(Daniel Berhane)
ፕ/ር መስፍን ወልደማሪያም ባለፈው እሮብ ከአባይ ጉዳይ በተያያዘ የጦርነት ቅስቀሳን ለመገሰጽና የግብጽን የጦር ሀያልነት ‹ለማሳወቅ› አንድ ጽሑፍ አስነብበውናል፡፡
ጽሑፉ በጥድፊያ እና/ወይም እንደተለመደው የኢሕአዴግን ባለስልጣኖች ለማብሸቅ ተብሎ የቀረበ ስለመሰለኝ አላተኮርኩበትም ነበር፡፡
ነገር ግን እሳቸው የጽሑፋቸውን ግልብነት (shallowness) አስተውለው – ጠለቅ ያለ ማብራሪያ በመስጠት ለማጠናከር ወይም ለማስተባበል ይሞክራሉ ብዬ ስጠብቅ፣ ትችት የሰነዘሩባቸውን ሰዎች በመሀይምነት መፈረጅ ነው የመረጡት፡፡
ሰለሆነም እንደው ምናልባት እሳቸውም ሆነ <መስፍን ህፀጽ አይገኝባቸውም> ብለው የሚያምኑ የሚመስሉት ደጋፊዎቻቸው ልብ አላሉት እንደሆን ለማስገንዘብ፤ ስለፕ/ር መስፍን ጽሑፍ አንድ ሁለት ልበል፡፡
የ ጽሁፉ ዋነኛ ጭብጥ በሚከተለው ጥቅስ ይወከላል፡፡
‹‹ጦርነት እንኳን ገና በልቶ ላልጠገበ ሕዝብና ለጥጋበኞቹም አይመጭም፤ የተራበ ሕዝብ በጠገቡ መሪዎች ሲነዳ ግን ጦርነት ለአጉል ጀብደኛነት ዝና የሚጠቅም መስሎ ይታያቸዋል፤……ለፍቅር መተዋወቅ እንደሚያስፈልግ ሁሉ ለጠብም መተዋወቅ ያስፈልጋል፤ የተሟላ መረጃ ቢኖረን የጥንት ታሪክ እየጠቀስን ሰዎችን ለጦርነት እንቀሰቅስም ነበር ብዬ አምናለሁ፡፡ ››
የትኛው ‹የጠገበ› ባለስልጣን ነው ለጦርነት የቀሰቀስው?
የመንግስት ባለስልጣኖች አንድ ሁለት ጊዜ – ከ2 ዓመታት በፊት – ‹‹ግብጽ ብትወረንስ›› የሚል ጥያቄ ሲቀርብላቸው ታሪክ ጠቅሰው እንደማይፈሩ መግለፃቸውን አስታውሳለሁ፡፡ (ግን ሌላ ምን መልስ ሊሰጡስ ይቻላቸዋል?) ከዚያ ባለፈ ግን ግብጽን አስመልክቶ አዎንታዊ እንጂ አሉታዊ ዘገባ እና ቅስቀሳ በመንግስት ሚዲያ ሰምቼ አላውቅም፡፡
እንዲያውም ከካይሮ ግድም አሉታዊ ወሬ በመጣ ቁጥር የመንግስት ባለስልጣኖች ጦርነትና ግጭት የመከሰት ዕድሉን ስለሚያጣጥሉ፣ አንዳንድ ታዛቢዎች ‹‹እነዚህ ሰዎች አስጠንቁለዋል እንዴ›› ያሉበት ጊዜ አለ፡፡ ለምሳሌ – ከአንድ ወር በፊት የጠ/ሚኒስተሩን ቃል-አቀባይ ጌታቸው ረዳን ሳናግረው ‹‹ግድቡን እንደማናቆም ሲያውቁ ራሳቸውን ከእውነታው ያስታርቃሉ›› ነበር ያለኝ፡፡
እርግጥ መንግስት በይፋ የሚያሳየው መተማመን ስልታዊ ሊሆን ይችላል፡፡ ግብጾችንም ‹‹ማነው ከግድቡ ጀርባ ያለው?›› የሚያሰኛቸውም እሱ ሳይሆን አይቀርም፡፡
ሌላው የጽሑፉ አንኳር ሀሳብ እንዲህ ይነበባል፡-
‹‹አንዳንድ አስፈላጊ መረጃዎችን ላቅርብ፤ — የግብጽ የጦር ኃይል በዓለም አሥረኛ ነው፣ በአፍሪካና በመሀከለኛው ምሥራቅ የሚወዳደረው የለም፤ አንድ ሚልዮን ተኩል ያህል የጦር ኃይል አለው፤ በዓየር ኃይልም ከዓለም አሥራ አራተኛ ነው፤ በታንክ ብዛት አራተኛ ነው፤ በባሕር ኃይል ሰባተኛ ነው፤ በጦር በጀት አርባ ሦስተኛ ነው፤››
