ባለፉት በርካታ ሳምንታት “ትዕምት” ወይም “ኢፈርት” በሚል የምህፃረ-ቃል መጠሪያዎቹ የሚታወቀው “ትካል ዕግሪ ምትካል ትግራይ(ትዕምት)” ኩባንያ በሹም ሽር እንደተጠመደ ይወራል::
ሂደቱ ስላልተጠናቀቀ እና/ወይም በተዛማጅ ምክንያቶች የተረጋገጠ ዜና ማቅረብ ሆነ ይፋዊ መረጃ ለማግኘት ቢያዳግትም ከኩባንያው ቅርበት ያለው ግለሰብ በመጋበዝ አጠቃላይ በሆኑ እና የዚህን ብሎግ አንባቢያን ትኩረት በሚስሉ ነጥቦች ላይ አጠር ያለ ቃለ-ምልልስ አድርገናል::
“ትካል ዕግሪ ምትካል ትግራይ(ትዕምት)” ወይም (Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigrai (EFFORT) የተሰኘው ኩባንያ – ህወሓት የሚባለው የኢሕአዴግ ፓርቲ በትጥቅ ትግል ወቅት ባፈራው ሀብት የተመሰረተ “የዘለቄታ በጐ አድራጐት ድርጅት”(Endowment) ሲሆን በኩባንያው ላይ በርካታ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትችቶች እንደሚሰነዘሩ ይታወቃል:: በመሆኑም ይህ ቃለ-ምልልስ እንደመነሻ በመውሰድ አንባቢያን የሚሰነዝሩት ሀሳብ በቀጣይ ለሚቀርቡ ቃለ-ምልልሶችና ዘገባዎቸች የትኩረት ነጥብ ይሆናሉ::
ጌታቸው አረጋዊ ለሶስት ዓመታት ገደማ የኩባንያውን የሚዲያ ጉዳዮችን ሲያስፈጽም የነበረ ሲሆን አሁን “ውራይና” የተሰኘ የትግርኛ የግል መጽሔት ዋና አዘጋጅ ነው::
ዳንኤል – በትዕምት ኩባንያ ውስጥ የአመራር ለውጥ እየተካሄደ ነው ይባላል፡፡ ስለዚያ ልትነግረን ትችላለህ?
ጌታቸው – የኣመራር ለውጥ እየተደረገ እንደሆነ ሰምቻለሁ። ለምሳሌ ከከፍተኛ ኣመራሮች ኣቶ ይተባረክ ኣመሃ ከም/ስራኣስፈፃሚነት እንደተነሱ ኣቶ ብርሃነ ኪዳነማርያም ግን በም/ስራኣስፈፃሚነት እንደቀጠሉ ነው የሰማሁ። ስለ ወ/ሮ ኣዜብም ኣንድ ግዜ ከዋና ስራ ኣስፈፃሚነት ተነስተዋል ይባላል ሌላ ግዜ ደግሞ ቀጥለዋል ይባላል:: ለሚመለከታቸው ስጠይቅ ሁለቱም ኣይነት መረጃ ኣገኛለሁ:: ብዙም ኣልገባኝም። ኣንትም ስለ እዚህ ከሌሎች ብትጠይቅ። ኦፊሻሊ ግን የተነገረ ነገር የለም።
ዳንኤል – የተነሱበት ምክንያት ምንድነው?
ጌታቸው – ለያንዳምዳቸው ምን ምን ተብለው/ተገምግመው እንደተነሱ ኣላወቅኩም። ኣቶ ይትባረክ ኣምሃ ወደ ስቪል ሰርቪስ ቢሮ ነው የተዘዋወሩ። በትዕምት በጣም ችግር እንዳለ በጀትም እንደታጣ ግን ለመገንዘብ ችየ ኣለሁ።
ዳንኤል – ወደአጠቃላይ ጥያቄዎች ልሂድና – ማነው የትዕምትን ቦርድና ሥራ አስኪያጅ የሚሾመው?
