ስለትግራይ ሕዝብ ጆሮ የሚጠልዙ ንግግሮችን በማሰማት የሚታወቁት መስፍን ወ/ማርያም(የቀድሞ የአ.አ.ዩ. ፕሮፌሰር)፤ ባለፈው ነሐሴ በፍትህ ጋዜጣ ላይ ባቀረቡት ጽሁፍ የራሳቸውን ክብረ-ወሰን አሻሽለዋል፡፡
በኤርትራና በትግራይ ይኖሩ የነበሩ የኤርትራና የትግራይ ዜጐች ተግተው ኢጣልያንን ቢወጉ ኖሮ ከሐረር፣ ከሀድያና፣ ከሲዳሞ፣ ከሸዋ… ወደ ሰሜን መዝመት አያስፈልጋቸውም ነበር፤ ይህ ቢሆን ዛሬ ሌሎች ያልሞቱትን ሞት በመሞታቸው አይወቀሱም ነበር፤
አፄ ምኒልክ ጦራቸውን ሰብስበው በእግርና በበቅሎ ከደቡብ ተነስተው ትግራይ እስቲደርሱ ኤርትራና ትግራይ ምን አድርገው ጠበቁዋቸው? የኢጣልያ ጦር ትግራይን ሰንጥቆ አምባ አላጌ እስቲደርስ ማን ሊያቆመምው ሞከረ? የኢጣሊያ ጦር መቀሌ ገብቶ ሲመሽግ ማን ተከላከለው? ስብሓት እስከዛሬ ሳይገለጥለት ቀርቶ ከሆነ የኢጣልያንን ጦር ከአምባ አላጌ ያስወጣው የምኒልክ ጦር ነው፡፡ ከመቀሌም ምሽግ ያስወጣው የጣይቱ ዘዴና የምኒልክ ጦር ነው፡፡ በኢትዮጵያዊ ይሉኝታ ተሸፋፍኖ የቆየውን እናፍረጥርጠው ከተባለ ለማን አሳፋሪ እንደሚሆን ግልጽ ነው፡፡
ስለአድዋው ጦርነት ምስክርነት የሚሰጠን ገለልተኛ ታዛቢ እስክናገኝ ስለማይጨው ጦርነት የነበረ የዓይን ምክስር አንድ በቅርቡ ያነበብሁት መጽሐፍ ትዝ አለኝ፤ አንድ የቼኮዝላቫኪያ ጎበዝ የጻፈውን የሃበሻ ጀብዱ የሚል መጽሐፍ ተጫነ ጆብሬ መኮንን የተባለ ሰው የተረጎመውን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሳትሞታል፤ አቶ ስብሓት ብቻ ሳይሆን ማንበብ የሚችል ሁሉ ሊያነብበው የሚገባ መጽሐፍ ነው፤ እኔ ፈረንጅ ስለኢትዮጵያ የፃፈውን ማንበብ ከተውሁ ብዙ ዓመታት ሆኖኛል፡፡ ይህንን ግን በአንድ ቀን ተኩል ጨረስሁት፤ የኢትዮጵያን ዘማቾች ከኋላ እያጠቁ ስለነበሩት “የትግራይ ሽፍቶች” ማን ይናገር? የነበረ፤ ነውና እንዲህ ይላል፡-
“ የትግራይ ሽፍቶች ለምን ወንድሞቻቸውን ይገድላሉ?… ከመሀል አገር ስድስትና ሰባት ወር ሙሉ ፍዳውን እያየ ሲጓዝ ከርሞ እዚህ የደረሰው ወንድማቸው፣ የነዚህን ምስኪኖች ህይወትና ንብረት ከጠላት ለመከላከል የገዛ ህይወቱን አልጋ ላይ ጥሎ፣ ቤት ንብረቱን በትኖ መከራውን ባየ ለምን ይገድሉታል?”
እነዚህ ሽፍቶች ወንድሙን የገደሉበት አብቹ የሚባል የአስራ ስድስት ዓመት የሰላሌ ዘማች በጣም ተናዶ የራሱን የግል ቡድን አቋቁሞ ያሳድዳቸው ነበር፡፡
ይህን ተከትሎ ገብሩ ታረቀ (ፕሮፌሰር ኤመሪተስ) እና አማኑኤል መሓሪ (ፀሀፊ ተውኔትና ገጣሚ) ጠንከር ያሉ ምላሾችን ሰጥተዋቸዋል፡፡ የመስፍን ወ/ማርያም ጽሁፍ በየዌብሳይቱ የሚገኝ ሲሆን፣ ባንጻሩ ምላሾቹ ተደራሽ ባለመሆናቸው በዚህ ብሎግ ላይ ማተሙ ተገቢ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
********************
በነገራችን ላይ፡- በHobart and William Smith Colleges ድረ-ገጽ የሰፈረው የገብሩ ታረቀ ግለ-ታሪክ እንደሚከተለው ይነበባል፡-
Gebru Tareke – Emeritus Professor of History (1978)
Ph.D., Syracuse
M.A.,Wisconsin, Madison
B.A., Addis Ababa
*******************************
ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም
ገብሩ ታረቀ (ፕሮፌሰር ኤመሪተስ)
ሰላምታየን ላስቀድምና በፍትሕ ጋዜጣ ነሐሴ 6 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም. “ንግግራችን ትርፋማ እንዲሆን ከአሉባልታ እንውጣ” በሚል ርዕስ ያቀረቡትን ጽሑፍ በአንክሮ አንብቤ (በጊዜው ባይሆንም) አንድ ሁለት ጥያቄዎችን ለመሰንዘር ፈለግኩ፡፡ እንደመቅድም አድርጌ ግን የማይተኛና የማያስተኛ አዕምሮዎትን ብሎም ኃይለኛ ብዕርዎን ከሚያደንቅልዎት የቀድሞ ተማሪዎችዎ አንዱ መሆኔን እንዲያውቁልኝ እፈልጋለሁ፡፡
ከአሉባልታ እንውጣና በቁም ነገር አዘል ጉዳዮች ላይ እንወያይ በማለት የቸሩንን አስተምህሮት በአክብሮት ተቀብየዋለሁ፡፡ የፍትሕ አንባቢያንም እንደሚስማሙበት አልጠራጠርም፡፡ ነገር ግን በጽሑፉ ውስጥ አሳሳቢ ስህተቶችና ክፍተቶች መስለው ስለታዩኝ ነጥቦች ባጭሩ ላብራራ ይፈቀድልኝ፡፡
አንደኛ፣ አቶ ስብሐት ነጋ “የውጫሌ ስምምነት ለምን አስፈለገ;” ብሎ ሲጠይቅ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ አይመስለኝም፡፡ ሌሎችም ጠይቀውታል፡፡ እውነትም የውጫሌ ውል ለምን አስፈለገ? ለዓድዋው ጦርነት ዋናው መንስዔ ውሉ ያስከተለው ንትርክና ሙግት ነበርን? እነዚህና የመሳሰሉት ጉዳዮች በግልጽነት በጥልቀትና በሚዛናዊነት እስካልተፈተሹ ድረስ በዚች ሀገር ዕርቅና አስተማማኝ ሰላም ይገኛል ብለው ያምናሉ?
