በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል በቁጥጥር ስር የዋሉት የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉሙሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር እና ሌሎች አስራ ሁለት ሰዎች ዛሬ ግንቦት 5/2005 ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
ተጠርጣሪዎቹ የቀረቡበት የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት አቃቢ ህግ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ማሟላት አለብኝ በማለት ባቀረበው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ላይ የቃል ክርክር አካሂዷል።
ችሎቱ ተጠርጣሪዎቹን በሶስት የክስ መዝገቦች በመከፋፈል የተመለከተ ሲሆን በእነ አቶ መላኩ ፋንታ የክስ መዝገብ ዘጠኝ ተጠርጣሪዎች ተካተዋል ።
በዚህ መዝገብ የቀረቡት ተከሳሾች ከተከሰሱባቸው ወንጀሎች መካከል ቀረጥና ታክስ ማጭበርበር፣ አራጣ በማበደር የተከሰሱ ግለሰቦችን ክስ ስልጣንን በመጠቀም እንዲቋረጥ ማድረግና በዚህም ያልተገባ ሀብት መሰብሰብ ይገኝበታል፡፡
የአንደኛው ተጠርጣሪ የአቶ መላኩ ፋንታ ጠበቃ ደንበኛቸው በዋስ ለመለቀቅ ያስችሏቸዋል ያሏቸውን ማስረጃዎች ለፍርድ ቤቱ በቃል አቅርበዋል።
ሀሳቡን ያደመጠው ፍርድ ቤትም በጊዜ ቀጠሮው ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ ለነገ ግንቦት 6/2005 ስምንት ሰዓት ቀጠሮ ይዟል።
በተመሳሳይ በነገብረዋህድ ገብረ ጊዮርጊስ የክስ መዝገብ ተጠርጣሪዎችንና የአቃቢ ህግ መከራከሪያን ያደመጠ ሲሆን መደበኛ የስራ ሰዓት በመጠናቀቁ በጊዜ ቀጠሮው ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለነገ ግንቦት 6/2005 ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ መዝገብ የተከሰሱት ተጠርጣሪዎች ከተከሰሱባቸው ወንጀሎች መካከል ወደ አገር ውስጥ እንዳይገባ የተከለከለ ሲሚንቶ እንዲገባ ማድረግ፣ በኮንትሮባንድ ንግድ የተሰማሩ ግለሰቦችን ማገዝ፣ ከተጠርጣሪዎች መካከል የሁለቱን ክስ የሚደግፉ ሰነዶችን ማሸሽ ይገኝበታል።
በሶስተኛው የክስ መዝገብ የሚገኙ ስድስት ተጠርጣሪዎች ደግሞ የናዝሬት ጉምሩክ ቅርንጫፍ ባልደረቦች ሲሆኑ ከተከሰሱባቸው ወንጀሎች መካከል በኮንትሮባንድ የተለያዩ እቃዎች ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ ማድረግና ያልተገባ ሀብት መሰብሰብ ይገኝበታል።
**********
Source: ERTA – May 13, 2013. Originally titled “በሙስና የተጠረጠሩት ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ”.
Check the Melaku Fenta et al saga archive for previous posts.
THANKYOU VERYMUCH
ማን ነው ባለሳምንት?
የኢትዮጲያ የታክስ ሲስተም ምን ነበር?
እንዴት ተሻሻለ?
ማን አሻሻለው?
አንዳንድ ያልተማሩ ነጋዴዎች የታክስ ስርዓቱን በጭፍን ይቃወማሉ መቃወማቸው አለመማራቸው ሲሆን
በርካታ ለውጥ ያመጣው የታክስ ስርዓት ለሀገሪቱ ምን ያህል አስፈለጊ እንደሆነ የማይታበል ሀቅ ነው
ይሁን እንጂ ወያኔ ፖለቲካውን ከነካህበት በምንም ምክንያት ይቅርታ ስለማያደርግ የታክስ ስርዓቱን ከምንም የተሻለ
እና ዘመናዊ ያደረጉት ሚኒስተር ከርቸሌ ሊወርዱ አይገባም ነበር የሳቸው ስህተት ግን ቀድሞዉኑ ወያኔን ማመናቸው ነው
ወያኔ በመሆናቸው ብጠላቸውም በታክሱ ዙሪያ ያደረጉት ለውጥ ግን ብቃት እንዳላቸው ለመገንዘብ ችያለሁ
ማን ነው ባለሳምንት?
አገር እንዳያድግ የልማት እንቅፋት የሆኑት ሆዳሞች ሌቦች መያዛቸው ደስ ብሎኛል፡፡ ማፈሪያዎች ሞት ክብር ነው እነዚህ ግን በቁማቸው የሞቱ ናቸው፡፡ በመድረክ ላይ ሲናገሩና ሲታዩ ለአገር የሚያስቡ ይመስላሉ ፡፡ እንዳውም እንደነዚህ ዓይነቱ መጠርጠር ነው፡፡ መንግሥት እንዲህ ዓይነቱ እርምጃ ሊቀጥልበት ይገባል፤ እንዳውም ዘግይቷል፡፡ ፡፡ ለሌሎቹም ትልቅ ትምህርት ነው፣ ሌሎቹም ንብረትና ገንዘብ እንዳያሸሹ በፍጥነት እርምጃ መወሰድ አለበት፡፡ መላኩ ፈንታ ጉበኛ ሌባ መሆኑ ገና ሀ ብሎ ጉምሩክ ሲገባ ነው የሚታወቀው ባለጉዳዮች ቢሮ ሲሄዱ አያስገባም አያነጋግርም ነገር ግን የምሽት ቢሮ በሰሜን ሆቴል አካባቢ (ባር) እየተገናኘ ጉቦ እንደሚወስድ፣ ሻንግሬላ ሬስቶራንት በየቀኑ ያዘወትር እንደነበረ ይታወቃል፡፡ አንድ ባለሥልጣን ወይም የወር ደመወዘተኛ በየቀኑ ትልልቅና ውድ የሆኑ ሬስቶራንቶች መመገብ ከኪሱ የሚከፍለው ይመስላቹሃል? ይህንን ሁሉ ቀደም ብሎ ሲነገር ነበር፡፡
በወቅቱ የሚሰማ ሰው አልነበረም፡፡ ለማንኛውም አሁንም በርቱ ሌሎችም ይኖራሉ ገና ይቀራል፡፡ ክብርና ምስጋና ለብሄራዊ መረጃ ደህንነት ሁሌም የምኮራበት የምተማመንበት ነው፡፡
I like your link