ጌታቸው – ትዕምት የራሱ ምክር ቤት ኣለው፤ ምክር ቤቱ ቦርድ ይመርጣል፤ ቦርዱ ደግሞ ስራ ኣስከያጅ ይሾማል እናም ለምክር ቤቱ ያሳውቃል። የትዕምት ምክር ቤት ከህዝቡ ነው የሚወጣው:: ማለትም ምክር ቤቱ (ከየወረዳው የሚወከሉ፡ ኢሮብ እና ኩናማ ጨምሮ)፣ ከሲቪክ ማህበራት ( የወጣቶች ማህበር፣ የሴቶች ማህበር፣ የገበሬዎች ወዘተ)፣ ከሀይማኖት ተቃማት፣ ከነባር የህወሃት ታጋዮች፣ ከምሁራን የትግራይ ፓትሪዮት ወዘተ የተውጣጡ ኣባላት የያዘ ነወ።
ዳንኤል – ምክር ቤቱ የተመረጠው መቼ ነው?
ጌታቸው – ምክር ቤቱ እኮ በህዝባዊ ምርጫ ኣይደለም የሚመረጠው። ከላይ እንደጠቀስኩት ከየሚመለከታቸወ ኣካላት/ድርጅቶችና ማህበራት ተወክለው ነው የሚያቃቁሙት። በዚህ ደግሞ ትዕምት በህግ ከተቃቃመበት ግዜ ጀምሮ ነው የተቃቃመው። በተሃድሶ ማግሰት በ2003 ዓ/ም ደግሞ በከፍተኛ ቁጥር የምክር ቤቱ ኣባላት እንዲቀየሩ ተደርገዋል። ኣመራሩም በዛው ልክ።
ዳንኤል – የህወሓት አመራሮች የትዕምት የቦርድ አባል ናቸው – አክሲዮን አላቸው ሲባል እንሰማለን፡፡ ይህ ማለት የድርጅቱ ባለቤቶች ናቸው ማለት ነው?
ጌታቸው – በኣሁኑ ሰዓት በትዕምት ሼር/ኣክስዮን/ ያለው የህወሓት ኣመራር የለም። ቦርድ ኣባላት ግን የህወሓት ከፍተኛ ኣመራሮች ናቸው። ይሄ እውነት ነው። ይሄ ማለት ግን የድርጅቱ ባለቤቶች ናቸው ለማለት ኣያስችልም። ባለቤቱ የትግራይ ህዝብ ነው። ግልፅ ነው።
ዳንኤል – ግን’ኮ አንዳንድ የሕወሓት አመራሮች በትዕምት ኩባንያዎች ኣክስዮን እንዳላቸው ይወራል። የቦርድ አባል ለመሆን ባለአክሲዮን መሆን አያስፈልግም ወይ?
ጌታቸው – የቦርድ ኣባል ለመመረጥ አክሲዮን ኖሮህ ወደ ጠቅላላ ስብሰባ መግባት መቻል እንዳለብህ ግልፅ ነው። ይሄ ድግሞ እንደ ግለሰብ በሚኖርህ አክሲዮን ወይም በምትመራው ድርጅት ስምም ሊሆንና በዚያ መሰረት ልትገባና ልትመረጥ ትችላለህ። ለምሳሌ ኣፍሪካ ኢንሹራንስ ኩባንያ በወጋገን ባንክ ትልቅ ሼር ኣለው፤ ስለዚህ የኣፍሪካ ኢንሹራንስ ስራኣስከያጅ በወጋገን ባንክ የቦርድ ኣመራር ለመመረጥ ትልቅ እድል ይኖረዋል ማለት ነው። በዛ መልክ ነው።
ዳንኤል – የትዕምት ድርጅቶች ትርፍ ለማን ገቢ ይደረጋል? ለምን ዓላማ ወጪ ይደረጋል?