ሁለተኛ፣ የዓድዋን ጦርነት በተመለከተ፣ “የኤርትራና የትግራይ ዜጐች ተግተው ኢጣልያንን ቢወጉ ኑሮ”፣ የመሀል ሀገር ወገኖቻቸው ወደ ሰሜን መዝመት ባላስፈለገ ነበር ይሉናል፡፡ አስደማሚ ትችት ነው፡፡ ኤርትራውያን እኮ የኢጣልያ እስረኞች ከሆኑ ዓመታትን ቆጥረዋል፡፡ ራሳቸውን ነፃ ለማውጣት ለምን አጋጣሚውን አልተጠቀሙበትም እንል እንደሆነ እንጂ፣ ለኢትዮጵያ ለምን አልተዋጋችሁም ለማለት የሞራል ሉዓላዊነት የለንም፡፡ ፕሮፌሰር፣ ኢትዮጵያዊነታቸው ከተነጠቁ እኮ ሰንብተው ቆይተዋል! ለኢትዮጵያ “ተግተው” እንዲዋጉ የሚያስገድዳቸው የዜግነት ግዴታ ነበራቸውን;፡፡ ይህንን ለይቶ ለመረዳት ባለመቻል ሳይሆን ይቀራል አፄ ምኒልክ የእነዚያ 4ዐዐ የሚያህሉ ኤርትራውያን እጅና እግር አስቆርጠው የሕይወት ሽባዎች ያደረጉዋቸው; ከኢትዮጵያ ታሪክም የማይፋቅ አሻራ የተውልን; ከታሪካችን ጋር ለመታረቅ፣ ከድላችን ትረካ ጋር ገመናችንም አብሮ መጠናት የለበትም ይላሉ;
ትግራይን በተመለከተ፣ በዚያን ወቅት ክፍለ ሀገሪቱ የነበረችበት አሳዛኝ ሁኔታንና የኃይሎች አሰላለፍን ከግንዛቤ አለማስገባትዎ አስደምሞኛል፡፡ እውን ትግራይ በብቸኝነት የኢጣልያን ኃይል ልትመክት ትችል ነበር ብለው ከልብዎ ያምናሉ? እጠራጠራለሁ፡፡ ደግሞም ኢትዮጵያዊ ዜግነትን በትግራይ ዜግነት መተካትዎ ምን ቢያስቡ ነው? በዚህ አባባልዎ ብዙዎች ዜጐችን ሳያስከፉ እንዳልቀሩ ሳልጠቅስ ለማለፍ አልፈልግም፡፡
ሶስተኛ፣ እኔ ያላነበብኩትን መጽሐፍ አንብበዋል፡፡ በእርስዎ ትጋት ስደነቅ በራሴ ስንፍና አፈርሁ፡፡ የሆነ ሆኖ የቼኮዝላቫኪያው “ጐበዝ” በማይጨው ጦርነት “የትግራይ ሽፍቶች” በሀገር ወገኖቻቸው ስለፈፀሙት ግፍ የጻፈውን አስነብበውናል፡፡ መልካም፡፡ ይህንን መጥቀስዎ በሽፍቶቹ አሳብበው መላውን ትግራይ ለመፈረጅ ነው የሚል እሳቤ የለኝም፡፡ ምናልባት ወንጀለኞቹ ከራያና አዘቦ ሳይሆኑ አይቀርም የሚል ግምት አለኝ፤ ግምቴ ትክክል ከሆነ ስለድርጊቱ እኮ ብዙ ተጽፏል፤ ለምን አዲስ እንደሆነብዎት አስገርሞኛል፡፡ ለመሆኑ አመፁን ለመፈጸም የገፏፏቸው ታሪካዊና ማህበራዊ ምክንያቶች ይኖሩ ይሆን ብለው ራስዎን ጠይቀዋልን? በትክክል ጠቅሰውት ከሆነ “ጐበዙ”፣ ግን አላዋቂው ፈረንጅ ያልጠየቀው? ይህንን ስል ድርጊቱን የደገፍኩ መስሎ እንደማይታይብኝ እተማመናለሁ፡፡ ለመሆኑ ፈረንጅ የጻፈውን ማንበብ ካቆሙ ዓመታት ከሆነዎት፣ ይኸኛውን ለምን መረጡት? ወደዱትስ? ከኢትዮጵያ ታሪክ የሚያነቡት በመረጣ መሆኑን አስገንዝበውኛል፡፡ የሆነ ሆኖ ስለድርጊቱ እኔም በመጠኑ ጽፍያለሁና፣ ለየት ያለ ግንዛቤ ያገኙበታል ከሚል ግምት የመጀመሪያው መጽሐፌን፣ በተለይም አራተኛውን ምዕራፍ እንዲያነቡልኝ በትህትና እጋብዝዎታለሁ፡፡
“እንነጋገር ማለት እውነትን በማስረጃ አስደግፎ ነው” ሲሉ፣ የታሪክ ባለሙያነቴን ነውና ያስታወሱኝ አመሰግንዎታለሁ፡፡ እንደ ሙያተኛነቴ ደግሞ ታሪክን እየቦጫጨቁ ማንበብ ተገቢ አለመሆኑን ስጠቁም፣ እንደርስዎ የመሰለ ሊህቅና ተመራማሪ የሚስተው አይደለም ብዬ በማመን ነው፡፡ ፕሮፌሰር፣ እኔም እንደ አስገደ ገብረሥላሴ “የወዲያው ማዶ” ልጅ ነኝ፡፡ ግና ይህች ማስታወሻ የቀረበችልዎት ከአንድ የታሪክ ተማሪ እንጂ ከ”ማዶው ዜጋ” ሆና እንዳትታይልኝ አደራ እላለሁ፡፡ ታሪክ-ተኮር ጥያቄዎችንና አስተያየት እንዲህ ቢሆን ኖሮ በሚል ማዕቀፍ በመሰንዘሬ ‘ወተት ቢኖር በእንጀራ አምገህ ትበላ ነበር’ ካለችው ሴትዮ ጋርም እንደማያመሳስሉኝ አምናለሁ፡፡
ለጨዋታ ያህል ደግሞ ዲግሪዬና ፕሮፌሰርነቴ ከአሜሪካ ናቸው፣ በዶላር እንዳልተሸመቱ ሳረጋግጥልዎት በትህትና መሆኑን ይገንዘቡልኝ፡፡ ትንሽ ለማሰብና ለመተንፈስ ስለቆሰቆሱኝና ስለገፋፉኝ በእጅጉ አመሰግንዎታለሁ፡፡
ገብሩ ታረቀ (ፕሮፌሰር ኤመሪተስ)
Email: [email protected]
***********************************
ኤርትራ፣ ሚኒልክ፣ ፕሮፌሰር እና አቦይ ስብሓት
(አማኑኤል መሓሪ – ፀሀፊ ተውኔትና ገጣሚ)
ይህን ፅሁፍ ለፍትህ ጋዜጣ አዘጋጅቼ የላኩት ከሶስት ሳምንት በፊት ነበረ፡፡ ሆኖም ግን ፅሑፉን ያደረስኩበት ቀንና ጋዜጣው የሚወጣበት እለት በጣም ተቀራራቢ ስለነበር ለህትመት ሳይበቃ መቅረቱን ከጋዜጣው ዋና አዘጋጅ ወዳጄ ተመስገን ደሳለኝ ለመረዳት ቻልኩኝ፡፡ እኔም ፅሑፉ ካልወጣ አይቀር የተመስገንን ፅሑፍ መነሻ በማድረግ በተከታታይ የወጡትን የፕ/ር መስፍን እና የአቦይ ስብሓት ህትመቶችን በማንበብ የፀሐፊዎቹን ተከታታይ ሓሳቦች ያካተተ ሃሳብ ለመጨመር እና ለማጠናከር ጊዜ እንዲሰጠኝ ጠይቄ ዛሬ ምልከታዬን ለማስፈር ሞክሬያለሁ፡፡
ርዕሰ ጉዳዩ ከእድሜአችን በላይ ያረጀ ቢሆንም፤ በተለይም በወጣት ፀሐፍት በተደጋጋሚ የሚነሳው “ኤርትራን እንዴት አጣናት” የሚለው ጥያቄ እና ጭፍን ድምዳሜ በአብዛኞቹ ፀሐፊዎች ያለው ተመሳሳይነት የፈጠረብኝ ግረምት ነው ለዚህ ፅሑፍ መነሻ የሆነኝ፡፡ በዚህ ላይ ሰሞኑን አ ቦይ ስብሓት በገደምዳሜ ፕ/ር መስፍን እሳቸውን “እናፍረጥርጠው” በማለት የሰነዘሯቸው ሀሳቦች ሌላው ንሸጣ ነው፡፡