የመረጃ ምንጩን ባይጠቅሱም ከመጠነኛ አሰሳ በኋላ እንደተገነዘብኩት መረጃውን ያገኙት ከGlobalFirePower.com ነው፡፡ የዌብሳይቱን የደረጃ አሰጣጥ ስልት ከተረዳሁ በኋላ ግን መስፍን ጽሑፋቸውን በችኮላ እንደጻፉት ደመደምኩ፡፡
ከGlobalFirePower.com ደረጃዎች ጥቂቶቹን በምሳሌነት ላቅርብ፡-
* የእያንዳንዱን ሀገር ጠቅላላ የጦር አይሮፕላን (ጀት፣ ሔሊኮፕተር፣ ወዘተ) ብዛት በመቁጠር፡- በአየር ሀይል ለኢራን 5ኛ፣ ለሳውዲ አረቢያ 11ኛ፣ ለግብጽ 14ኛ፤ ለእስራኤል 20ኛ ደረጃ ይሰጣል፡፡
* በባሕር ኃይል (ሁሉንም የባህር ላይ የጦር ተሸከርካሪዎች በመቁጠር) በሰጠው ደረጃ ግብጽ ሰባተኛ ደረጃን በመያዝ ከቱርክ ከፈረንሳይ ከጣልያን ከሕንድና ከእንግሊዝ ትበልጣለች፡፡
* በታንክ ብዛትም የግብጽ ደረጃ ከህንድ ከሩሲያና ከፈረንሳይ በላይ ነው፡፡
* የግብጽ ወታደር ብዛትም (ግማሽ ሚሊዮን ቋሚና 1 ሚሊዮን ተጠባባቂ ወታደር በመያዝ) ከፈረንሳይ ከእንግሊዝና ከእስራኤል ይበልጣል፡፡
ይህን የደረጃ አሰጣጥ መሠረት አድርጎ የወታደራዊ ሀያልነትን መመዘን አሳሳች መሆኑ ለማንም ግልጽ ስለሆነ ብዙ አልልም፡፡
ያም ሆነ ይህ ግን የኢትዮጲያ ጦር ሀይል የወታደር ቁጥር እና የበጀት መጠን ውስን እንዲሆን የተደረገበት ሳይንሳዊ መነሻ ሲኖረው፤ ግብጽ ደግሞ የጦር ሀይል ብዛትና ወጪ ማብዛት የፈለገችበት የፖለቲካ ምክንያት ለግማሽ ክፍለ-ዘመን ከቆየው ከፊል-ወታደራዊ ስርአቷ ባህርይ ጋር ይያያዛል፡፡
ይልቁንስ ፕሮፌሰሩ ሊያነሱ ይገባ የነበረው ጥያቄዎች፡-
* በዚህ ዘመን የጦርነት መነሳት ሆነ ውጤት በጥይት ብዛት ነው እንዴ የሚመሠረተው? (የዲፕሎማሲ፣ የኢኮኖሚ፣ የinternational public opinion ወዘተ ወሳኝ ሚናስ)
* እኛ እና ግብጽ የጋራ ድንበር ስለሌለን፤ ግብጽ ሺህ ኪሎሜትሮች ተጉዞ ለሚደረግ ጦርነት በቂ ክህሎት፣ ልምድ፣ ድርጅት እና ሎጂስቲክ አላት ወይ?
* ሱዳን ወይም ኤርትራ በሺዎች የሚቆጠር የግብጽን ሠራዊት ለማስፈርና ለማሳለፍ ይፈቅዳሉ ወይ?
አንዳንድ ሰዎች፣- ውስን የዓየር ወይም የኮማንዶ ጥቃት(surgical attack) ሀሳብ በማንሳት የመስፍንን ጽሑፍ ለማሻሻል ይሞክራሉ፡፡ እዚህ ላይም የቴክኖሎጂ ጥያቄ አለ፡፡ ከካይሮ ተነስቶ ኢትዮጲያ ደርሶ የሚመለስ አይሮፕላን ግብጽ አላት? (ስለሌላትም) የሱዳንን ዓየር ክልል ጥሶ መብረር ብቻ ሳይሆን ማረፊያም ማግኘት ትሻለች፡፡ እናስ ሱዳን ትፈቅዳለች?