ጌታቸው – ምን መሰለህ የትዕምት ድርጅቶች ትርፍ ወደ የትዕምት ኢንቨስትመንት ማዕከል/ካዝና/ ነው የሚገባው። ማዕከሉ ደግሞ ለካምፓኒዎች ኢንቨስትመንት ማስፋፍያ እና ለአዲስ ኢንቨስትመንት እንደአግባቡ ያዉለዋል። በጀት ሲመደብ በትዕምት ኢነቨስትመንት ማእከል ማኔጅመንት ተጠንቶ ይቀርብ እና በትዕምት ምክር ቤት ይፀድቃል። የትዕምት መተዳደርያ ደንብ ለግብረሰናይ ስራዎችም በጀት እንዲኖር ያዝዛል:: እስከኣሁን ግን ብዙ ኣይደለም። ለኣንድኣንድ ነገሮች ሰፖንሰር ከማረግ በስተቀር።
ዳንኤል – የህወሓትን ሥራ ማስኬጃ ወጪ ትዕምት ነው የሚሸፍነው ይባላል?
ጌታቸው – ይሄ ብዙ እዉነታ የለዉም። ህወሓት ወጪው የሚችለው ከኣባላቱ በሚሰበሰብ መዋጮ ነው። የተለየ ዝግጅት ኖሮት ከደጋፊዎቹ እና ከባለሃብቶች ገቢ ሲያሰባስብ ትዕምትም እንደ ሌሎች ድርጅቶች አስተዋጽኦ የሚያደርግበት ሁኔታ ኣለ። በተለየ መልኩ ግን ህወሓትን ኣይደግፍም።
ዳንኤል – አብዛኞቹ የትዕምት ድርጅቶች ከሥረው ለመዘጋት በቋፍ ላይ ናቸው ይባላል?
ጌታቸው – እንደምናስታውሰው ባለፈው ዓመት የ2005 ዓ/ም በጀት ግምገማን ወ/ሮ ኣዜብ ሲያቀርቡ በትዕምት ኩባንያዎች ጥሩ ዕንቅስቃሴ እንዳለ ገልፀው ነበር። ኦፊሻል የሰማነው እና የተከታተልነው ይሄ ነው። ከዛ በሃላ እንደሰማነው ከሆነ ደግሞ ለ2006 በጀት ገንዘብ እንዳነሰ ነው። በርግጥ የተምታታ ነገር ያለ ይመስላል፤ የተወሰነ ኪሳራ እንዳለም ኣያጠራጥርም። ከስረው ሊዘጉ በቋፍ ላይ ናቸወ የሚለውን እንካን እኔ ኣላምንበትም። ምክንያቱም በተለያየ ምክንያት ለግዜው ሊከስሩ ይችሉ ይሆናል እንጂ መዘጋት ኣይታሰብም:: ብዙ እህት ኩባንያዎች ስላሉ ኣንዱ ቢከስር ለኣንዱ እያበደረ ወደ ትርፍ እንዲገባ ያግዘዋል። የሄ ከኣሁን በፊትም ሲሰራበት የነበረ ኣሰራር ነው።
ዳንኤል – የትዕምት ኩባንያዎች በትግራይ የግሉ ዘርፍ እንዳያድግ የገበያ ዕድል የማጣበብ ተፅዕኖ አሳድረዋል ይባላል፡፡ እንዴት ታየዋለህ?
ጌታቸው – እንደውም የተገላቢጦሽ ነው። ትዕምት በትግራይ መኖሩ ባለሃብቶች እንዲመጡ ነው የሚያበረታታ። ይሄ ጥያቄ የሚያነሳ የእንዱስትሪ ባህሪን የማያውቅ ነው። ኢንዱስትሪዎች በባህሪያቸው ወደኣንድ የሚሰበሰቡት እንደ በግ። ይሄ ሎጂክ እንዳለ ሁኖ፡ እንዲያውም ትዕምት ሆን ብሎ የግል ባለሀብቶችን ያበረታታል ለራሱም ስለየሚያስፈልገው ጭምር። በተለይ ደግሞ ለጥቃቅንና ኣነስተኛ ተቃማት በተደራጀ መልኩ ነው የሚያግዘው። ሁለተኛ ደግሞ ትዕምት የተሰማራበት ኢንቨስትመንት በጣም ትልቅ ነው – በሀገር ደረጃም ቢሆን የግል ባለሀብት ሊደፍረው የማይችል ነው።
ዳንኤል – የግሉን ዘርፍ ካነሳን ላይቀር – በትግራይ ክልል ከትዕምት ውጭ ጉልህ የግል ዘርፍ ኢንቨስትመንት እንዲኖር አይፈለግም ይባላል?
