“አህያ!” – “ደደብ፥ ደነዝ፥ የማይገባው” ለማለት፣ “በቅሎ አባትሽ ማን ነው ቢሏት አጎቴ ፈረስ ነው አለች” – ለአህያ ያለንን ዝግተኛ ግምት ያሳያል፣ “አህያ ሰባ ምን ሊረባ” – የአህያ ሥጋ እንደማይበላ ይጠቁማል፣ …ወዘተ። እድሜ ለአለም አቀፉ የገበያ ትስስር (Globalization)፣ በሀገራችን ክብር የተነፈጋት እና ዝቅተኛ ግምት የመሚሰጣትን አህያ የሚፈልግ እንግዳ ከሩቅ ምስራቅ ድረስ መጥቷል። የአህያን ሥጋ ቬትናሞች ለምግብ፣ ቻይናዎች ደግሞ ቆዳዋን ለመድሃኒት በጥብቅ እየፈለጉት እንደሆነ ሰሞኑን ተሰምቷል። ስለዚህ፣ እኛ የማንፈልገውን ፈልጎ ደጃፋችን ድረስ የመጣን እንግዳ በአግባቡ ማስተናገድ እንጂ ሌላ ሁኻታ መፍጠር ተገቢ አይመስለኝም።
በመጀመሪያ ደረጃ ነገሩ ሀገራዊ ብቻ ሳይሆን ዓለም-አቀፋዊና አህጉራዊ ጭምር እንደሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል። በእርግጥ የአህያ ሥጋ ከቬትናም በተጨማሪ በቻይና እና አንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት ጭምር ለምግብነት እንደሚውል ይታወቃል። ነገር ግን፣ አህያን በጣም ተፈላጊ ያደረጋት ከሥጋዋ ይልቅ ቆዳዋ ነው። በቻይና የአህያ ቆዳ በጣም ተፈላጊ ነው። ምክንያቱም፣ ቻይናዊያን የአህያን ቆዳ በመቀቀል ከውስጡ ¨gelatine” የተባለ ንጥረ ነገር የሚያመርቱ ሲሆን ይህ ደግሞ ”Ejiao” ለተባለው የቻይና ባህላዊ መድሃኒት ዋና ግብዓት ሆኖ ያገለግላል።
በቻይና የአህያ ቆዳ ተፈላጊነት እንዲጨምር ያደረገው መካከለኛ ገቢ ያላቸው የሀገሪቱ ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ ፍጥነት መጨመሩና ስለ ”Ejiao” ፍቱን መድሃኒትነት በሚቀርቡ የማስታወቂያ ሥራዎች እንደሆኑ ዘገባዎች ያስረዳሉ። ዛሬ በቻይና አንድ ኪሎ ግራም “Ejiao” እስከ £300 ፓውንድ በሚደርስ ዋጋ ይሸጣል። በዚህ ምክንያት በቻይና የአህያ ቁጥር እ.አ.አ. በ1991 ከነበረበት በእጥፍ መቀነሱን ዘገባዎች ያስረዳሉ። በዚህ ምክንያት በዓለም አቀፉ ገበያ ውስጥም ከፍተኛ የሆነ የፍላጎትና አቅርቦት አለመመጣጠን ተፈጥሯል። ለዓለም ገበያ በአንድ አመት ውስጥ 1.8 ሚሊዮን የአህያ ቆዳ ለሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን ዓመታዊ የገበያ ፍላጎቱ ግን 4 እስከ 10 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል ይገመታል።
የአህያ ቆዳ ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ ምክንያት፣ ለምሳሌ በቡርኪና ፋሶ የአንድ አህያ የመሸጫ ዋጋ እ.አ.አ. 2014 ከነበረበት 60 ዶላር ወደ 108 ዶላር ጨምሯል። እንደ ግብፅ፣ ደቡብ አፍሪካና ታንዛኒያ ባሉ ሀገራት ደግሞ አህዮችን ለቆዳቸው ሲባል በሕገወጥ መንገድ መስረቅና በየስርቻው ማረድ እንደተጀመረ አንዳንድ ሪፖርቶች ይጠቁማሉ። በአህያ ብዛት በአፍሪካ ቀዳሚ በሆኑት ኬኒያና ኢትዮጲያ ደግሞ በመንግስት እውቅና የተሰጠው የአህያ ማረጃ “ቄራ” ተከፍቷል።
