በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የተያዙት የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉመሩክ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ ባለቤት ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋይ ባለቤታቸው ከተጠረጠሩት ወንጀል ጋር ተያያዥ የሆኑ ሰነዶችን ሲያሸሹ በመገኘታቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ከፖሊስ የገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ኮሎኔል ሃይማኖት ከመኖሪያ ቤታቸው ወስደው በሌሎች ግለሰቦች እጅ እንዲደበቁ ያሸሺቸው ሰነዶች በተለያዩ ቦታዎች በአቶ ገብረዋህድ ስም የተመዘገቡ የቤትና የቦታ ካርታዎች ናቸው፡፡
ኮሎኔል ሃይማኖት ካርታዎችን ሲያሸሹ ጥቆማ የደረሰው የደህንነትና የፖሊስ ሃይልም ክትትል በማድረግ ካርታዎቹን ከተደበቁበት ቦታ ይዘዋቸዋል፡፡
በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ከትላንት በስትያ ግንቦት 2/ 2005 ዓ/ም በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች ቤት በተደረገው ብርበራ ከፍተኛ መጠን ያለው የኢትዮጵያና የውጭ ሃገራት ገንዘብ እንዲሁም የተለያዩ ሰነዶች መገኘታቸው ይታወሳል፡፡
*************
Source: ERTA
Check the Melaku Fenta et al saga archive for previous posts.