ወጣት ፀሐፍት ማለቴ ሆን ብዬ የመረጥኩት ቃል ነው፡፡ ምክንያቱም ካሁን ቀደም በነበሩ እና አሁንም ባሉ ጋዜጠኞች ላይ በርካታ አምደኞች ወጣት መሆናቸውን ከስማቸው በላይ በሚታየው ፎቶ ግራፍ መገንዘብ ከመቻሌም በላይ ከአንዳንዶቹ ጋር የቀረበ ግንኙነትም ስላለኝ ጭምር ነው፡፡ በእኔ እምነት እነዚህ አምደኞች ኤርትራን ያጣንበት መሰረታዊ ምክንያት ላይ ያላቸው ግንዛቤ ሁሉም ለማለት በሚያስችል ሁኔታ ተመሳሳይ ነው፡፡ የተመሳሳይነት ስህተቱ የሚመነጨው (አውቀው እያጠፉ ካልሆነ) በመሰረቱ ከፀሐፊዎቹ አይደለም፡፡ ስህተቱ ከተቃራኒው ወገን የሚቀርብ ይህ ነው የሚባል ተጨባጭ መልስ በተደራጀ እና በተጠና መልኩ ካለመቅረቡ ላይ ነው፡፡
በጣም የሚገርመው ደግሞ ቴሌቪዥን እና ሬዲዮ ማለትም ትልቁን ሚዲያ ለ20 ዓመታት በእጁ የያዘው አካል እያለ ኤርትራን አስመልክቶ ታሪካዊ ማስረጃዎችን የሚያቀርቡልን ፈፅሞ ከስርዓቱ ጋር ግንኙነት የሌላቸው ታሪክ ፀሐፊዎች እና ተመራማሪዎች መሆናቸው ነው፡፡ ገሚሶቹ የውጭ ዜጐች መሆናቸው ደግሞ የበለጠ ግርምትን ይፈጥራል፡፡
በእርግጥ አንዳንዶቹ በፕ/ር ደረጃ ያሉ ምሁራኖች እውነታውን በደምብ ስለሚያውቁት በዚህ ርዕስ ላይ ደፍረው ከመናገር ይልቅ ዝምታን መምረጣቸው በሰፊው የሚስተዋል ሲሆን ከዚህ የከፋው ደግሞ ወጣቶች አስተያየታቸውን ሲያሰፍሩ ጠላቴን በተሳሳተ መልኩም ቢሆን መውቀስህ ትክክል ነው ብለው ማመናቸው ነው፡፡
የዚህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ለኤርትራ መገንጠል አፄ ሚኒልክ ምንም ሚና የላቸውም ተጠያቂዎቹ አቦይ ስብሓት እና ጓደኞቻቸው ናቸው ማለታቸውን ተከትለው ለወጡት ኤርትራን የተመለከቱ ክርክሮች መነሻ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ቢያንስ ቢያንስ ነገርን ከስሩ ከመሰረቱ (Root cause) የማየት ችግር የአብዛኞቹ አምደኞች ችግር መሆኑን በቀላሉ የሚያመለክት ነበር፡፡ የነገርን ምንጭ የማያገናዝብ ፅሑፍ ሳይንስ መሆኑ ቀርቶ እምነት አሊያም አውቆ መተኛት ይሆናል፡፡
የነገርን ምንጭ ማገናዘብ ስንጀምር ኤርትራን የማትጨምር ኢትዮጵያ መቼ ተፈጠረች ብለን ለመጠየቅ እንገደዳለን፡፡ በመሆኑም አንድ መካድ የሌለበት የታሪክ እውነታን መጥቀስ ግድ ይለናል፡፡ ኤርትራን የማትጨምር ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈጠረች ው በአፄ ሚኒልክ ዘመነ መንግስት መሆኑን አረረም መረረም የግድ መቀበል ይኖርብናል፡፡ አፄ ቴዎድሮስም ሆኑ አፄ ዮሐንስ ከዚያም በፊት የነበሩት አፄዎች ኤርትራን የማትጨምር ኢትዮጵያን አያውቁም፡፡ ለዚህም ይመስላል በአፄ ሚኒልክ ያጣናትን ኤርትራ ከሃምሳ እና ስልሳ አመት በኋላ በአፄ ኃ/ስላሴ ስትቀላቀል የሚከተለው ውዳሴ ለንጉሱ የቀረበው፡፡
ምነው ቀድሞ ቢሆን ያንተ መወለድ
ምፅዋና አስመራ ጅቡቲ ሳይሄድ(የሕልም ሩጫ ቢተ- እንዳልካቸው መኮንን 1949)
ጅቡቲ የክርክራቸው ማዕከል ስላልሆነች ቢያንስ ጅቡቲንም በማን እና በምን ምክንያት እንዳጣናት በልባችን እናቆይና ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን ኤርትራን ከአፄ ኃ/ስላሴ በፊት በነበሩት ሚኒልክ እንዳጣናት ይህ ለጃንሆይ በውዳሴነት የቀረበው እና በመጽሐፉ የታተመው ግጥም ያስረግጥልናል፡፡ በዛ ላይ ፀሐፊው ቢተ-እንዳልካቸው መኮንን መሆናቸው በጃንሆይ ዘንድም ተቀባይነት ያገኙ ፀሐፊ መሆኑን መዘንጋት የለብንም፡፡
አሁን ሚኒልክ ኤርትራን ሳያስመልሱ ከአድዋ ለምን ተመለሱ የሚለውን የምንጊዜም አነታራኪ ርዕሳቸውን መጀመር እንችላለን፡፡ ይህን ርዕስ ከመጀመሬ በፊት አንዱ ማሳሰቢያ ቢጤ ጣል ማድረግ እንዳለብኝ ተሰምቶኛል፡፡ እንዲህ ያሉ ርዕሶችን ስናነሳ አንዱን መሪ ለማወደስ ወይም ለማዋረድ ለማስጠላት ወይም ለማስወደድ አላማ አድርገን መነሳት ስህተት መሆኑን መግለፅ ይኖርብኛል፡፡ ይልቅስ ሚኒልክን የመሰሉ መሪ እምዬ እስከመባል ያደረሳቸው ታላላቅ ተግባራት በጋራ ልንኮራባቸው፤ የፈፀሟቸው ስህተቶችን በጋራ ልናዝንባቸው ነው የሚገባ፡፡ አለመታደል ሆኖ ይህ ፀሐፊ በታላላቅ ተግባሮቻቸው የሚኮራባቸውን ያህል በኤርትራ ጉዳይ ላይ በወሰዱት አቋም ከሚያዝኑት ወገን ነው፡፡
