Highlight:
“የኢትዮጵያ ቅርስና ውርስ ማህበረሰብ በሰሜን ኣሜሪካ (EHSNA) የሚባል ድርጅት ኣቋቋሙ፡፡ ዝግጅቱን የሚያቀርብበት ጊዜም ከ ESFNA ጋር በተመሳሳይ ጊዜ እንዲሆን ወሰኑ፡፡ ብርቱካንም የዝግጅቱ እንግዳ እንድትሆን ኣደረጉ -ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ፡፡ እንዲህም ኣሉን – “የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ለዘመናት ስታቀርበውና ስትታገልለት የነበረውን የብርቱካን የክብር እንግዳነት ጉዳይ ይሄው እውነተኛና ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ኣሳክተውታል፡፡ ደስ ብሎናል ደስ ይበላችሁ፡፡ድል ለኛ ሞት ለ ESFNA” ኣሉ፡፡
የወያኔ ነው የተባለው ESFNAም ሃሳቡን ቀይሮ ብርቱካንን ጋበዘ፡፡ እንዲህ ነው ጨዋታ፡፡ “ታሪክ ራሱን ይደግማል” እንደሚባለው ዘንድሮ 2012 ደግሞ ሌላ “የመላ ኢትዮጵያውያን የስፖርት ማኅበር ኣንድ (AESAOne)” የሚባል ድርጅት ተቋቋመ፡፡
ይህ ኣጭር መጣጥፍ ዲሲ ላይ ስለመሸጉት ፖለቲከኞቻችን የህይወት ጉዞና የሰሞኑ እንቅስቃሴኣቸውን በተመለከተ የሚያማ ጽሁፍ ነው፡፡ ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲከኞች መፃፍ ለሚፈልግ ሰው ስለ ዲሲ ፖለቲከኞች መፃፍን የመሰለ ኣዝናኝ ነገር እንደሌለ በዚህ ኣጋጣሚ ልነግረው እፈልጋለሁኝ – ኣያሌ ያልተነገሩ ታሪኮች ኣሏቸውና (ስለ ኢህኣዴግ ብዙ ተጽፏል)፡፡
እነዚህ ሰዎች ባለፉት 21 ኣመታት ኣቅጣጫና መድረሻ የሌለው ተቃውሞ ሲያሰሙ የከረሙ ናቸው፡፡ ኣብዛኞቹ በትርፍ ሰኣታቸው ኣንዳንዶቹ ደግሞ እንደ ሙሉ ጊዜ ስራ (ቢዚነስ) የያዙት ናቸው፡፡ እንደ ሙሉ ሰኣት ቢዝነስ ከያዙት ውስጥ ለምሳሌ ኣበበ በለው፣ ኣበበ ገላው፣ ኣበበ በላቸው፣ ኣበበ ተክሌ፣ ኣበበ ሃይሌና ሁሉም የኢሳት ሰራተኞች ይገኙባቸዋል፡፡
ተቃውሞኣቸው የጀመረው ገና ኢህኣዴግ ምን ኣይነት መንግስት እንደሚያቋቁም ሳያውቁ፣ ዴሞክራሲያዊ ነው ኣይደለም ሳይለዩ ብቻ ኢህኣዴግ የሚባል ድርጅት ስልጣን ስለያዘ ብቻ መቃወም የጀመሩ ናቸው፡፡ በባህርያቸው ብሄር ብሄረሰቦች፣ በኣፍ መፍቻ ቋንቋ መማር፣ የራስን እድል በራስ መወሰን፣ ኦሮሚያ ክልል፣ ሶማሌ ክልል፣ ትግራይ …… ወዘተ የመሳሰሉ ቃላቶች ኣይመቿቸዉም፡፡ ከ 1983 ዓ/ም ጀምሮ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ጥምረቶችን ኣቋቁመዋል፣ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ሰላማዊ ሰልፎችን ኣደራጅተዋል፣ በብዙ ሚልዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከደጋፊ ኣሰባስበዋል፣ ኣልፎ ኣልፎም በስድስት ወርና በኣንድ ኣመት ውስጥ ኢህኣዴግን እንጥላለን ብለው ለደጋፊዎቻቸው ቃል ገብተው ባሉበት ጭጭ ብለዋል፡፡ ስለ ዛሬይቷ ኢትዮጵያ ሲኦልነት፣ ስለ ኢህኣዴግ ኣውሬነትና ስለ ኢህኣዴግ ደጋፊዎች ጭራቅነት ብዙ ሺ ኣርቲክሎችን ጽፈዋል፣ ኣሳትመዋል፡፡ ለበርካታ የኣሜሪካ ሴናተሮች በስልክ፣ በኢሜይል በደብዳቤ ኢትዮጵያ ላይ ማእቀብ እንዲጣል ኣቤቱታ ኣቅርበዋል፡፡ በኣንድ ወቅትም ወደ ኤርትራ ጎራ ብለው ኣቶ ኢሳያስን ተማፅነዋል፡፡ በርግጥም የዛሬን ኣያርገውና ከ 2000 ዓ/ም በፊት ዋሽንግተን ዲሲ ለኢህኣዴግ የማትመችና የማትደፈር ከተማ ኣድርገዋት ቆይተዋል (ኣሁን ስልታዊ ማፈግፈግ ኣድርገው ይሆን?)፡፡
የውድቀታቸው መጀመርያ በ1997 ዓ/ም ኢትዮጵያ ውስጥ የተደረገው በብዙዎቹ ዘንድ ነጻና ዲሞክራሲያዊ ነበር የተባለለት ምርጫ ነው፡፡ በወቅቱ እነዚህ የዋሽንግተን ፖለቲከኞች በኣንድ ሺ ኣመት ኣንዴ የማይገኝ እድል (Jackpot ) ከች ኣለላቸው – በምርጫ ተወዳድሮ ብዙ ወንበሮችን ባገኘው በቅንጅት በኩል ፓርላማ መግባትና በሂደት የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር መቀራረብና ሰላማዊና ስልጡን በሆነ መንገድ ማሳመን፡፡ ሆኖም ከመጀመርያው መቃወም እንጂ ሌላ ኣላማ ኣልነበራቸውምና እድሉን ሳይጠቀሙበት ቀሩ፡፡ ፓርላማ ኣንገባም የማለታቸው ጦስም ወደ ኣንድ ሺ ኣንድ መቶ ድርጅቶች ፣ጥምረቶችና ግለሰቦች በታትኗቸው ይሄው ኣሁን ያሉበት የኋልዮሽ ጋሪ ውስጥ ከቷቸዋል፡፡ (እዚህ ላይ RIP ብያለሁ)፡፡ በመሆኑም ባለፉት ጥቂት ኣመታት የተደራጀ የፖለቲካ ድርጅትና ኣላማ ኣጥተዋል፡፡ ደጋፊዎቻቸው ሁሉ ተሰላችቷል፡፡ ስለዚህ የሚደረጉ ተቃውሞዎች በሙሉ ያልተደራጁና ኣንዳንዶቹም ኣስቂኝ ናቸው – ለምሳሌ የህዳሴ ግድብን መቃወም፣ ቻይና ለኢትዮጵያ እርዳታ እንዳትሰጥ ባንዲራዋን ማቃጠል፣ የኢትዮጵያ መንግስት የተለያዩ ስብሰባዎችን ሲያደርግ ማወክና ኣጋጣሚው ከተመቻቸም የስብሰባው ተሳታፊዎቹን መደብደብ፣ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ ኣየር መንገድን እንዳይጠቀሙ መወትወት፣ መንግስትን የሚደግፉ ወይም ኢትዮጵያ ውስጥ መዋእለ ነዋይ ያፈሳሉ ብለው ያሰቧቸውን ሰዎች ስም ማጥፋት ወዘተ….. ናቸው፡፡
