የኢኮኖሚ ችግር ሲፈጠር ስደተኛዉን ኢላማ ኣድርጎ ጥቃት መሰንዘር በደቡብ ኣፍሪካ ብቻ የታየ ችግር ኣይደለም። ግሪክ፣ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ሩስያ እና በብዙ ኣገሮች የታየ የተለመደ ክስተት ነው። ህንዳውያን በግሪክ ጎዳና ለመንቀሳቀስ ኣዳጋች እየሆነባቸው እንደሆነ ሁሉ ሞስኮም ኣሁን የውጭ ዜጋ እንደልቡ እማይንቀሳቀስባት ከተማ ሁናለች፤ ለምን ቢባል የኢኮኖሚ ችግር።በነዚህ ኣገሮች ከፈተኛ የፀረ ስደተኛ ጥቃትም እሚፈፀምባቸው ኣገሮች እየሆኑ ነው:: ይሄ ነገር ከዘር እና ከጥቁረት እያገናኙ ደቡብ ኣፍሪካውያንን የቀኝ ገዢዎች ንድፈ ሃሳቦች እየተጠቀሙ “ድሮስ ጥቁር….ለነፃነት ኣቅም ያልደረስ እንስሳ” ምናምን እያሉ የትምክህት ቃል መሰንዘር የጉዳዩን ትክክለኛ ገፅታ ኣለመረዳትን ነው እሚያሳየው።
የኢኮኖሚ ችግር ወደ ፖለቲካዊና የፀጥታ ችግር እንደሚቀየር ሳይታለም የተፈታ ሃቅ ነው። በሩዋንዳም በሌሎች ኣገራትም የታየው ይህ ነው። እንዲህ ኣይነት ሁኔታ ለሰነፍ ፖለቲከኞች ጥሩ ኣጋጣሚ ይፍጥራል፤ የሰነፍ ፖለቲካ ደግሞ ቀላል ግን ኣውዳሚ ስለሆነ ዉጤቱ ኣሁን ደቡብ ኣፍሪካ ላይ እያየን ያለነው ኣይነት እልቂት ያስከትላል።ኣንዱን በማስወገድ “መፍትሄ” ለመሻት መጣር ነው የሰነፍ ፖለቲካ ማለት።ለዚህ መዋቅራዊ መደላድል እሚፈጥረው ግን የኢኮኖሚ ችግር ነው። ሁቱዎች ቱትሲዎች ላይ ገጀራቸውን ከማሳረፋቸው በፊት የዋጋ ንረት እና ስራ ኣጥነት ሂወታቸው ላይ ገጀራዉን ኣሳርፎ ነበር። ይህ ቀቢፀ ተስፋነት ሰለፍ ፖለቲከኞች ተመቻቸው እና ዘርን ለማጥፋት ተጠቀሙበት። ደቡብ ኣፍሪካ ላይ እየተፈፀመ ያለ ነገርም ከጄኔቲክ ሳይሆን ከኢኮኖምያዊ ሁኔታ መመሰቃቀል እሚመነጭ ነገር ነው።
የደቡብ ኣፍሪካ ለየት እሚያደርገው የኣፓርታይድ ስርኣት በፖለቲካው ረገድ “ሲገረሰስ” የኢኮኖሚው ሁናቴ በነጮች እንደተያዘ እንዲቀጥል መፈቀዱ ነው። ማንዴላ ከዚ ዉጪ ኣማራጭ ነበረው ወይ? የሚለው መከራከር ይቻላል:: ማንዴላ እሚመራው ፓርቲ ያመጣው ሰላም ዘላቂ የሆነ ስላም ሳይሆን ጦርነት ኣለመኖርን እሚያመላክት ሰላም ነው (Negative Peace እሚባለው) በኢኮኖምያዊ እርምጃ ያልተደገፈ ሰላም የዉሸት ሰላም ነው። ኣቶ መለስ ዜናዊ እንዲህ ኣይነት ሰላም የኪራይ ሰብሳቢዎች ሰላም (Rental Peace) ይለው እንደነበር ኣሌክስ ዲዋል ይናገራል። ትክክልም ይመስለኛል።
ኢትዮጵያዊያን እና ሌሎች ስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ነገር ኢኮኖምያዊ ድቀት፣ ድንቁርና እና ኃላ-ቀርነት ተደማምረው የፈጠሩት ተስፋ መቁረጥ ያስከተለው ኣሳዛኝ ክስተት ነው። ይህን በዜጎቻችን እየደረሰ ያለው ነገር ለድርጅታዊ ፖለቲካዊ ትርፍ ለማዋል መንቀሳቀስ ሌላ ሳይሆን ኢትዮጵያዊ “ፖለቲከኛነትን” ነው እሚያሳየው። ለኔ ትምህርቱ ኣንድ እና ኣንድ ነው፤ የኢኮኖሚ የጀርባ ኣጥንቱ የተወሰኑ ሞላጫዎችን ብቻ ደግፎ የሚንቀሳቀስ ማህበረሰብ ኣወቃቀሩ ለሰላምም ለዴሞክራሲም ጠንቅ መሆኑ ነው። ብዙ ድሃና ድንቆሮ ተይዞ ዘላቂ ሰላም ብሎ ነገር የለም።
እምናየው እና እምንሰማው ነገር በርግጥ ያበግናል፤ ይሁን እንጂ ኣሁንም ዋና ጠላታችን የራሳችን ድህነት ነው።በየቦታው ላለመበተን ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባት ነው ቁልፍ መፍትሄው፤ ኢኮኖሚ ኢኮኖሚ ኣትበሉ መናገርያ ማይክራፎን እና ያራት ኪሎ ወንበር ብቻ ይሰጠን እንጂ ዳቦ ኣያስፈልግም እምትሉ ባለ-ዳቦ እና ባለ-በርገር “ፖለቲከኞች” ኣንድ ማወቅ ያለባቹህ ነገር ቢኖር ያ ደቡብ ኣፍሪካ ያለው ዜጋችን ማይክራፎን እና ያራት ኪሎ ወንበር ሳይሆን ዳቦ ፍለጋ ነው እዛ ድረስ የሄደው። እናም ኣገራችን ማይክራፎንም ዳቦም እንዲኖራት ጠንካራ እና ፍትሃዊ ኢኮኖሚ ያስፈልጋታል።