ፕ/ር መስፍን ባሳተሙት ፅሑፍም ሆነ በዚህ ጋዜጣ ላይ በጻፉት ጽሑፍ በተደጋጋሚ እንደሚገልፁት ሚኒልክ አንድ ሺህ ኪሎ ሜትር ተጉዘው ትግራይን በተለይም አድዋን ነፃ ሲያወጡ የአካባቢው ህዝብ ማለትም የትግራይና የኤርትራ ህዝብ ምን ይሰራ ነበር? ከዚህ በላይ ምን ሊያደርጉ ይችሉ ኖሯል? የሚል መከራከሪያቸውን ከማቅረብ አልፈው በቅርቡ ለህትመት የበቃውን "የሀበሻ ጀብዱ" የተባለ በቺኮዝላቫኪያዊ /እሳቸው ጐበዝ ቼኮዝላቫኪያዊ ነው የሚሉት/ የተፃፈ መጽሐፍ ጠቅሰው እንዲያውም የትግራይ ሽፍቶች ለሚኒልክ ሰራዊት የጐን ውጋት ሆኖውባቸው ነበር የሚል ድምዳሜ ይዘው "በኢትዮጵያዊ ይሉኝታ ተሸፋፍኖ የቆየውን እናፍረጥርጠው ከተባለ ለማን አሳፋሪ እንደሚሆን ግልፅ ነው" ይላሉ፡፡ ለማን አሳፋሪ የሚለው ቃል ከሳቸው ባይጠበቅም፡፡
አቦይ ስብሓት ደግሞ "በአፄ ሚኒልክ ዘመነ መንግስት የነበረውን ብናየው ግን ከኢትዮጵያዊነት ስሜት የራቀ መደረግ ያልነበረበትን ስላደረጉ ነው ኤርትራ የተገነጠለችው” በማለት ተደረገ የሚሉትን ከኢትዮጵያዊነት ስሜት የራቀ ተግባር ሳይገልፁ ያልፉታል፡፡ ስለትግራይ ሽፍቶች እና ስለመሳሰሉት ባለፈው ሳምንት በሰፊው ስለገለፁት መድገሙ አላስፈለገኝም፡፡
ሁለቱን ጠንካራ ፅሑፎች መነሻ በማድረግ ወደ ቀጣዩ አጀንዳ ስገባ አቦይ ስብሓት መደረግ ያልነበረበት በማለት በግርድፉ ምናልባትም “በኢትዮጵያዊ ይሉኝታ” ያለፉትን እና ፕ/ር “ተሸፋፍኖ የቆየውን እናፍረጥርጠው” በማለት የተጠቀሙበትን አገላለፅ ከኢትዮጵያዊ ይሉኝታ በመገለል የማፍረጥረጥ አንድ አካል ወደሆነው ቀጣዩ ሐተታ እዘልቃለሁ፡፡
በዚህ ዓመት ፕ/ሩ ከጠቀሱት “የሀበሻ ጀብዱ” የተሰኘ መጽሐፍ ተመሳሳይ ጊዜ ለህትመት የበቃው እና በሁለት ፖላንዳውያን /ጎበዛዝት/ ተመራማሪዎች የተፃፈው እና በአለማየሁ አበበ “የኢትዮጵያ ታሪክ” በሚል ርዕስ የተተረጐመው መጽሐፍ አቦይ ስብሓት ሊነግሩን ያልደፈሩትን የሚኒልክ ከዓድዋ መመለስ ፖለቲካዊ ምስጢር በዝርዝር ያትታል፡፡ መጽሐፉ ሚኒልክ ከዓድዋ ድል በኋላ ወደ ሸዋ ለመመለሳቸው በተደጋጋሚ ሶስት ምክንያቶች እንደሚጠቀሱ ገልፆ እነሱም የክረምት ወራት መቃረብ፣ የውስጣዊ አመፆች ስጋት እና ድንገት ሳይሳካ ቢቀር የተገኘውን ድል ከንቱ እንዳይሆን ከመፍራት ነው የሚሉ ምክንያቶች ይጠቅስና ፖለቲካዊ አንድምታው ግን የኢትዮጵያ ውስጣዊ ሁኔታ መሆኑን በሰፊው ያብራራል፡፡ (ሶስቱን ምክንያቶች ውድቅ የሚያደርግበትን ምክንያት መጽሐፉ ላይ በሰፊው ስለምታገኙት እዚህ አልጠቅሳቸውም፡፡)
መጽሐፉ እንደሚያስረዳው በዚያን ወቅት በሸዋ እና በትግሬ ጠቅላይ ግዛት /የአሁና ትግራይ የቀድሞ መጠሪያ ነው/ መካከል የበላይነትን የማስከበር ሽኩቻ በተደጋጋሚ ሲካሄድ የቆየ መሆኑን ይጠቅስና እንዲህ እያለ ይቀጥላል
“በሚኒልክ ዓይን ትግሬ ለሸዋው ስርወ መንግስት የመሪነት ስልጣን እጅግ አደገኛ ተፎካካሪ ነው፡፡ ስለዚህ የትግሬ ተሰሚነት ማደግ ለዚህ ስርወ መንግስት የሚበጅ አይሆንም፡፡ ጣሊያኖችን ከኤርትራ ጨርሶ ማስወጣት የግድ የዚህን ጠቅላይ ግዛት ክብደት ያጠናክረዋል፡፡ ኢትዮጵያ የባህር በሯን መልሳ እጇ ከተደረገ የውጭ ንግድ ስለሚስፋፋ የባህር አዋሳኝ የሆኑ አውራጃዎች ሁሉ ትግሬም ጭምር በኢኮኖሚ እንዲጠነክሩ ያደርጋል፡፡ በአንፃሩ ሸዋ ከባህር ርቆ በደቡብ የሚገኝ እንደ መሆኑ ከባህሩም ጋር የሚያገናኘው ምንም አመች መንገድ ስለሌለው ተጠቃሚነቱ ውስን ነው የሚሆነው፡፡ ስለዚህ በሚኒልክ አስተሳሰብ የትግሬ መዳከም ለሸዋ ጠቃሚነው የሚባል ከሆነ ኤርትራን ለማስመለስ ያልተጨነቀበት ምክንያት ግልፅ ይሆናል”
በማለት በኢትዮጵያዊ ይሉኝታ የተሸፈነውን ታሪክ ይተነትናል፡፡
የወቅቱን ፋሽን ማለትም የላስታ፣ የትግራይ፣ የጐንደር እና የሸዋ የበላይነትን ለማስከበር ይደረጉ የነበሩ ሽኩቻዎችን ላስተዋለ ሚኒልክ ትግረኛ ተናጋሪውን ክፍል ሁለት ቦታ ከፍለው መመለሳቸው የሸዋን የበላይነት ከማስጠበቅ አንፃር የመከራከሪያ ሀሳቡን ከባድ ሚዛን እንዲደፋ ያደርገዋል፡፡
መጽሐፉ ያነሳውን ርዕስ ከማጠቃለሉ በፊት የደረሰበትን ድምዳሜ ሲያስቀምጥ
“ለጠቅላላው ኢትዮጵያ ጐጂ የነበረ ቢሆንም ለሸዋው ዲናስቲ የራሱን የበላይነት ለመጠበቅ እድል የከፈተለት እና ስልጣን ለማጠናከር ዋስትና የሚሰጠው በመሆኑ በትግሬ ኪሳራ የተገኘውን የመረብና የበለሳን ወንዞች የኢትዮጵያ ሰሜናዊ ወሰን አድርጐ ተቀበለ፡፡ የዚህ ስርወ መንግስት የውጭ ፖሊሲ ዋና ትኩረት ያረፈው በደቡብ አቅጣጫ አንጂ በሰሜኑ ላይ አልነበረም፡፡ ስለዚህ ሚኒልክ ኤርትራን ችላ ብሎ ከአድዋ የተመለሰበት መሰረታዊ ምክንያት የሸዋን እና ከዚህ ግዛት የበቀለውን ስርወ መንግስት ጥቅም ከመላዋ ኢትዮጵያ መንግስታዊ ጥቅም በላይ አድርጐ በማየቱ ነው፡፡ ዳግማዊ ሚኒልክ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታላቅ ሚና የተጫወቱ መሪ መሆኑ ቢታወቅም እንኳ ይህን እውነታ ሊለውጠው አይቻልም” ይላል፡፡ (ገጽ 353-356)
