የፌዴራሉ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፋንታ እንዲሁም ምክትላቸው አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ 13 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን ገለፀ፡፡
የኮሚሽኑ መግለጫ እንዳመለከተው ኮሚሽኑ ከህዝብ የተቀበላቸውን ጥቆማዎች መነሻ በማድረግ ከብሄራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎተ ጋር በመተባበር በጥናት ላይ ተመስርቶ ከቆየ በኃላ በተጠርጣሪዎች ላይ በቂ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ማሰባሰብ ችሏል፡፡
ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት እስኪቀርብ ድርስ ተጠርጣሪዎቹ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲቆዩ ማድረግም አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ከሁለቱ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር በቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረጉት ግለሰቦች
1.እሸቱ ወልደሰማያት – በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የአቃቤ ህግ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
2.አስመላሽ ወልደማሪያም- የቃሊቲ ጉምሩክ ኃላፊ
3.ጥሩነህ በርታ- በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የተወረሱ ንብረቶች አስተዳደር ቡድን መሪ
4.አምኘ ታገለ- የናዝሬት ጉምሩክ ኃላፊ
5.ሙሉጌታ ጋሻው- በኦሮሚያ ልዩ ዞን መሀንዲስ
6.ከተማ ከበደ- የኬኬ ትሬዲንግ ባለቤት
7.ስማቸው ከበደ- የኢንተርኮንቴንታል ሆቴል ባለቤት
8.ምህረት አብ አብርሀ- ባለሀብት
9.ነጋ ገብረእግዚአብሄር- የነፃ ትሬዲግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ባለቤት
10.ዘሪሁን ዘውዴ -ትራንዚተርና ደላላ
11.ማርሸት ተስፉ – ትራንዚተርና ደላላ ናቸው፡፡
*********
Source: ERTA
* ዕርማት፡- (ቅዳሜ ማምሻውን መረዳት እንደተቻለው) አቶ አስመላሽ ወልደማርያም – በፌዴራል ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የጉምሩክ ስነ ስርዓት አፈፃፀም የስራ ሂደት፤ የኤርፖርት ጉምሩክ ድህረ ክሊራንስ ኦዲት የስራ ሂደትና የኤርፖርት ጉምሩክ ስነ ስርዓት የስራ ሂደት ቡድን መሪ በመሆን በተለያዩ ወቅቶች ካገለገሉ በኋላ ሚያዚያ 2004 ነበር ስራ የለቀቁት፡፡ (Daniel Berhane – May 12, 2013 – 4pm)
@abaybeshilo…so in your assessement, crimes are only those linked to cash theft ?? there are no innocent journalists in jail. In fact, the journalists you claim innocent ( so why not you represent them if you can prove their innocens) is even worse than what these guys did. Yet, both should face the court of law, and prove their way out. Ahus yeselechegn ye endante aynetu ye “tifozo” sira new. Just because you are a big fan of Eskinder Nega does not make him the “good guy”. If you have any idea to what I mean.
Go to salitemihret way Desse Road under Dimetree Building with his peasant families .It is the newthing. CATCH exploiter and make free the Innocent Jounalists and Politicians it was for the purpose of hidden theft .Now councoullors go to prison and listners go to school of them they start to steal the country with Deaf ears.