ሙክታር ከድር የኦህዴድ ሊቀመንበር – አስቴር ማሞ ምክትል ሆነው ተመረጡ

የኦሮሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት(ኦህዴድ) ማዕከላዊ ኮሚቴ ድርጅቱን የሚመሩትን መሪዎች መረጠ።

በምርጫውም አቶ ሙክታር ከድር የድርጅቱ ሊቀመንበር፣ወይዘሮ አስቴር ማሞ ምክትል ሊቀመንበር ሆነዋል።

አቶ ሙክታር በፌዴራል መንግሥት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር አስተባባሪነትና በሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነት በማገልገል ላይ ናቸው።

ወይዘሮ አስቴር የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ሰርተዋል።

ድርጅቱን በሊቀመንበርነት የመሩት አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ በጤና ችግር ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው ይታወሳል።

አቶ ዓለማየሁ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድርነት መምራታቸውን ኢዜአ በዘገባው አስታውሷል።

የክልሉ መንግሥት ምክር ቤት(ጨፌ ኦሮሚያ)በሚጠራው ጉባዔ የክልሉን ርዕደ መስተዳድር ይሰይማል ተብሎም ይጠበቃል።

**********
ምንጭ፡- ኢዜአ – የካቲት 20/2006

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

more recommended stories