ፀሐፊዎቹ ዳግማዊ ሚኒልክ በኢትዮጵያ ታሪክ ታላቅ ሚና የተጫወቱ መሪ መሆናቸውን መግለፃቸው እንደሚያስመሰግናቸው ተስማምተን የዛሬው ማጠንጠኛ ወደሆነው የ”እናፍረጥርጠው” ፕሮግራም ስንመለስ አንዱ ተጨማሪ ሀገር በቀል መጽሐፍ ለመጥቀስ እንገደዳለን፡፡ በዘውዴ ረታ የተፃፈው “የኤርትራ ጉዳይ” የተሰኘው መጽሐፍ በኃ/ስላሴ ስርዓት ከ1955 እስከ 1962 የኤርትራ ቺፍ ኤግዚኩቲቭ የነበሩት ቢትወደድ አስፈሐ ወልደሚካኤል እንዲህ ብለው በምሬት መናገራቸውን በደማቅ ይገልፃል “እኛ ኤርትራውያን ንጉስ ሚኒልክ ለጣሊያን ሸጠውን ነው አንጂ ኢትዮጵያውያን ነን” (ገጽ 460)
ይህን ጽሑፍ ከማጠቃለሌ በፊት ሁለት ነገሮችን ማንሳት እፈልጋለሁ፡፡ አንደኛው ለዚያን ያህል አመታት ኤርትራን አግልለን ቅኝ ያልተገዛች ሀገር እያልን ማውራታችን ምን ማለታችን እንደነበረና ከዚያ በኋላ በተከታተሉት ስርዓቶች የተፈጠረው የታሪክ ሂደት መነሻ ምንጩ ምኒልክ ስለመሆናቸው ሲሆን ሁለተኛው ነጥብ ደግሞ የአፄ ሚኒልክን ያህል ባይሆንም ኃ/ስላሴ ኋላ ላይ የተፈጠሩትን ፌደሬሽኑን በአግባቡ አለመያዝ እና እኛን መስላቹ እደሩ የአገዛዝ ስህተቶች ጨምሮ (የኤርትራ ጉዳይን ልብ ይላል) ለኤርትራ ዳግም መነጠል የሻዕቢያ መፈጠርን ጨምሮ የራሳቸውን ድርሻ እንዳላቸው ማስገንዘብ ነው፡፡
በቀጣይ ጽሑፌ ከሻዕቢያ መፈጠር በኋላ ለኤርትራ መገንጠል ከኤርትራ ህዝብ ትግል በተጨማሪ በወቅቱ የነበረው የደርግ አገዛዝ ጉዳዩን የያዘበት መንገድ ፣ ኢህአዴግ ከሻዕቢያ ጋር የፈጠረው ስትራቴጂክ ትብብር እና ያራመደው አይዶሎጂ ፣ ኢህአፓን ጨምሮ በወቅቱ የነበሩ ሀይሎች በኤርትራ ጉዳይ ላይ የነበራቸው የኃይል አሰላለፍ እና ተቃርኖ በዚህም ምክንያት ኤርትራ ዳግም ከእናት ሀገሯ በህጋዊ ማህተም የተለየችበት ሁኔታ ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡ የነገሩ ምንጭ ሳይዘነጋ፡፡
********************************
ተዛማጅ ጽሁፎች፡-
ወያነ-ትግራይና የሉዓላዊነት አጀንዳ | Woyane-Tigray and the Question of Sovereignty
Yihe Mesfin Yemibal sew gin? Sasibewsasibew sasibew befetari sihtet tefetere indalil fetari aysasatim, be seytan tefetere indalil seytan ayfetrim. Tadiya min libelew wegen? Inde mesyten yale, chiraq, weyis bedin huno keruq yemishet. Awo yi sayshal ayqerim. Lemin bibal yemote ahyoa keruq yishetal ina, mikniatu bizu behiwot iyale agbesbiso silemibela.
you are below animal stupid you can not insult people you can insult him but not the people. you think you will live like this insulting you will pay for it
Mesfin deserves nothing he is just an old moron man who have lost all the respect value from the people of Ethiopia.
Shame on you mesfin Weld wtf
Amara, the world’s most evil tribe !
This fat pig, Prf Mesfin is twisting the truth.
endedurow meslot ko new, hezbu kedmoh awkewal !
The above article was from Professor Mesfin
የአስተሳሰብን ህግ ካልጠበቅን ለመግባባት ያቅተናል
ለብዙ ዓመታት የማውቀው ወዳጄ ገብሩ ታረቀኝ በፍትህ ጋዜጣ ላይ፣ የማላውቀው አቶ ዓሥራት በአድማስ ጋዜጣ ላይ በትግሬነታቸው ተቆርቁረውና እኔን ባዕድ አድርገው የጻፉትን አንብቤ ሁላችንንም የሚያውቁ ሌሎች ሰዎች አስተያየት እንዲሰጡበት በማለት መልስ ከመስጠት ተቆጥቤ ቆየሁ፤ ሆኖም እስካሁን ከአንድ ሰው በቀር የደረሰልኝ የለም፤ ስለዚህ እኔው ልጋፈጠው፡፡
ገብሩ ወዳጄ ነው የምለው ሰው ስለሆነ የጋለ ስሜቱን ይዞ አደባባይ ከመውጣቱ በፊት ከእኔ ጋር ጉዳዩን አንስቶ አለመወያየቱ ከሚችለው በላይ የሆነ ግፊት ቢያጋጥመው መስሎ ታየኝ፤ እንዲያውም ሌላ ሰው እሱ ያለውን ሲናገር ቢሰማ ለእኔ ቆሞ ይከራከራል ብዬ የምገምተው ሰው ነበር፤ አንድ ሳይካያትሪስት (የአእምሮ ሐኪም) ሲናገር እንደሰማሁት የጎሳ አስተሳሰብ የጎሳን ድንበር ጥሶ ወዳጅነት የሚባል ነገር አያውቅም ያለውን አስታወሰኝ፤ ይህ እንደማይሆን ተስፋ አለኝ፡፡
በምን ላይ እንደጻፍሁት ሳልናገር ለሁለቱም የትግራይ ተቆርቋሪዎች የሚከተሉትን አጫጭር ነጥቦች ላመልክታቸው፡-
1. ወያኔ ..ከሚኒልክ በፊት ኢትዮጵያ አገር አልነበረችም ሲል የአፄ ዮሐንስንና የራስ አሉላን ትግሬነትና ኢትዮጵያዊነት በመካድ.. ጀመረ፤
2… የጎንደርን በሬ፣ የጎጃምን በሬ፣ የሸዋንም በሬ፣
ባንድ አርጎ ጠመደው የትግሬው ገበሬ..
