የነሚ/ር መላኩ ጉዳይ| የናዝሬትና የጋምቤላ ጉሙሩክ ኃላፊዎች ታሠሩ

በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በፖሊስ ሲፈለጉ የነበሩት የናዝሬት ጉሙሩክ የህግ ማስከበር ኃላፊ አቶ ተመሰገን ጉልላት በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

ሰሞኑን በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉት ተጠርጣሪዎቸ ጋር ሲፈለጉ የነበሩት ግለሰቡ ከአዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ በመሸሽ ሱዳን ለመግባት ሁኔታዎችን ሲያመቻቹ ነበር፡፡

ተጠርጣሪው በእጃቸው የተለያዩ ሰነዶችና 160 ሺህ ብር ይዘው ነበር የተሰወሩት፡፡ የጋምቤላ ጉሙሩክ ስራ አስኪያጅ ለሆኑት አቶ ጌታቸው አሰፋ 80 ሺህ ብር በመስጠት ወደ ሱዳን ለመግባት ጥረት አድርገዋል፡፡

ሆኖም ግን በህዝቡና በጸጥታ ኃይሉች ትብብር ዋንኛ ተፈላጊ የነበሩት አቶ ተመስገን ጉልላትም ሆኑ እሳቸውን ወደ ሱዳን ለማስገባት የተባበሯቸው አቶ ጌታቸው አሰፋ በቁጥጥር ሰር መዋላቸውን ኢሬቴድ ከፖሊስ ያገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

*************

Source: ERTA

Check the Melaku Fenta et al saga archive for previous posts.

Daniel Berhane

more recommended stories