ሰሞኑን ከወደ ቢሾፍቱ (ደብረዘይት)የተሰማው ዜና ከላይ የተጠቀሰው አለም አቀፋዊና አህጉራዊ እውነታ ጋር በቀጥታ የተያያዘ ነው። በዘገባው መሰረት፣ በቢሾፍቱ ከተማ በ80 ሚሊዮን ብር ወጪ “የአህያ ቀራ” መገንባቱ እና የአህያ ስጋና ቆዳን ወደ ዉጪ መላክ ሊጀመር እንደሆነ ተገልጿል። ከዚህ በተጨማሪ፣ ሌላ የአህያ ቄራ በኦሮሚያ ክልል፥ አርሲ ዞን፥ አሰላ አከባቢ በቻይናዊያን ባለሃብቶች እየተገነባ እንደሆነ ተጠቅሷል።
ከላይ የተጠቀሰው ዜና ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ መነጋገሪያ ርዕስ ሆኖ ሰንብቷል። “የአህያ ስጋና ቆዳ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ በሀገራችን ሊከፈት አይገባም”፣ “ፋብሪካው እንዲከፈት በመፍቀድ መንግስት የሀገሪቱን ሞራላዊ እሴት ጥሷል” እና የመሳሰሉት ዓይነት አስተያየቶች በስፋት እየተደመጡ ይገኛል። ከዚህ ጋር በተያያዘ፣ ከጥቂት ወራት በፊት በቢሾፍቱ የተገነባው ፋብሪካ የዚህ ዓይነት አመለካከት ባላቸው ሰዎች በእሳት ተለኩሶ እንደነበር ዘገባዎች ያስረዳሉ።
በእርግጥ የአህያ ስጋን አለመብላት መብት ነው። ሌሎች ሰዎች እንዳይበሉ መከልከል ግን ወንጀል ነው። በዚህ መሰረት፣ ከላይ የተጠቀሰው ድርጅት የተቋቋመበትን ዓላማና ተግባር እንዳያከናውን እንቅፋት መሆን ከሞራልና ኢኮኖሚያዊ መርህ አንፃር ተቀባይነት የለውም። ለዚህ ደግሞ ሦስት መሰረታዊ ምክንያቶችን መጥቀስ ይቻላል።
1ኛ) የጅብ ቆዳን እየገዛን የአህያ ቆዳ እንዳይሸጥ መከልከል
የአህያ ቆዳ በቻይና ተፈላጊ የሆነበት ምክንያት ለባህላዊ መድሃኒት ማምረቻ ግብዓት ሆኖ ስለሚያገለግል ነው። በቢሾፍቱ ከተማ የተቋቋመው ድርጅትም የአህያ ቆዳን ለዚሁ ገበያ የማቅረብ ዓላማ እንዳለው ተገልጿል። በተመሣሣይ፣ በተለያዩ የሀገራችን አከባቢዎች የጅብ ቆዳ እና የጃርት ስጋ ለባህላዊ መድሃኒት እንደሚውሉ ይታወቃል። ስለዚህ፣ እኛ በሀገራችን የጅብ ቆዳን ለባህላዊ መድሃኒትነት እየተጠቀምን ቻይናዎች የአህያ ቆዳ ለተመሣሣይ ዓላማ እንዳያውሉ መከልከል በፍፁም አግባብ ሊሆን አይችልም።
2ኛ) የበሬ ስጋን የሚበላ የአህያ ስጋን መከልከል አይችልም
ኢትዮጲያ ውስጥ የበግና የበሬ ስጋ ተወዳጅ እንደሆነ ሁሉ ቬትናም ውስጥ የአህያ ስጋ ተወዳጅ ነው። በቢሾፍቱ የተቋቋመው ድርጅትም የአህያ ስጋን ለሀገር ውስጥ ገበያ ሳይሆን ለቬትናም ገበያ የሚያቀርብ ነው። የገና እና ኢድ በዓል በመጣ ቁጥር በሬና በግ በየመንገዱና በየሰፈሩ የሚያርድ ማህብረሰብ ዘመናዊ የአህያ ቄራ በመቋቋሙ ምክንያት የሚያጣው ነገር ምንድነው?