(የትግራይን የኢትዮጵያዊነት መሰረት ለማስረዳት የጠቀስሁት)
3. ..የትግሬ ዘር (ኤርትራውያንን ጨምሮ) የኢትዮጵያ መሰረት ነው፤ የትግሬ ዘር የኢትዮጵያን ታሪክ ተሸካሚ ነው፤ እንኳን በኢትዮጵያዊነታቸው ያሉትን ትግሬዎች የተገነጠሉትንም ለማጥፋት ማሰብ በምድርም በሰማይም ይቅርታ የማያስገኝ ወንጀል ነው፡፡ ከኤርትራውያን ጋር የተደረገውንም የወንድማማቾች ጦርነት አጥብቄ የተቃወምሁት በዚህ ምክንያት ነበር፤ በሰሜን ያሉትን ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን ከመቅጽበት ወደባዕድነት ለውጠን አሁን ደግሞ የተረፍነውን አጥፊና ጠፊ አድርጎ መፈረጁ ለማንም የሚበጅ አይሆንም፡፡..
ብዙ ሌሎችንም መጥቀስ እችላለሁ፤ ልብ ላለው ይበቃል፡፡
በደርግ ዘመን በዩኒቨርስቲ ውስጥ ስናወራ ስለ የአእምሮ ወዝ-አደር ስናገር አንዱ ካድሬ የአእምሮ ወዘ-አደር የሚባል ነገር የለም ብሎ ተቆጣ፤ አብረውን የነበሩት ሁሉ በስምንት ተኩል እኔ ቢሮ እንዲመጡ ጋበዝሁና መጽሐፉን ይዤ መጣሁና ለካድሬው አሳየሁት፤ በሌላ ጊዜ ደግሞ ሌኒን ተናዶ በደርዘን የሚቆጠሩ ካድሬዎችን በአንድ ትጉህና ታታሪ ባለሙያ የሚለውጠኝ ባገኘሁ ብሏል ስል ያው የማይማር ካድሬ ተቆጣና ..አይወጣውም…. አለ፤ መቶ ብር ከኪሴ አወጣሁና አንድ ጊዜ በነፃ አስተምሬሃለሁ፤ አሁን ግን መክፈል አለብህ፤ የሌኒንን ጽሑፍ ካላመጣሁልህ መቶ ብር ታገኛለህ፤ ካመጣሁ ግን መቶ ብር ትከፍላለህ ብለው አሻፈረኝ ብሎ በስሀተቱ ጸና፤ አቶ ዓሥራት ብዙውን ጽሑፎቾን አንብቤአለሁ ሲል እውነት እንዳልሆነ ስለማውቅ ውርርድ ላቀርብለት ፈልጌ ነበር፤ ስለአማራ የተናገረው እኔ የጻፍሁትን እንዳላነበበ ጥሩ ማስረጃ ነው፤ ሳያውቁ በእርግጠኛነት አዋቂ መስለው ለሚቀርቡ ቀላሉ መንገድ በአደባባይ ውርርድ ነው፤ ገብሩ ታረቀ እንኳን በአሜሪካ የፈረንጅ ልጆች ሲያስተምር ስለኖረ በአገር ውስጥ የተጻፈውን ሁሉ ማንበቡ አጠራጣሪ ነው፡፡
ለነገብሩና ለነዓሥራት ትልቁ ፍሬ ነገርና ቁም-ነገር ትግሬነታቸውን ለብቻቸው የያዙት መስሎአቸው ነው፤ በትግሬነታቸው ውስጥ አነሱንና እኔን የሚያያይዙ ብዙ ከባድ ሰንሰለቶች መኖራቸውን አያውቁም፤ ለነሱ ትግሬ ከትግሬነት ሌላ ፋይዳ ወይም ትርጉም የለውም፤ እንደዚህ ያለ ክርክር መነሳቱ ኢትዮጵያዊነት ምን ያህል እንደላላ የሚያመለክት ነው፡፡
..ማወቅ ወደ እርግጠኛነት የሚያመራው በመጠራጠርና በመጠየቅ ነው፤ አለማወቅ ግን ምንጊዜም ወደጠን ካራ የጨለማ እርግጠኛነት የሚመራ ነው፤ አለማወቅ ከኃይል ጋር ሲጋባ የአምላክን ቦታ ይይዝና እስመ አልቦ ዘይሰአኖ ይሆናል፡፡..
ሁለቱም ሰዎች፣ ፕሮፌሰር ገብሩም አቶ ዓሥራትም ባሳዩዋቸው ሁለት የእውቀት ጉድለቶች ልጀምር፤ ይህንን ማድረጉ አያስደስተኝም፤ ነገር ግን አለማወቅን ወደ እውቀት እየለወጡ ሰዎችን ማሳሳቱ፣ ከዚያም አልፎ በትግራይ ማህበረሰብ ላይ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ የጥላቻ መርዝን ለመንዛት የሚደረገውን ሙከራ አገርን የሚጎዳ ነውና ሊታለፍ አይገባም፤ ፕ/ር ገብሩም አቶ ዓሥራትም በሂሳብ ትምህርታቸው ስለ Set theory ትንሽ ቢያውቁ ..የኤርትራና የትግራይ ዜጎች..ያልሁት ደማቸውን አያፈላውም ነበር.. ትግራይ በኢትዮጵያ ውስጥ፣ ኢትዮጵያ በትግራይ ውስጥ ይገኛሉ፤ የኔ ስህተት የአንባቢዎችን ደረጃ ከፍ አድርጌ መመደቤ ነው፡፡
ሌላው የእውቀት ልዩነት ሰው የመሆን ግንዛቤያችን ነው፤ ለእኔ ሰው በቁና የሚሰፈር፣ ወይም በከረጢት የሚታሰር አይደለም፤ እያንዳንዱ ሰው በነጠላ ለራሱ ስራ ኃላፊነቱን ይወስዳል፤ እንኳን በ2004ዓ.ም ጥንትም ቢሆን ጽድቅም ሆነ ኩነኔ የግል ነው፤ በጎሳ ወይም በጅምላ አይመጣም፤ የሰው ልጅ እንደ አይጥና እንደድመት አይደለም፤ እንኳን አብሮ የኖረና የተዛመደ፣ አንዱ ለሌላው የመጨረሻ መስዋዕትነት የከፈለ ቀርቶ እንግዳም ቢሆን አንዱ ለሌላው መሰረታዊ ጠላትነት የለውም፤ ፕ/ር ገብሩና አቶ ዓሥራት እንጀራቸውን ለማብሰል ለትግሬዎች ዘብ የቆሙ መስለው ባልገባቸው ነገር ሁሉ ደማቸውን ያገነፈሉት እኔን ባዕድ በማድረግ ለመጠቀም ነው፤ ለእነሱ አዝናለሁ፤ የትግራይ ህዝብ እኔን በነሱ ዓይን እንደማያየኝ አምናለሁ፡፡
ፕ/ር ገብሩ ..እኔም እንደአስገዶም ገ/ስላሴ የወዲያ ማዶ ልጅ ነኝ.. ይላል፤ ወዲያ ማዶ ስል ትግራይ ማለቴን ማን ነገረው? ስብሐት ነጋን ወዲህ ማዶ ሳደርገው በገብሩ ግንዛቤ ትግሬ አይደለም ማለቴ ነው መሰለኝ.. ገብሩን ወዴት ከፍ ከፍ እለዋለሁ.. ገብሩ የወዲያም የወዲህም ልጅ አይደለም፤ የባህር ማዶ ልጅ ነው..
