Amhara regional government will take over administration of the land, the land will stay the same, the people will stay the way they are, nothing will actually change… In my opinion what made the issue complicated than it needs to be is the ethnic rivalry among individuals who impose their misguided ideologies and hatred upon the poor farmers and laborers who couldn’t care less about who’s what , but need an outlet for their grievances caused by unrelated issues poverty being one of them …
Voting to whom ? to those 500.000 tigrians placed on wekait fertile lands ? Where 1.000.000 welkait peoples were chased and killed ? Stop writting new child-play stories . Go back behind tekeze river … Ethiopia can hold even one of us !
This is a new story written by Woyane clans as your immaginary Manifesto. Please, stop this stupidity if you want to live peacefully. Wolkayit is AMARA and those who beleive to be Ethiopians can live in. The rest is only your mimic political circus.
አቶ ገብሩ አሥራት
“እኔ ትግራይን ሳስተዳድር ነበር፡፡ ..ወልቃይት የተከለለው በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት መሠረት ነው፡፡ የፌዴራል አከላለል ቋንቋ፣ ባህል፣ አሰፋፈር የመሳሰሉትን መሠረት አድርጎ ነው፡፡ በዚህ መሠረት የወልቃይት ሕዝብ ትግርኛ ይናገራል፡፡ የፀገዴም ሕዝብ ግማሹ ትግርኛ ይናገራል፡፡ ትግርኛ ተናጋሪው ፀገዴ ወደ ትግራይ ተካሏል፡፡ አማርኛ ተናጋሪው (ጠገዴ) ደግሞ ወደ አማራ ክልል ተካሏል፡፡ ከትግራይም አገውኛ የሚናገር ወደ አማራ ክልል ተካሏል፡፡ አፋርኛ የሚናገሩ አምስት ወረዳዎችም ወደ አፋር እንዲሄዱ ተደርጓል፡፡ መነሻውን ማየት አለብን፡፡ መነሻው የሀብት ወይም የመሬት ዝርፊያ አይደለም፡፡ ይኼን ላረጋግጥ እወዳለሁ፡፡ የመሬት ዝርፊያ ቢሆን ኖሮ፣ የሀብት ቢሆን ኖሮ የጨው ማዕድን፣ የፖታሽ ማዕድንና ሌሎች ውድ ማዕድናት ያሉበት የአፋር ክልል ይበልጣል፡፡ ከሁመራ አካባቢ ይልቅ ማለት ነው፡፡ ግን አፋር ተናጋሪ አፋር ነው ተብሎ ወደ አፋር ተካለለ፣ ወልቃይት ደግሞ ትግርኛ ይናገራል ተብሎ ወደ ትግራይ ተካለለ፡፡ ስለዚህ በዚህ የአከላለል ሥልት ድሮ የነበረው ተለውጧል፡፡ ይኼ አከላለል በትግራይ ብቻ አይደለም፡፡ ኦሮሚያ ድሮ የሸዋ ክፍለ ሀገር፣ ባሌ፣ ሐረርጌ የሚባሉትን ጨምሮ ነው የተካለለው፡፡ አፋርም የተካለለው ከወሎና ከትግራይ ተውጣጥቶ ነው፡፡ እንደ ጥያቄ መቅረብ ያለበት መካለል በዚሀ መሆን አለበት ወይ? የሚለው ነው፡፡ መካለል ያለበት በብሔረሰቦች ወይ በማንነት መሆን አለበት ወይ የሚል መሆን አለበት? ወይስ በሌላ? የሚለው ጉዳይ አነጋጋሪ ሊሆን ይችላል፡፡ ወልቃይትም ሌላውም በዚህ መሠረት ነው የተካለለው፡፡ ጥያቄው ከተነሳ በትግራይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ክልሎችም መነሳት አለበት፡፡ ” (ሪፖርተር)
First of all there is no region called Gondar now. There is only Amhara region. Gondar used to be a province before the EPRDF took power. Now it is only a town. Next, when the federal arrangement was formed areas from Tigray were taken away to be part of the Amhara region example Sokota and other areas. A big chunk of eastern Tigray was given to the Afar region. Tigrigna speakers from Wolkayt, Tsegede and Kafta Humera are made under Kilil Tigray accordingly. This applied to other areas in Ethiopia. This has been very clear for the last 25 years.