እውነት ለመነጋገር፣ እስኪ በየከተማው ያሉ ሥጋ (ሉካንዳ) ቤቶችን ልብ ብላችሁ ተመልከቷቸው። ከምግብ ቤት ይልቅ የሰው ልጅ ጭካኔ ማሳያ እኮ ነው የሚመስሉት። የቤት እንስሳት ያለ ርህራሄ አካላቸው ተተልትሎና ተጨፍጭፎ ወደ ተሰቀለበት ሉካንዳ ቤት ሄደን ለመብላት ዘወትር የምንጎመዥ እኮ ነን። ቀን በወጣና በገባ ቁጥር የበሬ፥ በግ፥ ፍየልና የዶሮ አንገትን ያለ ርህራሄ በቢላ ስንቀነጥስ፣ ስጋቸውን ስንበላና አጥንታቸውን ስንግጥ ያልነበረ የሞራል ስብዕና ዛሬ “አህዮች በዘመናዊ ቄራ ታርደው ሥጋቸው ወደ ቬትናም ሊላክ ነው” ሲባል ከወደየት መጣ? በአጠቃላይ፣ እኛ የበሬን ስጋ እየበላን ቬትናሞች የአህያ ስጋን እንዳይበሉ መከልከል አንችልም።
3ኛ በአህዮቹ ላይ የመወሰን ስልጣን ያለው አርሶ አደሩ ብቻ ነው
አብዛኛው የኢትዮጲያ አርሶ አደር አንድ ውሻና አህያ ከቤቱ አይጠፋም። ምክንያቱም፣ እነዚህ ሁለት እንስሳት ከአርሶ አደሩ ኑሮና አኗኗር ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያላቸው ናቸው። አርሶ አደሩ በተለይ አህያን ለገበያ የሚያቀርበው ወይ ሌላ ትርፍ አህያ ስላለው ነው አሊያም ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ስላጋጠመው ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ በጤና እና እድሜ ምክንያት አገልግሎት የማይሰጡ አህዮች ሲሞቱ ጠብቆ ለጅብና ጥንብ-አንሳ ከመስጠት በስተቀር ሌላ አማራጭ የለውም። በአጠቃላይ፣ አህዮችን ከአንድ ቦታ ገዝተው ወደ ሌላ ቦታ ወስደው ከሚሸጡ ነጋዴዎች በስተቀር አርሶ አደሩ አህያን አርብቶ ለገበያ የማቅረብ ልምድ የለውም።
ይህ “አህያ ሰባ ምን ሊረባ” ከሚለው የሞራል እሳቤ በተጨማሪ የእንስሳቱ የውልደት መጠን በጣም ውስን በመሆኑ ለእርባታ ምቹ አይደሉም። ነገር ግን፣ የአህያ ስጋና ቆዳ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ በቢሾፍቱ ከተማ መቋቋሙ አርሶ አደሩ አህያውን በተሻለ ዋጋ እንዲሸጥ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርለታል። በጤና እና እድሜ ምክንያት አገልግሎት መስጠት የማይችሉ አህዮችን ተንከባክቦ ለገበያ የማቅረብ እንዲችል እድል ይፈጠርለታል። በዚህም ለጅብና ለጥንብ-አንሳ ይተወው ከነበረው የአህያ ሥጋና ቆዳ ተጨማሪ ገቢ ያገኛል። በዚህ መልኩ አርሶ አደሩ አህያውን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሊሆን ይችላል።
በተቃራኒው፣ ይህ ተግባር “ከእምነቴና ሃይማኖቴ ጋር አብሮ አይሄድም። ስለዚህ አህዮቼን ለድርጅቱ አልሸጥም” ካለም መብቱ ነው። በአህዮቹ ላይ የመወሰን ስልጣንና መብት ያለው አርሶ አደሩ እንጂ የተወሰኑ የከተማ አፈ-ጮሌዎችና የሃይማኖት ሰባኪዎች አይደሉም።
በአጠቃላይ፣ የእኛ ባልሆነ ንብረት ላይ የማዘዝ ስልጣንና መብት የለንም። ስለዚህ፣ አህዮቹን ለቄራ የመሸጥና ያለመሸጥ ውሳኔን ለአርሶ አደሩ መተው አለብን። ከዚህ በተጨማሪ፣ እኛ የጅብ ቆዳን ለባህላዊ መድሃኒት እንደምንጠቀመው ሁሉ ቻይናዎችም የአህያ ቆዳን መጠቀም ይችላሉ። በተመሣሣይ፣ እኛ የበሬ ስጋ እየበላን ቬትናሞች የአህያ ስጋን እንዳይበሉ መከልከል ደግሞ ተገቢ አይደለም።
*********
እንቶፈንቶ የወያኔ የተለመደ አስተያየት ነዉ፣፣ አህያ ሰዉ ብትሆን ሲጀምር ተንቀሽ ተረግጠሸ፣ ስትንቋሸሺ ብሎ የህወሀትን ያዞ እንባ ወሬ ጀምሮ መደምደሚያዉ ግን ሸጨ ልጠቀም ነዉ፣፣አሁን ግን እድሜ ለአለም አቀፍ ገበያ ክብር አገኜች፣፣ ልክ እድሜ ለህገ መንግስቱ ብሄር ብሄረሰቦች ክብር አገኙ እንደሚሉት፣፣ የተለመደ የማታለል አስተያየት ነዉ፣፣ መጀመሪያ ቄራዉ ያረጁ ገበሬዉ የማይጠቀምባቸዉን አህዮች ሳይሆን ሁሉንም አህያ ነዉ የሚያርደዉ፣፣
ሁለተኛ የሀገሩን ባህል ክብር፣ የሰዉን ፍላጎትና አስተያየት ሳያከብር ለቤትናምና ቻይና ጠበቃ ሆነ
ሶስተኛ ገበሬዉ የአህያ ኢኮኖሚዊ ጠቀሜታዉ ተሸጦ ከሚገኘዉ ገንዘብ በላይ ነዉ፣፣ አህያ ሁሉ ነገር ናት ለገበሬዉ