ሁለተኛ ስለኤርትራውያን የተናገረው መልካም ስሜቱን ከመግለጽ በቀር መጽሐፉን ቢያነብበው ኤርትራውያን በስሜት ሳይሆን በተግባር እሱ ..እስረኞች.. ያላቸው ሰዎች የገለጹትን እውነት ያስተባብለዋል፤ በተጨማሪም ለታሪክ ባለሙያው መንገር ካልሆነብኝ የሠርጸ ድንግልን ዜና መዋዕል ቢያነበው ከወራሪ መከላከል እንደሚችሉ ሊገነዘብ ይችላል፡፡
ሶስተኛ፣ ..የሞራል ሉዓላዊነት.. በአማርኛም ሆነ በእንግሊዝኛ አልገባኝም፤ አላግባብ ተሰካክቶ የተደነቀረ ነገር ነው፡፡
አራተኛ፣ ለኢጣልያ ገብረው የጠላት ወታደር በመሆን ወገናቸውን የወጉት ኤርትራውያን እጅና እግር መቆረጡ በአሁኑ ጊዜ ላለነው የሚዘገንን ነው፤ ነገር ግን ፕ/ር ገብሩ በዓድዋ ጦርነት በምኒሊክ አገዛዝ የተደረገውን ሲናገር በቅርቡ በማይጨው የደጃዝማች ኃ/ስላሴ ጉግሳን ሆነ በሌላ የተፈፀመን ቅጣት አለማንሳቱ፤ በአገራችንም ቢሆን የአፄ ቴዎድሮስን አልሰማም ይሆን? የአጼ ዮሐንስንስ አልሰማም ይሆን? ወይስ እኔ እንዳነሳለት ፈልጎ ይሆን? አንዳንድ ነገሮችን እየነቀሱ በማውጣት ታሪክ እንደማይጻፍ ለፕ/ር ገብሩ መንገር አያስፈልግም፤ የምኒልክን ሀጢአት ለማበራከት ከሆነ ከሸዋ ሳይወጣ በጧፍ ያነደዱትን ሊጨምርበት ይችላል፡፡
አሁን ከባድ ወደሚመስሉኝ ነጥቦች ልምጣ፤ ለእኔ እንደሚገባኝ ታሪክ ሁነትን በመግለጽ ይጀምራል፤ በትክክል ለተመዘገበው ሁነት ፍቺ መስጠት፣ ወይም ጥሩና መጥፎነቱን በመግለጽ ፍርድ መስጠት በኋላ የሚመጣ ነው፤ በሌላ አነጋገር ፍርድ ሁነትን ተከትሎ ይመጣል እንጂ የሁነቱ ፍቺ ወይም በሁነቱ ላይ የሚሰጠው ፍርድ አይቀድምም፤ ይህ ከሆነ ፈረንጆች እንደሚሉት ፈረሱን በጋሪው ለመጎተት እንደመሞከር ይሆናል፤ አጉል ድካም ነው፤ አንድ ጊዜ ብቻ አይደለም፤ ለሁለት ጊዜ ገብሩ ለማድረግ የሚፈልገው ይህንን ነው፤ ምን እንደተናገርሁ ለአንባቢው ሳይነግር፣ በራሱ ግምት የተናገርሁ ለመሰለው ነገር ፍቺና ፍርዱን መስጠት ይጀምራል፤ ይህ የእውቀትና የእውነት ፈላጊ ምሁር የአጻጻፍ ስርዓት አይደለም፤ በዚህ ጉዳይ አቶ ዓሥራት እኔ ያልሁትን በትክክል ጠቅሶ ወደራሱ አስተያየት ይሻገራል፤ ይህ ተገቢ ነው፡፡
ገብሩ ግን ..ኢትዮጵያዊ ዜግነትን በትግራይ ዜግነት መተካትዎ ምን ቢያስቡ ነው?.. ይለኛል፤ መጀመሪያ በዚህ ጉዳይ ላይ እኔ ምን እንደተናገርሁ አይገልጽም፤ የተገነጠለውን ኤርትራን ይገድፍና ዘልሎ ትግራይን ለማስገንጠል የፈለግሁ ለማስመሰል ..ምን ቢያስቡ ነው?.. ይለኛል.. ኤርትራን የጨመረ እንደሆነ ተንኮሉ ይበላሻል.. ለኢትዮጵያውያን ነግሮ ሊያስወነጅለኝ ፈልጎ ነው? ወይስ ለአስገንጣዮቹ ነግሮ ሊያስሸልመኝ.. ለተገንጣዮቹና ለአስገንጣዮቹ በስሜት ማንኛችን እንቀርባለን?
ከላይ እንደጠቀስሁት በሂሳብ ወይም በፍልስፍና ንባብ ቢደገፍ እዚህ ስህተት ላይ አይወድቅም ነበር፤ ..ምን አስበህ ነው?.. የሚለው ለመወንጀልና ለማስወንጀል የተቃጣ ለማንም ግልጽ የሆነ ንጹህ ተንኮል ነው፤ ከኢትዮጵያ ዜግነት የተለየ የትግራይ ዜግነት መኖሩን ሊነግረኝ ያሰበ ይመስላል፤ እንዲህ ያለ መያዣና መጨበጫ የሌለው ነገር እኔ አልተናገርሁም፤ በ1998 ጓደኞቼና እኔ ከተከሰስንበት አንዱ የትግሬን ዘር ለማጥፋት መሞከር የሚል ለጆሮም የሚቀፍ ነገር ነበር፤ በ1998 ፍርድ ቤት በቀረብንበት ጊዜ የዛሬው የገብሩ ጽሑፍ ቢገኝ ትልቅ ማስረጃ ሆኖ ይቀርብ ነበር፤ እግዚአብሔር ሲያወጣን ገብሩ በዚያን ጊዜ ከእኛ ጣጣ ተከልሎ በአሜሪካው ነበር፤ ዛሬም 1998 እየሸተተ ነውና ገብሩ ስራ አያጣም፡፡
አንድ የታሪክ ባለሙያ ፕ/ር ትናንት በጋዜጣ የተጻፈውን በትክክል መድገም ሲሳነው ከአስር፣ ከሃምሳ፣ ከመቶ ወይም ከዚያ በላይ የቆዩ ጉዳዮችን እንዴት አስታውሶ እውነቱን ሊናገር ነው? እኔ የጻፍሁትን እሱ በመሰለው ተርጉሞ ከአገርና ከዘመድ ጋር የሚያጣላ ከባድ ነገር ሲለጥፍብኝ በጣም ያሳዝናል፤ መቼም ኢትዮጵያ ሆነና ነው እንጂ በሌላ አገር ቢሆን የጋዜጣው አዘጋጅ ያልተባለ ነገር ተቀብሎ አያሳትመውም ነበር፤ ከዚያም በላይ ገብሩና እኔ ስለምንተዋወቅ እሱ የጻፈውን ሌላ ሰው ቢጽፈው ገብሩ ይቃወማል ብዬ ሙሉ እምነት ነበረኝ፤ እንዲህ ዓይነት ጭራሽ ትርጉም የሌለው ነገር እኔ አልወጣኝም፤ ከኢትዮጵያ የተለየ የትግራይ ዜግነት የሚባል ነገር መኖሩንም አላውቅም፤ ዜግነት ምን እንደሆነና ከጎሳዊነት የተለየ መሆኑን አውቃለሁ፤ ዜግነትን በጎሰኛነት የሚተኩት እነማን እንደሆኑ ገብሩ አላወቀም ማለት ነው፤ ወይም አምስት መቶ ዶላር ኪራይ የሚከፈልበት ጊዜያዊ ዜግነት ከሌለው በቀር ወደ ቀበሌ መታወቂያ ለማውጣት ሲሄድ ያስረዱታል፤ እኔ ግን ዜግነትንና ጎሰኛነትን አላነካካቸውም፤ ዜግነቴንም እንዲያው በዋዛ አላየውም፡፡
* ..የኤርትራና የትግራይ ዜጎች.. ያልኋቸው ኢትዮጵያውያን ካልሆኑና የዜግነት ግዴታ ከሌለባቸው ኃላፊነቱን ከየት አምጥቼ ጫንሁባቸው?