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መንግስት ዋሽንግተን ዲሲን ከማትደፈር የተቃዋሚዎች ምሽግነት ወደ ትግል ሜዳነት ቀይሯታል፡፡ ባለፉት ጥቂት ኣመታት ደጋፊዎቹን በቅፅበት ኣነቃነቀ፡፡ የተቃዋሚዎቹ ደጋፊዎች ብዛት ኣሽቆለቆለ፡፡ ከዛም ኣልፎ የዋሽንግተን ተቃዋሚዎች የተቃውሞ ኣጀንዳ የሚቀርጽላቸው የኢትዮጵያ መንግስትራሱ ሆነ፡፡ ለምሳሌ የኣባይ ግድብን እገነባለሁ ብሎ ገንዘብ ለማሰባሰብ ከፍተኛ ባለስልጣኖቹን መላክ፣ የግልገል ጊቤ ግድብን መገንባት፣ የእርሻ መሬቶች እንዲለሙ ለውጭ ኣገር ኢንቨስተሮች መሬት መስጠት፣ የእርዳታና በጎ ኣድራጎት ድርጅቶችን ኣዋጅ ማውጣት…… ኣስፈላጊ ሲሆን ደግሞ (ዋሽንግተን ጭር ካለ) ኣንድ ሁለት ጋዜጠኞችን ወይም የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችን ማሰር፡፡ ስለ
the diaspora in DC and all other Ethiopian haters are becoming out of the game because the Ethiopian people know them who are they.we Ethiopians in the homeland are busy to get rid of poverty and we are always united against poverty and our enemies who are stood against our development. We ar
e constructing the great dam -which is our national pride.if Diasporas do not contribute for this our national pride they are not really Ethiopians .and they should be silent .otherwise if they try to disturb while we are in constructing this dam they are our enemies and they could Egyptians(not all Egyptians of course)
Don’t be disappointed by diaspora politicians. I rather wish them long life in DC, enless freedome of speech. What can I say, they never get tired of talking, they have no gut but big stomach. Let them talk and dance in DC for ever. We are doing much better without them.
Ethiopian diaspora, the worst diaspora of any nation!!!… their love to Ethiopia is just by “talk” only words. Most of the diaspora I saw & meet show acts & are proud of acting western & yet they try to say they treasure being Ethiopian, bull sh*t!… they need to evolve!!!
This shows nobody really cares about Ethiopia…it’s just a way to fatten the pocket. I feel sorry for the type of Ethiopia in the future!. Our diversity can be make us prosper & shine in the world, but we should start to “think out of the box” & REALLY care for Ethiopia!
Well we have heard this motto that ወያነ will fail since Derge, Derge used to say that unfortunate for you he failed yet ወያነ shines. I would have taught you will be ashamed for singing the same song for over 17+21 years, it turns out I was wrong I read it all over the web.
Ethiopians are one. Woyane will fail in DC!!!
Indeed “…ከዛም ኣልፎ የዋሽንግተን ተቃዋሚዎች የተቃውሞ ኣጀንዳ የሚቀርጽላቸው የኢትዮጵያ መንግስት ራሱ ሆነ፡፡” And how about after Al-AMoudi stops the fund mainly because of their bad mouth, they now go and claim it is blood money, ….despite his limitation [the trend of fencing] he has done a lot more than all combined in creating jobs
You probably will have to review your article as it is full of factual errors. For example, Abebe Gelaw used to work for Woyane ministry of information before he left Ethiopia.