መዋቅራዊ መፍትሄው ኣገራችንን ማሳደግ ነው። ዘላቂ መፍትሄ ላይ እናተኩር፤ ክስተቶችን እየጠበቁ “የልዩ” ተቆርቛሪነት ካባ በመልበስ ኣርበኛ ለመሆን መሞከር ኣሁንም ሌላ ሳይሆን ኢትዮጵያዊ “ኣክቲቪስት” መሆንን ስለሆነና ይህም እርባና ቢስ ስለሆነ የራሳችን ልማት ለማፋጠን ኣርቀን ብናስብ ይሻላል እላለሁ። ለጥ ብለው ኣለም ሲቀድመን ተኝተው ከርመው ችግር ሲመጣ እንደሞፎከር ኣስጠሊታ ነገር የለም።ይቺ ግዝያዊ እና የሳምንት ኣርበኝነነት ማንንም ኣትጠቅምም። የችግሩ መሰረታዊ መንስኤ መረዳት ነው ጠቃሚው ነገር::
ዜጎቻችንን ለማዳን ተጨባጭ መፍትሄ ለማግኘት እየተረባረቡ ላሉ ሁሉም ማመስገን እፈልጋለሁ።የደቡብ ኣፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ እና ኣደባባይ ወጥተው ድርጊቱን የተቃወሙ የደርባን ከተማ ነዋሪዎች ኣፍሪካዊ ወንድማማችነትን በግዝያዊ ችግሮች መሸርሸር እንደሌለበት ላሳዩት ኣጋርነት ክብር ይገባቸዋል። የኣፍሪካ በጎ ነገር መዘገብ ዳገት እሚሆንባቸው የምዕራባውያን ሚድያ እይታችንን ሸራርፎ ኣፍሪካዊ ወንድሞቻችን እንዳንጠላ መጠንቀቅ ኣለብን።
ሆኖም ኣሁንም ጣታችን ወደ ራሳችን እንቀስር፤ ራሳችንን ዉብ እና ዉድ እናድርግ… ዘላቂ መፍትሄው ይህ ነውና! ደሀን እናቱም ኣትወደዉም ኣይደል ብሂሉ?
*******
this is, typically, a dehumanizing explanation of violence which ignores the fact that law is supposed to protect the weak against the well off. this may further facilitate impunity as it always holds victims responsible. what if the poor attacks the poor or the rich? It is not fair to say that the poor is bound to suffer because they are what they are. Does not Ethiopian government represent poor Ethiopians? in whose interest does EPRDF exercise power?do you know that even your economic determinism argument embraces that existence precedes essence? this shitty scribble of Nahusenay fetches the dictatorial tactic of avoiding accountability, nothing more. for what do you care if the poor can afford to buy machetes to kill the poor? realism, if you think of , honours survival that Ethiopian migration is to keep breathing and scape a grinding poverty.
ur economic analysis is right but ur conclussion is wrong endet bleh new yenesu meri yadeneqkow ljachew eko new ygedelu eyale yalew ye economy chgr siagatm behg wutuln malet aychalm ende? ende gn mnm bihon besew lij lay behg enji be esat maqatel alamnm.
u r right but endet bleh new yenesu meri yadeneqkow ljachew eko new ygedelu eyale yalew ye economy chgr siagatm behg wutuln malet aychalm ende? ende gn mnm bihon besew lij lay behg enji be esat maqatel alamnm.