(የትምወርቅ ዘለቀ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ያቀረበውን ጥያቄ ግንቦት 24 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲያካሂድ ፈቀደ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው እንደገለጹት ፓርቲው ግንቦት 14 ቀን 2005 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ያቀረበውን ጥያቄ በመቀበል አንድ ሳምንት ተራዝሞ ግንቦት 24 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲካሄድ መፈቀዱን ገልጸዋል፡፡
አስተዳደሩ የፓርቲውን ሰላማዊ ሰልፍ ለአንድ ሳምንት እንዲራዘም ያደረገው ለ50ኛው የአፍሪካ ህብረት በዓል በርካታ እንግዶች አዲስ አበባ ስለሚገቡ አመራሩና የጸጥታ አካላት ሙሉ ሃይላቸውን ለስብሰባው ስኬት እየተረባረቡ በመሆኑ ነው፡፡
ፓርቲው ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ህገ-መንግስታዊ መብቱ ስለሆነ ሰልፉን በሚቀጥለው ሳምንት እንዲያካሄድ የተፈቀደለት መሆኑን የገለጹት ምክትል ከንቲባው የፓርቲው የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ውድቅ ተደረገ መባሉ ግን ትክክል አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡
አስተዳደሩም ፓርቲው ሰላማዊ ሰልፉን ግንቦት 24/2005 እንዲያካሂድ መፈቀዱንና የሚመለከታቸው አካላትም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደረጉላቸው የሚገልጽ ደብዳቤ መጻፉን ገልጿል፡፡
**********
Source: ERTA – May 24, 2013. Original title “ሰማያዊ ፓርቲ ለጠየቀው ሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ተሰጠው”.
**********
**********
bezih amroh melkam sira sirabet yetesera atafris don’t be stupid i am not woyane but pls be normal don’t dinie the truth Ethiopia is our land why you always need blood shed.
weregna ethiopiyawi athun
why do you have to cry out to foreigners when we Ethiopians can solve our problems on our own? a party which requires the fuel of the west is useless for Ethiopia!
ሰማያዊ ፓርቲ ልክ እንደስሙ ሰማያዊ ፈረስ ላይ ሆኖ በሰማይ እንደሚጋልብ ለማወቅ ደቂቃም አይፈጅም፡፡ የኢትዮጵያን ሶሲዮ-ኢኮኖሚያዊና ፓለቲካዊ ሁኔታን በውል ሳያውቅ ለፖለቲካ ሥልጣን የሚኖሮጥ ፓርቲ ከሕዝብ የሚያገኘው ምላሽና ድጋፍ የቀዘቀዘ እንዲሁም እንደቀደሙት ተመሳሳይ ፓርዎች ሁሉ ሲሮጡ የታጠቁት ሲሮጡ ይፈታል አይነት እንደሚሆን ብትገነዘቡ ይጠቅማል፡፡
የአንድ ብሔር የበላይነትን ይዞ ከ80 በላይ የሚሆኑ ብሔሮችና ብሔረሰቦች በሚኖሩባት አገር የራሱን ወይንም የብሔሩን የበላይነት ይዞ የተነሳ ፓርቲ፣ የብሔሮችና ሕዝቦችን ማንነት ጨፍልቆ የቀደሙትን ጨቋኝ ሥርዓቶች አጀንዳ ይዞ የተነሳ ፓርቲ ከጅምሩ የሞተ፣ ሕይወት የሌለውና የህዝብ ድጋፍ የማያገኝ እንዲሁም በጥቂቶች ላይ የተመሠረተ፣ ምናልባትም በኃይል የፖለቲካ አጀንዳውን በሕዝብ ላይ ለመጫን ጥረት ሊያደርግ የሚያስብ ሊሆን እንደሚችል ለማወቅ አያዳግትም፡፡
“አማራ ብሔር አይደለም“ ያሉት ኢንጂነር፣ ኮ/ል መንግሥቱ ኃ/ማሪያምን ነው ያስታወሱኝ፡፡ ለእሳቸው ያለኝ መልዕክት የኢንጂነሪንግ ዕውቀታቸውን ባላውቀውም ለፖለቲካው ግን ብዙ ርቀት ሄደው የዛሬይቱ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ የሚፈልጉት ምን እንደሆነ፣ ሕገ-መንግሥታዊ መብቶቻቸውና በተግባር እየተፈጸመ ያለውን ሁኔታ ከማጥናትና ከማወቅ ቢጀምሩ የተሻለ ይሆናል፡፡
የአንድ ብሔር የበላይነት ወይንም በአገራችን ውስጥ የ“assimilation” ሂደት ከ20 ዓመት በፊት ላይመለስ ሞቶ ተቀብሯል፡፡ በዚህ መቃብር ላይ ቆሞ ለማጓራት መሞከር ያን መንፈስ ሊመልስ ይችላል ተብሎ ታስቦ ከሆነ መሞከር ይቻላል፡፡ ከከጅምሩ ውድቀታችሁን አሳይታችሁናልና በርቱና በሰማያዊ ፈረሳችሁ በሰማይ ላይ ጋልቡ፣ በኢትዮጵያ ሕዝብ ፊት መከስከሳችሁ አይቀርም፡፡
በመጀመሪያ ሕገ መንግሥቱ እስከ ፈቀደ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርተናል፤ ያለብን ኃላፊነት ለሚመለከተው ክፍል ማሳወቅ ብቻ ነው ሲሉ አልነበረም? ታዲያ ለምን ቀኑን በሳምንት አራዘሙት? ዓላማው የሰብዓዊ መብት ረገጣውን ዓለም እንዲያይ አይደለም? የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትርና የአፍሪካ መሪዎች ከሄዱ በኋላ ቢደረግ ፋይዳው እንደሚቀንስ እንዴት አጡት? መንግሥት የሚለውን እንደማይፈጽም እንዴት ዘነጉት? ከሳምንት በኋላ ፌዴራል ፖሊስ ተልኮ ረጋግጦ ሲያባርሯቸው ያኔ ይረዳሉ።