Another important point in this regard is if the people of wolkayt say they do not want to be in Tigray, the demonstrations and should take place in Wolkayt itself and not in Gondar. Why is it being taken place in Gondar and its environs? I think this has to be taken very seriously. We may end up becoming tools to Ethiopia’s mortal enemies. This should’nt have become a reason to attack tigreans and destroy their property. Look at what dangerous precedence this could have. Make the Amaras leave Oromia and other Ethiopian towns (we know how things go in this country) and so on God forbid! The Tigray and The people of Gondar are almost alike in many things. I am afraid for Ethiopia.
Last point is the people (politicians) doing this work are not smart enough. A smart politician can only isolate a party (TPLF in this regard) and not the entire proud people of Tigray. There are Tigreans who are not in good terms with the party, there are a great majority of Tigreans who suffer from the maladminstration in Tigray and others who do not care and believe they are Ethiopians and can leave anywhere in Ethiopia. What will this attack on Tigreans by their ethnicity brew? I don’t know.
People who take care of this business and the people of Ethiopia should take this very seriously before it is too late. Thank you
የኮምሶን ሁኔታ ከቅማንት ጋር እንጂ ከወልቃይት ጋር ማመሳሱልህ ስህተት ነዉ::ምክንያቱም ኮምሶም ሆነ ቅማንት ወደ ሌላ ክልል የመካለል ጥያቄ ሳይሆን ባሉበት ክልል የበለጠ ስታተስ የመፈለግ ጉዳይ ነዉ::ወልቃይት ግን ሁለት ክልሎች ያነካካ ስለሆነ ከሁለቱ ለየት ይላል::የክሬሚያን ነገር ማምጣትህ ትልቅ ስህተት ነዉ::ክሬሚያ ሊመሳሰል የሚችለዉ በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል ካለዉ ጋር ነዉ::የኛ ሁኔታ ግን ከሌላ አገር የይገባኛል ጥያቄ የተነሳበት አይደለም::ችግሩ ለምን እንደተወሳሰበ ገብቶሂል?ምክንያቱም እንደእኔና አንተ ባልገባን ጉዱይ ላይ ህዝቡን ስላወናበድነዉ ነዉ::በኛ ተንኮል ወይም የአመራር ብቃት ማነስ መነሾ የትግራይ ህዝብና አማራዉ ወንድሙ ሲገዳደሉ እያየን ከማብረድ ይልቅ ጭራሽ ዱላ እያቀበልን ነዉ::ስለዚህ የበለጠ ህዝብን ከሚያስቆጣና እንዱን ለይቶ ከመወገን እንቆጠብ::ህዝብን እንደህዝብ መዝለፍም ደግ እይደለም::አስታራቂ እንጂ የሚያጣላማ መች ጠፋ ብለህ ነዉ:: መንግስትአገር ለማዳን ፍዳዉን እያዬ እኛ ልናግዘዉ ሲገባን ጭራሽ እናጋግላለን::እንዳንዶቻችን የሀገሪቱ መፃኢ እድል ጭራሽ ያሳሰበን አይመስልም::እንዲያዉም የራሷ ጉዳይ ያልን ነዉ የሚመስለዉ::ፈጣሪ አገራችንን ይታደጋት እኛማ ራስ ወዳድ ሆነናል::ይቅርታ ካስከፋሁህ !
Wolk የነዚህ የትግሬዎች ነገር የሚገርም ነው። ወልቃይትን በሚመለከት የጻፉትን ማለቴ ነው። መጀመሪያ ተልቅ ተልቅ ያሉ ትግሬውች ወልቃይትን በሚመለከት ታሪክን አጣመው የትግሬ ነው የሚል የተጣመምና በውሸት የተሞላ ታሪክ ከጥቂት ቅመታት በፊት ጻፉ። አንሁ ደግሞ ትንንሽ ትግሬዎች ከሶስት አራት አመት ወዲህ ትልልቅ ትግሬዎች የጻፉትን የውሸት ታሪክ እንደ ማጣቀሻ እየጻፉ ነው። እውነተኛ ታሪክ እማ ከየት ይምጣ ታድያም? ቅቅቅ
Is Ethiopia Really Non-Colonized? I believe in the unity of Ethiopian peoples in blood & culture! But, let me say ‘make no mistake!’ All the European mumbojumbo texts you quoted are make-believe fictions vomited in 20th century. Critical scholars have adequately explained away that there was no any Portuguese in Ethiopia be it 16th c or before or after. Even there was no any Classical Greek text before 1840s or if earlier by 1785. These are faked up after 1868 by England monks & mercenary French & German & Italian intelligentsia. The so-called “ A New History of Ethiopia” by character called “ Ludolf” in “1682” is utter ridiculous! ( See a Portuguese critical researcher Andreu Martinez d’Alos-Moner (200). Colonialism and Memory: The Portuguese and Jesuit Activities in Ethiopia through the Colonial-looking Glass). So, colonial era mumbojumbo is successful in dividing, weakening & fighting us one against the other. What’s being ‘colonized’ if not this?
