ዛሬ በጎንደር ከተማ ስለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ዓላማ፣ ግብ፣ መልዕክቶች፣…ወዘተ ስለመሳሰሉት ጉዳዮች በማህበራዊ ድረገፆችና በዲያስፖራው ሚዲያዊች በሰፊው እንደሚዘገብ እገምታለሁ። በእነዚህ ጉዳዩዮች ዙሪያ በቂ መረጃ ይቀርባል። ስለዚህ፣ የእኔ ትኩረት “ከዛሬው ሰላማዊ ሰልፍ ምን እንማራለን?” በሚለው ነጥብ ላይ ነው። በተለይ ደግሞ የክልልና የፌዴራል መንግስታት ምን መማር አለባቸው የሚለውን እንመለከታለን።
የአማራ ክልላዊ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ትላንት በሰጠው መግለጫ “በጎንደርም ሆነ በሌሎች ከተሞች የተጠየቀም የተፈቀደም ሰላማዊ ሰልፍ የለም” ብሎ የነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ “በጎንደር ከተማ የተካሄደው ሰለማዊ ሰልፍ ምንም እንኳን በመንግስት የተፈቀደ ባሆንም ሰላማዊ ነበር…” እያለ ይገኛል።
በእርግጥ ይህ የብአዴን/ኢህአዴግ መግለጫ እናቴን ነበር ያስታወሰኝ። ልጅ እያለሁ፣ በተለይ ደግሞ ከእናቴ አጠገብ ስሆን ፈርዶብኝ የሆነ ነገር አጠፋለሁ፡፡ ታዲያ ይቺ እናቴ “እስኪ ትንፍሽ በል…ዋ! ዝም…ዝም በል…” እየለች ነበር የምተገርፈኝ፡፡ መግረፏ ሳያንሰኝ “ዝም በል” ማለቷ የባሰ ያስጨንቀኝ ነበር፡፡ ዝም እንዳልል ምቷ ሰለሚያመኝ አለቅሳለሁ … ሳለቅስ ደግሞ “ዝም በል” ብላ ከዱላው ትጨምርልኛለች፡፡ መጨረሻ ላይ ሲመረኝ ብንን ብዬ ከአጠገቧ በሩጫ አመልጣለሁ፡፡ ዛሬ የጎንደር ህዝብ ልክ እንደ እኔ በምሬት ሮጦ ወደ አደባባይ የወጣ ይመስለኛል፡፡
በተለምዶ “ሰው ፖለቲካዊ እንስሳ ነው” ይባላል። ይህ አባባል ለምን እንደሚባል አይገባኝም ነበር። ትርጉሙ የገባኝ “Aristotle” የተባለው የግሪክ ፈላስፋ “Politics” በሚለው መፅሃፉ ስለዚህ አባባል የሰጠውን ትንታኔ ካነበብኩ በኋላ ነው። እንደሱ አገላለፅ፣ ሰው ከሌሎች እንስሳት በተለየ ሕመም እና ደስታን (Pain and Pleasure) በቋንቋ መግለፅ ይችላል፡፡ የቋንቋ ችሎታውን በመጠቀም መከፋቱንና ደስታውን፣ ድጋፍና እና አቤቱታውን በቀጥታ በንግግር፣ በፅሁፍ ወይም በሰልፍ መግለፅ ይችላል።
በመሆኑም፣ እያንዳንዱ ግለሰብ በግል እና በቡድን የሚያደርገው ማህበራዊ ግንኙነት በዚህ ተፈጥሯዊ ባህሪ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በመጥቀስ፣ “ሰው ፖለቲካዊ እንስሳ ነው!” (Man is a political animal) ይላል “Aristotle”። አባባሉ “ሰው ፖለቲካዊ እንስሳ ነው” ሲባል በአንድ ነገር ላይ የተሰማውን ጥሩም ይሁን መጥፎ ስሜት በግል ወይም በቡድን በቃል ንግግር፣ በወረቀት ፅሁፍ ወይም እንደ ዛሬው በአደባባይ ሰልፍ የመግለፅ ተፈጥሯዊ ባህሪ እንዳለው ያሳያል።
በአጠቃላይ፣ ሰው በአንድ ነገር ላይ የተለያየ አመለካከት መያዙና ሃሳቡን መግለፁ ተፈጥሯዊ መለያ ባህሪው ነው። ለዚህ ነው ዓለም-አቀፍ ድንጋጌዎችም ሆኑ ሀገር-አቀፍ ሕጎች ሰው ያለማንም ጣልቃ-ገብነት የመሰለውን አመለካከት መያዝና ሃሳቡን የመግለፅ ነፃነት እንዳለው የሚደነግጉት። ምክንያቱም፣ ይህ የሰው-ልጅ ተፈጥሯዊ ባህሪ እንጂ በሌላ አካል ፍቃድና ይሁንታ የሚሰጥ አይደለም።
የኢፊዴሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 30 ለዚህ ጥሩ ማሣያ ነው።
“ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን ማሣሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነፃነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው። ከቤት ውጪ የሚደረጉ ስብሰባዎችና ሰላማዊ ሰልፎች በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች በሕዝብ እንቅስቃሴ ላይ ችግር እንዳይፈጥሩ ለማድረግ…አግባብ ያላቸው ስርዓቶች ሊደነገጉ ይችላሉ።”
ከላይ በጥቅሱ ውስጥ እንደተጠቀሰው፣ በሕዝብ እንቅስቃሴ ላይ ችግር እንዳይፈጠር በሚል የሚወጣ ማንኛውም ዓይነት ስርዓት ከሕገ-መንግስቱ መሰረታዊ መርህ ጋር የሚጋጭ መሆን የለበትም። ሰላማዊ ሰልፉ በሚካሄድበት ቦታ የሚመለከተውን የመንግስት አካል ከማሳወቅ በስተቀር ሌላ ፍቃድ መጠየቅም ሆነ መጠበቅ የለበትም። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የሚካሄድበትን ቦታና ግዜን ከማሳወቅ ሌላ ፍቃድ የሚጠይቅ አሰራር ሊኖርም አይችልም። እንዲህ ያለ አሰራር ቢኖርም እንኳን ሕገ-መንግስቱን የሚጥስ ስለሆነ በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት የለውም።
ከዚህ አንፃር፣ የአማራ ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት በጎንደር ከተማ ለሚደረገው ሰለማዊ ሰልፍ “ፍቃድ አልሰጠሁም” ሲል ያወጣው መግለጫ በራሱ በቂ ማስረጃ ነው። ምክንያቱም፣ በሕገ-መንግስቱ መሰረት በሰላማዊ ሰልፍ ተቃውሞና አቤቱታን ለመግለፅ የሚጠበቀው ማሳወቅ ብቻ ነው። የክልሉ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ፅ/ቤት “በጎንደር ከተማ ነገ ለሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ፍቃድ አልሰጠሁም” በማለት የሰጠው መግለጫ በራሱ ሰላማዊ ሰልፉ እንዲካሄድ ከመፍቀድ ጋር እኩልና አንድ ነው። በመሰረቱ ከሕዝቡ የሚጠበቀው ማሰወቅ ብቻ ስለሆነ የፅ/ቤቱ መግለጫ የክልሉ መንግስት ማወቅ ያለበትን አውቋል ማለት ነው። በአጠቃላይ፣ “ሰላማዊ ሰልፍ እንዲካሄድ አልፈቀድኩም” ማለት በራሱ “ፈቅጄያለሁ” እንደማለት ነው።
መንግስት ማለት የጋራ ሰላምና ደህንነታችንን እንዲያስከብርልን በሚል ውክልና የተሰጠው አካል ነው። በውላችን (ሕገ-መንግስት) መሰረት ራስን-በራስ የማስተዳደር ስልጣናችንን እና የሀብታችንን አሳልፈን ሰጠነው። ሕዝብ የሰጠውን ስልጣንና አቅም ተጠቅሞ የብዙሃኑን መብትና ጥቅም ከማረጋገጥ ይልቅ የህዘቡን መብት ወደጎን ትቶ የራሱን ጥቅም አስቀደመ።
በህዝብ ፍቃድ ላይ የተመሰረተ መንግስት ያለእሱ ፍቃድ መናገር አትችሉም ሲል፣ ሕዝብ ወካይ፣ መንግስት ተወካይ መሆኑ ቀርቶ ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆነ። መንግስት በተግባር ማስከፋቱ ሳያንስ፣ ህዝብ “ከፍቶኛልና አቤቱታዬን አደባባይ ወጥቼ ላሰማ” ሲል ያለእኔ ፍቃድ አይሆንም ይላል። ሲጀመር ሕዝቡን ያስከፋው እኮ መንግስት ነው፡፡ ያስከፋውን ሕዝብ አቤቱታውን እንዲገልፅ ፈቃጅ መሆን የሚሻውም መንግስት ነው። አንዴት ሕዝብን አስከፍቶ አቤቱታውን አልሰማም ይላል? ታዲያ ሕዝብን አስከፍቶም-ገፍቶም ይቻላል እንዴ?