* ገብሩስ የኢትዮጵያ ዜግነታቸውን ተገፈፉ ብሎ ወደቁጣና ወደመከፋት ያመራው ዜግነታቸውን ከዜግነታቸው ግዴታ እንዴት ለይቶ ነው?
የዜግነት መብትና ግዴታ በእያንዳንዱ ግለሰብ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ ነው፤ ዘርን ወይም ጎሳን ከዜግነት ጋር ማገናኘት ግልጽ ስህተት ነው፤ በ1969 ሶማልያ ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ አንድ የትግራይ ዜጋ በራሱ ፈቃድና ወጪ አዲስ አበባ መጥቶ ለመዝመት መወሰኑን በቴሌቪዥን አይተናል፤ የኢትዮጵያ ዜጋ ስላላልሁት በተግባር የገለጠውን የዜግነት ግዴታ ይፍቀዋል የሚል የጎሳ ህመም የያዘው ብቻ ነው፡፡
እጅግ የሚያስደንቀውና ከገብሩ በጭራሽ የማልጠብቀው የቼኮዝላቫኪያውን ጸሐፊ የሀበሻ ጀብዱ የሚለውን መጽሐፍ ገና ሳያነብበው መጥላቱ ነው፤ እኔ ሰውዬውን ጎበዝ በማለቴም የተበሳጨ ይመስላል፡፡
..የትግሬ ሽፍቶች.. በሚለውም ጥቅስ ተበሳጭቷል፤ የእሱ መበሳጨት አንሶ ሌሎችን ለመቆስቆስ ..በዚህ አባባልዎ ብዙዎች ዜጎችን ሳያስከፉ እንዳልቀሩ ሳልጠቅስ ለማለፍ አልፈልግም.. ይላል፤ ብዙ ሰዎችን የሚያስከፋው አባባሌ ምን እንደሆነ የታሪክ ፕ/ሩ አልተናገረም፤ የእኔን ጽሑፍ ያላነበበ ሰው አንድ መጥፎ ነገር የተናገርሁ ይመስለዋል፤ እኔ ያልሁት ስላልተጠቀሰ አንባቢው የራሱን ፍርድ ለመስጠት እንዳይችልና የገብሩን ፍርድ ብቻ ተቀብሎ መስመር እንዲይዝ ይጋብዘዋል፤ ከገብሩ እኔ የምጠብቀው አንደኛ ምንም ያህል ቢያስከፋ እውነትን ለመቀበል ዝግጁ መሆንን ነበር፤ ሁለተኛ ፀሐፊው የጠቀሳቸውን የትግሬ ሽፍቶች ለትግራይ ህዝብ በሙሉ ማልበስ አጉል ጎሰኛ አስተሳሰብ ነው፤ ትዕግስትና ፍላጐት አድሮበት መጽሐፉን ቢያነብበው የራስ ስዩምም ጦር ከራስ ካሣ ጦር ጋር ተሰልፎ ሲዋጋ እንደነበረ መረዳት ይችል ነበር፤ በህገ ኀልዮት (ሎጂክ) ለጥቂቶች የተነገረውን ለጠቅላላው ማልበስ ልዩ ስም ያለው የአስተሳሰብ ጉድለት ነው፤ ነገር ግን ፕ/ር ገብሩ በዚህ በህገ ኀልዮት ስሀተቱ እኔን ለማቄል ..በሽፍቶች አሳበው መላውን ትግሬ ለመፈረጅ ነው የሚል እሳቤ የለኝም ይላል፤.. እንኳን ይቺንና የዝንብ ጠንጋራ እናውቃለን ሲባል አልሰማም መሰለኝ..
በፍትህ ጋዜጣ ከአቶ ስብሓት ነጋ ጋር የተጀመረው ክርክር በአንድ ጉዳይ ላይ ነበር፤ ከዚያ ክርክሩ እየወረደ የጎሳ ሽታ ይዞ መጣ፤ የኔ የመጨረሻ ጥረት ይህንን የጎሳ ሽታ ለማስወጣት ነበር፤ ሐጎስ እርገጤ ሌባ ነው ሲል በላቸው የሚናደድ ከሆነ፣ እርገጤ ሐጎስ ሌባ ነው ሲል ጥዑም የሚናደድ ከሆነ እንደሰዎች ለመነጋገር የምንችልበት ጊዜ አልደረሰም ማለት ነው፤ በግላችንም ሆነ በህዝብነታችን የሚያዳክመን አጉል መሸፋፈንና ድብብቆሽ ነው፤ እውነቱን ለማወቅና እውነቱን ለመናገር ድፍረቱን ከአገኘን ሳንጎዳዳ እንደልብ ለመነጋገር እንችላለን፤ ለጋዜጦቹም ሆነ ለአንባቢዎች አንድ ለመግባቢያ የሚረዳን ሀሳብ ላቅርብ፤ INTERNET ውስጥ ገብተን LOGICAL FALLACY ብለን ብንጠይቀው በምንነጋገርበትም ጊዜ ሆነ በምንጽፍበት ጊዜ ሊረዳን የሚችል ትምህርት የምናገኝ ይመስለኛል፤ በገለባ እየለወጥን የምናውቀውንም የማናውቀውንም እያደባለቅን ብንነታረክ ዋጋ የለውም፤ ከዚያም በላይ እያንዳንዳችን ተምረናል፤ አውቀናል፤ ብለን በውስጣችን ያለውን መርዝ ከምንነዛው በውስጣችን ይዘነው እኛኑ እንዳደረገ ያድርገን፡፡
The fact that Menelik spoiled Ethiopia cannot be denied. I once read a book entitled “Ethiopia at Bay” written by an American who worked for so long as Foreign Affair officer for Emperror Hailesselassie. He states that “… after reuniting Eritrea with Ethiopia, the Emperor sailed Assab along with his stuff and I can read the satisfaction he felt from correcting what Menelik mangled.”
So, let there be no doubt about Menelik’s poor leadership which resulted from his provincial way of thinking. A lot of other accounts state Menelik’s feared that Eteget Taytu and Alula Abanega(both from ‘semen’) would conspire and took his throne if he emancipated Eritrea. May be this was his paranoia or may be it was true but a leader who thinks his throne to be more important than his country is definitely as stupid as professor Mesfin.
Good articles. The old Amhara professor always talks rubbish and should not be taken seriously. He can say what ever he likes, but the fact is that Menelik and to a lesser extent Haileselasie are responsible for the separation of Eritrea. Tigrians simply saved Ethiopia from total disintegration.
በሽተኛ ካድሬ::
you only read and extract what you want.
Keep up buddy.
For you, there is only one way. Woyane and it’s racist way like you emotioally and ethinically attached; and for the extrimist opponant ( by the way don’t be glad you are extrimist too. But extrimist supporter) they only see what your favorite guy made a mistake.
Way to go guys. Kill this great country. You for your bread (and hate of Ethiopians and ቂጥ ላሺነት) and others to their hate of your man.
What I’m saying is read accordingly. I read all of them starting from your crazy racist old man sebhat and prof. Last article too.
Don’t rush for spin…..y**
If Menelik was in the Arada Giyorgis Church (Addis Ababa) in the morning of Yekatit 23, how was he able to travel 900km to Adwa and “participate” in the battle – actually it is to hide?