አንድ ነገር ልብ በሉ፡- ግድቡ ሲያልቅ ለማፍረስ ጥቂት ከባድ ቦንቦች ወይም ፈንጂዎች ሊበቁ ይችላሉ፡፡ ዛሬ ላይ ግን ማጥቃት የሚያስፈልገው እንዳለ የፕሮጀክት ሳይቱን ይሆናል፡፡ (ገና በጅምር ላይ ያለን ቤት ማጥቃት እና ተሠርቶ ያለቀን ቤት ማጥቃት አድርጋችሁ እዩት)
እነዚህንና ሌሎች ተዛማጅ ጥያቄዎች ሳይመልሱ ታንክ መቁጠር ግልብ ትንተና ይሆናል፡፡
ለማንኛውም ከሀይማኖት ወይም ፈሪሀ-እግዚያብሔር በመነሳት በድፍኑ ‹ጥጋብ ውርደት ያስከትላል› ብሎ መናገር ቢቻልም፤ የፕ/ር መስፍን ጽሑፍ ግን የመንግስት ሀላፊዎች ‹ጠግበው› ለጦርነት መቀስቀሳቸውን ሆነ ‹ጥጋባቸው› ‹ውርደት› እንደሚያስከትል በበቂ አላስረዳም፡፡
እርግጥ የግብጹ Al-Jamaa al Islamiya መሪ ኢትዮጲያ በአባይ ላይ የምትሠራው ሥራ የጦርነት አዋጅ ነው በማለት አፀፋውን ለመመለስ ዛቻ ብጤ አሰምቷል፡፡
ፕ/ር መስፍን የ‹ጠገቡ መሪዎች ለአጉል ጀብደኛነት ዝና› እየነዱን እንዳሉ አድርገው የቆጠሩት የሕዳሴ ግድብ ሥራን ይሆን እንዴ?
**************
Related:
* Ethiopia-Egypt | A War on Nile Improbable, for now
* Military expenditure at a historic low | Ethiopia
* Africa: Top 25 Military Spending Countries
he is one the ethiopian hero
Yeah, because you are a family member of professor mesfin. professor mesfin is a lier man.he don’t know the truth. I don’t know whether professor mesfin w/mariam is a kind of human or monkey. could you remember once up on a time what he said?
the tigrian peoples are made from one soap, and such a lot insult. he may have sth guarrent from Eritrean president esayas and ginbot 7. he may got a lot business also from Derg (mengistu hailemaryam) but he shouldn’t hate never his country Ethiopia. we love our country ethiopia. so you can follow being lier as your father or your uncle professor mesfin. but we are Ethiopians and we don’t cheat by business it might be american dollar or pound and such others.
bye bye.kkkkkkkkkkkkkkkkk!!!!!!
Truth
Prof. the true son of Ethiopia!!! He always stand for truth!…If you are accusing prof. for the action made in derg regime please come up with evidence and take him to court….Ok…Please all u stupid don’t bark..like..
@ Bekele; well said, Prof is a rational thinker at all; we should not focus only on the currenr issue, Abbay; see from general and previous points of the Prof. Ok!!
Mesfin Woldemariam,the master mind for the killings of thousands of Ethiopians during the derg regime is again trying any loophole to satisfy his last blood thirst from the yang Ethiopian.
No way we are looking any means to kick you stupid.I personally need to fight with such stupid thinkers to death.No room to kill our beloved mothers and there fetus again. Donkey!!!or Adgi!! ahyiya!!
I have also followed Professor Mesfin’s speeches writings etc for quiet a long time . Given his age , status and position I would assume he would use at least wiser, polite way of passing his ideas, whatever content and direction they may have . I don’t think , even our culture allows for the Professor’s way of speaking and referring to people. So I don’t see the Professor and his way of speech, writing etc as open , straight forward or bold. I see him as an arrogant and disrespectful person who purposefully disregards Ethiopian culture .
You are just one of the toxic losers we do not need dead ppl like you and your god father mesfin the pig.
Yes indeed! Dani you always amaze me sir.
Mesfin Woldemariam (mekshef) rest in hell.