በእርግጥ ዛሬ በጎንደር ከተማ የታየው ሰላማዊ ሰልፍ “ሕዝብን አስከፍቶም፣ ገፍቶም” መቀጠል እንደማይቻል ነው። በመጀመሪያ፣ የሚገፋውን አካል ገፍትሮ በመውጣት መከፋቱንና ብሶቱን ይገልፃል። በቀጣይ ሲመጣ ግን አስከፍቶ የሚገፋውን መንግስት ገፍትሮ ይጥለዋል። በኃላ ላይ ከመገፍተር አሁን መማር የሚበጅ ይመስለኛል።
******
Aye Gondere eyadere THREE honeko, minus temezebere endemanim deha Ethiopiawi yeminor enji min alew, mins neberew yaw Tarik eyamenejeke yienor neber yaw,yene Atse Tedros yejegininet tarikim behon yaw yeza Ethiopian betariqua tsenta endetinor yaschalat hizib yekoratu yee Tigrayu new, Tarikachihu keyet endemetachihu enquan sataku mejenen yaw lemad ayker honena bebado medaa kurat mejenen yikir, zeregnoch timkihtegnochu maferiawochu betarik wudaki atihunu
TPLF-EPRDF mingizem kurat new.Bezih tarikawi wekit ena yee Ethiopia edget alemesatef berasu wudket new
Well, you can have your say.. But this site is neither Melaku Tefera’s nor EPRDF’s website … your comment and suggestion would be helpful if it focus on the subject of the article.
ከመላኩ ተፈራና መሰሎቹ ጭቆና ለመላቀቅ መላው የጎንደር ህዝብ መሪር መሰዋትነት ከፍሏል፡፡ደርግን መጣልም ከዚህ ሰፊ ህዝብ ተጋድሎ ውጭ የማይቻል ነበር ይህን ሀቅ እናንተ ኢህአዲጎችም አትክዱትም፡፡ስልጣን ያስጨበጣችሁትን ህዝብ ሌላ መላኩ ተፈራ/ደርግ ሆናችሁበት፡፡ 25 ዓመት ሙሉ በብአዴን ተላላኪነት ጨቆናችሁ፤መዘበራችሁ፤ማንነት አሳጣችሁ ታገሳችሁ አሁንስ ግፍ በዛብኝ ብሎ አደባባይ ሲወጣ ደግሞ ወገኑን ለመግደል ጀግና በሆነው ልዪ ሀይላችሁ አስገደላችሁት ታዲያ ህዝብ ምን ይሁንላችሁ…………..ከመላኩ ተፈራና መሰሎቹ ጭቆና ለመላቀቅ መላው የጎንደር ህዝብ መሪር መሰዋትነት ከፍሏል፡፡ደርግን መጣልም ከዚህ ሰፊ ህዝብ ተጋድሎ ውጭ የማይቻል ነበር ይህን ሀቅ እናንተ ኢህአዲጎችም አትክዱትም፡፡ስልጣን ያስጨበጣችሁትን ህዝብ ሌላ መላኩ ተፈራ/ደርግ ሆናችሁበት፡፡ 25 ዓመት ሙሉ በብአዴን ተላላኪነት ጨቆናችሁ፤መዘበራችሁ፤ማንነት አሳጣችሁ ታገሳችሁ አሁንስ ግፍ በዛብኝ ብሎ አደባባይ ሲወጣ ደግሞ ወገኑን ለመግደል ጀግና በሆነው ልዪ ሀይላችሁ አስገደላችሁት ታዲያ ህዝብ ምን ይሁንላችሁ…………..
Bandirachin behibret chikun beher-behereseboch yatsedekinew new silehonem timkihtegnoch yekebere sendek alamachin min gizem behon lezeregnoch ena letimkihtegnoch yezewetir rasmitat hono yiketilal
Zeregnochu timkihtegnoch bezich ager afrash engi yelimatim yeselam atsewatsio saynorach ew mekeberachewe ejig des yilal lemin yekeseru yewedeku zeroch ena zegoch bemehonachew
Shame all this chauvinistics are barking dogs without teeth. Shame Gonder shame on you Gotegnoch don’t forget that this action will need you to pay big price once you try to superpas the RED line mind you & take care tolerance is not meaning to fear.
You know EPRDF’s stick
Aye Gondere believe on rationalism than being JEBDEGNET
Ke Melaku Tefera mengage netsa yaweta hizib ena mengist endih bewaza eju amed afash yihun, Gondar ewnetun tifred.
Jegninet bebado medda sayhon, kemis wustie tedebiko sayhon ende weyane lijoch bezu waga mekfel yiteyikal. Ye Ethiopia chikun hizboch andenet endih bezeregnoch ena timkihtegnoch chihot ayfersim
Timkihtegnaw diaspora yihin sponsor kemadreg ena yewetatun gizena gulbet kemiyatefa minew Gondar bialemat
Jegina eko yager selam bemastebek limat yemiyameta enji bebodo timkihit limat yemiyadenakif timkihtegnam zeregnam malet aydelem. Aye Gondere???