Kemisse,Bati, Robit, Dessie, Wereilu, Werehimanu, Borana, Woldia, Gubalafto, Raya, Ashabo, Werebabo, Werebacho.Legambo, Legahida, Kombolcha, Wallo, Arabati, Chaffa, Borkana, Harbu, Dawey, Mersa, Barentu(Eritrea) –isn’t this very interesting? What do these names tell us? History is so intriguing. It is challenging as well–between past and present. Should we respect it and know our interesting past or reject it and and live in a dilemma and prejudice? The present is of course the most important with regards to demographic issues.
Leave the welkait people to vote referendum
አቶ wolk አንተው ራስክ ከምትሳደብ አለኝ የምትለውን እውቀት እና ታሪክ አቅርበህ አትወያይም? ስድብ ደካማነትህን ዝና ጭፍንነትህን ያሳብቅብሃል
For me as old soldier it is painful to hear when brothers are attcking each other.Regarding the current crisis,i think the residents of wolkait should be given a chance to exercise their constitutional rights to decide freely their destiny w/o any interference from either tigray or amhara region.if they think they can benefit from being tigray let they decide.i think our federal system should have adequate answer for such disputes on identity.If the system is incapable to resolve this problem in appropriate way it may raise a question whether we can proceed further or not when a dozens of woredas all over the country are demanding the same quastion.in order to preserve our beloved country from disintegration there is no other solution than taking strict measures. God bless ethiopia!
Sijemere mereja ende kumita Yaterh sw neh!siketel tiraze netek selehonk enji mnm aynet yteberara ena yereba neger alasekemetkm!selesemeth gobez neh kezih wuchi gin bizu anbebe tyek….Astaraki hasab endemametat chirash….!!!
አሪፍ Article ነው። በተለይ የወልቃይት መሬት ትግርኛ ተናጋሪ ነው በጣም ተመችቶኛል፡ አውቆ ለሚዋሹና ፈጣጣ ሌብነት ያሉትን ምን ማድረግ ይቻላል?
https://youtu.be/U8ebZRsPHxo
ሲነሳ ስለምታውቁት ልብ ግዙ! የጀግና የሆነው የትግራይትም ሆነ የወልቃይት ሕዝብ ታጋሽነት አትናቁት ሸሽታቹህ በምድረ አሜሪካ የተሸገሸጋቹሁት ከአሁን በፊት ክንዱን ስለምታውቁት አይደለም አትርሱት እንላለን!
https://youtu.be/0MccKMVACOs
እነዚህ ሰዎች በስድብ ብቻ ነው የተመረቁት?… ያም ሆነ ይህ አቶ Wolk የውልቃይት ጉዳይ የወልቃይት ሕዝብ ጉዳይ ነው የማንም አይደለም የወልቃይት ሕዝብ ደግሞ በራሱ ምርጫ በቃንቃው በባህሉ መሰረት እየኖረ ነው። ጠማማ አእምሮ ለማሳመን ጊዜ ማጥፋት ከንቱ ነገር በምድር ላይ የለም። https://youtu.be/a88qUa6wsP4
XX
ጅል። ሰው ጥራ ቢሉት እራሱ መጣ አሉ። ትንሽ ጊዜ ወስደህ፡ አጥንተህ፡ የታሪክ መፅሓፍትን አጣቅሰህ ብትመጣ ኑሮ፡ ቢያንስ ፅሁፍህ መወያያ ይሆን ነበር። እዚሁ ድረ ገፅ ላይ የተለቀቁ ሁለት ፅሁፎችንና ቅዠትህን ጨምረህ፡ ታሪክ ብለህ ይዘህ መምጣትህ፡ አሣፋሪነው። ከመጠምጠም፤ መማር ይቅደም የተባለው ላንተና ለመሠሎችህ፤ ነው። እግዜር ልብ ከሠጠህ፤ የ ጠባብ ብሄርተኛ መነፅርህን አውልቀህ፤ በእውነት መነፅር ታሪክ አጥንተህ፡ መዎያያ የሚሆን በሣል ፅሁፍ ይዘህ እንደምትመጣ፤ ተስፋ አደርጋለሁ።