በእድሜዬ ማለትም 40-45 ውስጥ ስለእውነት በእውነትና እውነት እንናገራለን የሚሉ በርካታ ሰዎችን አድምጫለሁ ። ስለ እውነት እንናገር ብለው ይነሱን እውነት የመሰላቸው ነገር እውነት ሳይሆን ቀርቶ ስለ እውነት ብለው ሃሰት ይናገራሉ። በእውነት እንናገር ይሉና በእውነት ላይ ሳይቆሙ ይቀራሉ። እንግዲህ ምን ቀረ እውነትን እንደወረደ እንናገራለን የሚሉ! እነዚህ ደግሞ ሁሌም እውነትን ለመናገር ፍላጎት ቢኖራቸውም ወይ ድፍረት ወይ ይሉንታ አልያም አድርባይነት ያደናቀፋችውና ይሰናከላሉ። ይህን ሁሉ መሰናክል አልፈው እውነትን ለመናገር ያልደከሙ ሰው አንድና አንድ ሰው ብቻ በእድሜዬ አይቻለሁ። እሳቸውም ፕ/ሮ መስፍን ናቸው። ግትር ሊሆኑ ይችላሉ። ግን እውነትን ይዘው ነው። ለምን ተነካሁ ባይ ሊሆኑ ይችላሉ አሁንም እውነትን ይዘው ነው። ከ እውነት ጋር ችግር ያለበት ከ ፕ/ሮ መስፍን ጋርም ችግር አለበት ማለት ነው። ፕ/ሮ ፖለቲከኛ አይደሉም ( ስለዚህ ዋሽተው ማሳመን አይፈልጉም) ፕሮ ዲፕሎማት አይደሉም (አሳምረው ተናግረው ሰው አንጀት መጎዝጎዝ አይሹም) ፕሮ እውነተኛ ሰው! ስለሃገራቸው ስለ ህዝባቸው መጻዊ እድልና እጣ ፈንታ የሚጨነቁ ክቡር የሃገር ቅርስ ናቸው። እባካችሁ ብዕርና ወረቀት አገኝን ብላችሁ እኝህን ክቡር ሰው አትናገሩ፡፤ እባካችሁ።
በዚህ አጋጣሚ ስለ አባይ የተናገሩትም እውነት መሆኑን በቅርቡ ታዩታላችሁና አትቸኩሉ!
Abay malet YE mengist bicha Adelem Abay malet ye Ethiopia hizb dem new. be Abay yemeta Antagesm!!!!wa
Ato mesfin Wa Wa Wa blenal
I expect a more detailed analysis rather than a shallow point-less piece that any googler may blog. I think this professor’s views, opinions and forecasts (since dergs times) need to be reviewed by someone to see how many times he got things right and how many times he misguided the public. I think that is the only way to drive him in or out of the media.
Being strong doesn’t mean having too many soldiers & equipment.
It is about quality not quantity..
who makes Egypt to have the world most ten powerful army? this is a clear lie do not post everything as it is. where is the location of Israel? do you know that Israel have the most ten powerful army in this world? so please do not make peoples to hesitate with false informatio. from middle east Israel have most number one strong army.
We have two losers: narrow minded supports & oppositions. Both of you come to your sense. Please!
dani yhe ygermhal..Eskinder Nega article posted on Nazret.com on March 26, 2011 said.Ethiopia is not ready to fight because of “vivid Eritrean air superiority”ldgemew “vivid Eritrean air superiority”.germuni ygerm
yours is a foolish idea. you have tried to comprehend what the professor said with your moaning belly, not with your mind.
i like the way u observe z prof. Article.tanx
The grantee of generation is good governance not only infrastructure and natural resources.The Congolese Diamond could’nt deliver them from poverty.The Corrupt EPRDF
GO HOME PROF. MESFIN, U ARE DRUNK
Dear Prof, You are entitled to your wrong opinion but not your own facts. May be its time for you to retire if this is what you can contribute: a totally shallow and inaccurate piece.
ስኔ እንለው እነዚህ ሰዎች በዚህ ትውልድ ማላገጥ ኣይበቃቸውም እንዴ ኣባይ ማለት ለኔ ከርካሽ ፖለቲካ በላይ ነው የመንግስት ሃላፊዎችም ሆኑ ተቃዋሚዎች የፈለገ ቢዘፍኑ ኣባይ ማለት ለዚሀ ትውልድ የህልውና ጉዳይ ነው ከድህነት እና ከውርደት በዚህ ጦርነት መሞተን እመርጣለሁኝ ግብጽ ሚሊዮን ሰራዊት ኣላት እስከ ኣፍንጫዋ ታጥቃለች ገለመሌ ይምጡ እና ያገናኘን ቢመጡ በ ፖርት ሱዳነ ወይም በኤርትራ ነው የዛኔ ያገናኘን የኢትዮጵያ 85+ ሚሊዮን ህዝብ ወታደር መሆኑን ረሱት እነዴ ድንቄም ሚሊዮን ወታደር ጫት ከመዋም እና ሳንድዊች ከመገመጥ ሌላ የማያቅ ወታደር የዞ ጉራ ምን የባላል ኑ እና ሜዳው የፍረደን እኔም ከዛሬ ጀምራቹህ እንደ ኣንድ ወታደር ቁጠሩኝ ከናንተው ከበሮ ሆድ ወታደር ኣልሰንፍም ኣባቶቸ እንፎርት ቁሞ መተኮሰ ኣስተምረውኛል ኣመዳም ኣናትህን ኣፍርስልሃለሁ ና እና ፈትነኝ በኣባይ ድርድር የለም ::
Mesfin Woldemariam the die hard falacy professor who never acknowledges reason