ጌታቸው – ትግራይ እንድትለማ የሚፈልግ ሰው ከሆነ ትዕምት በመኖሩ ሊከለክለው ኣይችልም ሊያግዘው ካልሆነ በስተቀር። የትግራይን ልማት ለማደናቀፍ በመፈለግ ትዕምትን ሰበብ ኣድርጎ ሌላ ባለሀብት እንዳይመጣ የሚያዳክም ካለ ያ ሌላ ጉዳይ ነው። በክልሉም መንግስትም ይሁን በትዕምት የግል ባለሃብቶችን የሚገድብ ህግም ሆነ ፍላጎት የለም፤ ሊኖርም ኣችልም። እንዳውም ቅድም ከገለፅኩት የኢንዲስትሪ ባህሪ ተነስተው ሌሎች ባለሃብቶችን ለመሳብ ነው የሚጣጣሩት።
ዳንኤል – በሌሎች የሀገሪቱ ክልሎች የውጭ ኢንቨስተሮች በሰፋፊ እርሻዎች ልማት ሲሳተፉ በትግራይ ግን አልተፈቀደላቸውም የሚል ሀሜት አለ፡፡ ምን ያህል እውነት አለው?
ጌታቸው – በትግራይ እንደ ሌሎች ክልሎች ሰፋፊ መሬት እንደሌለ የታወቀ ነው። ስለዚህ መሬት ከሌለ ከየት ነው የሚሰጣችው? እንጂ የተለየ ፖሊሲ በትግራይ ኖሮ ኣይደለም። በምዕራብ እና በደቡብ ትግራይ ካሉ የተወሰኑ የእርሻ መሬቶች ግን የተወሰኑ ትንሽ ትንሽ መሬቶች የያዙ ኣሉ። በቅርቡ እንካን የተሰጡ ኣሉ:: በሁመራም በራያ ኣካባቢም። ስለዚህ ከማጣት እንጂ ካለመፈለግ ኣይመስለኝም።
ዳንኤል – እስኪ ስለ”ውራይና” መጽሔት ትንሽ ንረገን:: ማን ነው አሳታሚው? ለምንድን ነው በትግርኛ የሆነው?
ጌታቸው – “ዉራይና” መጽሔት የሚታተመው በwurayna media and Arts plc ነው። በግለሰቦች የተመሰረተ ነው። ለምንድን ነው በትግርኛ የሆነው? ለሚለው፤ በዋነኝነት ስለ ትግራይ ስለ የሚያወራ ለትግርኛ ኣንባቢዎች/ተናጋሪዎች ነው ስለሚታተም ነው። እግረመንገዱ ደግሞ የትግርኛ ስነ ፅሑፍ እና ቋንቋ ለማዳበር እንዲረዳ ነው። ጥያቄህ ገብቶኝ ከሆነ እንደዛ ነው።
ዳንኤል – ትግራይ ውስጥ መጽሔት ማዘጋጀት ቀርቶ አዲስ አበባ የሚታተሙትን እንካን ማሰራጨት እንደማይፈቀድ ነው የምንሰማው:: ለአንተ/ለ”ውራይና” እንዴት ተፈቀደ?
ጌታቸው – ኣቶ ዳንኤል የሰማሀው እጅግ በጣም ስህተት ነው። ኣዲስ ኣበባ የሚሰራጭ ሁሉም ኣይነት መጽሔትም ጋዜጣም መቀለ ይሰራጫል። ይሄ በተግባር የሚታይ ስለሆነ ሄደህ ማረጋገጥ ነው ሮማናት በሚባል ኣደባባይ ተዘርግተው ታገኛለህ። ስለ እዚ “ውራይና” መጽሔትንም የሚከለክል ነገር ኣይኖርም። ኣገሪትዋ እኮ ያላት ኣንድ ሕገ መንግስት ነው ትግራይ ለብቻው ልከለክል ቢልስ ማን ይሰመዋል፤ እምቢ ሕገ መንግስታዊ መብታችን ነው የምንለው እንጂ። የትግራይ መንግስት በልዩ ትኩረት ያበረታታል? ኣያበረታታም? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችል ይሆናል። ይሄን ደግሞ ገና ወደፊት እናየዋለን። እስከኣሁን “ዉራይና” ለመንግስት እንድያግዛት ጥያቄ ኣላቀረበችም። ሁኔታው ግን ጥሩ ይመስላል።
**********
ማስታወሻ – በዚህ ቃለ-ምልልስ ላይ ሆነ ተዛማጅ ጉዳዮች ላይበ ቀጣይ በሚቀርቡ ቃለ-ምልልሶችና ዘገባዎቸች ላይ እንዲተኮርበት የምትሹትን ነጥብ ከታች በአስተያየት መስጫው እንድትጠቁሙ እንጋብዛለን::
ትእምት???????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????????
He couldn’t precisely answer you who the BIG BOSS is. How come he, the media person, doesn’t know the Executive director of the company he works in ????? Does this mean: Transparency? Accountability? ….
IF the Endowment is of the people of poor Ti gray, why don’t they have annual report for the public – just like any public company anywhere else? why don’t they open discussion on priorities of the people demands? why don’t they invest on labor intensive rather than let the young people flee his beloved county.
The Endowment take loans from the CBE without the right way or procedure, I know this from a friend who works in Development Bank. And have been more or less run in loss. So if formerly they didn’t consult with the people and are running in loss: do you think this is a public endowment.
And I do know these companies never pay any loyalty cost the the community where they extract local resources. Why? Hope as they carry out the budget settlement, they don’t count this as a cost.
Why are they so stupid that they don’t let the company be administered by educated people????
I don’t have much more claim but three:
1) how is Budget auditing in EFFORT plus neat management? if neat management free from corruption is available I am definitely sure that none of the companies fall into risk since they have almost controlled the market. but who is auditing the expense and the income? and Big question about the corruption status in EFFORT companies?
2) what is the stored money doing in Banks? why not EFFORT expend it to large projects that the people can directly use from? or is there any secret behind like keeping TPLF reach and unbeatable party using that money? if so, there is still doubt in the peace of our Ethiopia.
3) Are the officers, the managers and the other workers in EFFORT companies professionally and personally qualified enough? I do have big doubt here also!!!!!!
Thanks!
The whole effort thins is a laughable fiasco. How can you be a non-profit foundation (which is a facade not to pay taxes and get preferential treatment on imports etc..) and engage in profitable businesses (effort has 80+ companies each with more than a billion birr start up in cement, engineering, transportation and all sectors of the economy in Ethiopia). According to sisbat nega’s response on his interview at the voa by a wide margin there’s no other wealthy organization as effort is in Ethiopia. Now danny (tplf’s errand boy) want us to believe that effort is tigrean people company and itsboard/members (entirely tplf) are serving it without any share or making any penny for themselves (LoLLLLLL). Not only that the company that has monopoly on every sector of the whole Ethiopian economy is on the verge of bancruptcy or collapse? SAAIIWEDDU YISSEKKU ALUU!!! YOU HAVE NO SHAME IN WRITING THIS KIND OF NONSENSE danny the errandboy?!?!? I feel so sorry for you and gematchew guy .. you are reaaly waste of skins!
Thanks Danny! That was an excellent interview. I bet Getachew knows the inside out to the EFFORT and his open-minded view makes this interview very balanced. When the question of EFFORT comes into place, people always gets too emotional on the tiny details and often ended up in missing the bigger picture. Remember, we are talking about the land that twenty five years ago was considered as “not fortunate enough even to cover the cost of a piece of chalk supplies to the schools”. The question of prohibitive effect of EFFORT on the private industries goes back to 1995 when the idea of Addis Pharmaceuticals, Mesobo Cement and Mesfin Industrial were on the groundbreaking process. The other question those “offended guys” are not answering is, if not EFFORT which Tigraway had enough knowledge and capital to build such massive investments? The most we could do was hotels after hotels. Now, thanks for the knowledge and wealth created by the endowment fund, we are seeing citizens participating in such industries – like the Raya Beer, Gypsum PLC and the so many large scale private farms in the Western and South Eastern lowlands, few to mention. The matter of poor management, inadequate auditing, lack of transparency, loss and profit always comes with any business and the fact that they survived the most difficult global economic climate shows might of the firms. But I also agree that as any business they need constant push and improvements, that I bet they will. But I always thank EFFORT for taking the lead in bringing businesses to the mark, as much as I thank the TPLF for rescuing us from extinction. I wish successes for continued development of the people!!
Daniel, I am happy you tried to address one of the ‘BIG 5’ questions(EFFORT BEING ONE OF THEM) that I keep them for many years. I suggest the following questions:
A. Ownership of EFFORT: isn’t it difficult to say it is owned by Tigray people? Are there any legal documents to support the claim? I want to see legal documents regarding its establishment, ownership, etc. Look at EFFORT’s own documents if you find, otherwise it is difficult to accept the hypothesis that it is owned by Tigray people.
B. Management of EFFORT: The guy tried to highlight ‘representatives’, but are there non-TPLF members and/or opposition party members in the board at least in the ‘mekrbet’? So, if all the members of the board and ‘mekrbet’ are TPLF members, the most realistic claim is to say it is owned by TPLF. Look at the members profile (both in the board and ‘mekrbet’).
C. Finacial management of EFFORT: Are there certified documents (well certified may mean approved by ‘mekrbet’ (EFFOR’s pwn ‘mekrbet’ or Tigray regional ‘mekrbet’, auditor or any thing that shows similar things) to show historical financial performance: total revenue, profit, re-invested amount, contributions to NGO’s etc.? Why it has never been told to the public if it is owned by the people, at least to Tigray rigional ‘mekrbet’?
D. Election of members of EFFORT: if it is owned by the Tigray people, isn’t it rational to elect members from Tigray regional ‘mekrbet’? Then one can defend why there are no opposition party members(if there are not) inside the board or ‘mekrebet’.
5. Corruption at EFFORT: there are thousands of rumours in the public about corruption at EFFORT. Were/are there any initiatives to prove and disprove such rumours? Did the management take these concerns and tried to come up with investigation reports and announce to its own ‘mekrebet’ and the general public?
etc……….
etc……….
etc……….
etc………
Thousands of other questions regarding EFFORT!!
1) ህወሃት ኦዲት ተደርጎ አያቅም የሚባለው እውነት ነው ወይ?
idiot ! he’s not a politician, he’s a journalist…………. but according to the current Ethiopia situation, you are right, he’s not only a politician and journalist, but he’s also an administrator, police officer, judge, killer, and he could be all he wants if he is affiliate of the TPLF mafia group……………. you got it?…………. but who knows, perhaps you are one of them or their child……….
ኣሁን ደህና ቃለ ምልልስ ኣበብኩለሀ
Let yours be the leading blog.
“Don’t be afraid to give your best to what seemingly are small jobs. Every time you conquer one it makes you that much stronger. If you do the little jobs well, the big ones will tend to take care of themselves.” Dale Carnegie
Get strong and stay Blessed!
I like the interview, and i appriciate the answer of Getachew. He is a real matured politician.