አራተኛ ቄራዉ በደብረ ዘይት ብቻ በአመት እስከ 100,000 አህዮችን ለማረድ እቅድ አለዉ፣፣ የአሰላዉ ሲጨመር ምን ያክል እንደሚሆን መገመት ይቻላል፣፣ አህያ በጣም በትንሹ ከሚራቡ እንስሳት አንዷ ናት፣፣ በአጭር ግዜ ከሀገሪቱ ዉስጥ ትጠፋለች ማለት ነዉ፣፣ ለገበሬዉ የሚያመጣዉን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት መገመት ቀላል ነዉ፣፣
አምስተኛ በሬና በግን በጭካኔ የሚያርድ ማህበረሰብ የሚል ሰንካላ አመክንዮ አምጥቷል ለመሆኑ ቻይናወቹ አህያን የሚያርዱት ራሷን ቅቤ እየቀቡ፣ ክላሲካል ሙዚቃ እያሰሙ እሹሩሩ ብለዉ አስተኝተዉ ነዉዴ
ሰንት ቆንጆ እያለ ይህቺን እቀያሚ አህያ መለጠፍህ የምርጫ ችግርህን ያሳያል፡፤በነገራችን ላይ ደሳለኝ የሚባል አህያ ነበር ሲባል የሰማሁ መሰለኝ እሱ ይሁን እንዴ?
ይህ ህዝብ ወግና ባህሉ ከሀይማኖቱ ጋር ተቀላቅሎበታል።የፖለቲካ ሳይሆን የባህል ኣብዮት ያስፈልገዋል።
Quiet a nonsense, What kind of argument is it, to say “you use a hyena skin for folk medicine, so Vietnamese can use donkey skin for folk medicine”. Of course, Vietnam has the right to use in their own country, but do they have a privilege, If I am not willing to allow slaughter in my backyard? Will Americans allow slaughtering dogs in their country? Will Saudis allow eating pork in their country? But, we all know all countries cannot interfere in other countries interest, when it comes to eating habits.
Misappropriated comment. What Seyoum Teshome is talking about and your comment is totally different. Talk always as contextual as possible. Never be hasty to mention the name brave TPLF for all evil intentions. TPLF never came by writing hate words rather paid many sacrifices for the whole 17 years armed struggle in the ground. Go to CIA and MI6, ask them to help you in removing TPLF and you will hear what will be their answer. CIA never been played critical role on liberating our territory rather they inclined by the end of the day to the winners. Thus, made yourself committed to pay all the sacrifices including your life, and then you will see how much it is very destructive and bitter for the people. Never pray to get power by simply defaming TPLF, which will never happen. Never again Emperors in the heart of Ethiopia. Nightmare.
There is a British saying. “If wishes were horses, beggars would ride them.” I Wish Emperor Tewodros was born again to unite Ethiopia.But, it is impossible. We can not deny history. Although Mengistu is a dictator, he had exerted all his efforts to protect the territorial integrity and unity of our motherland. Thanks to the support rendered by CIA and MI6, EPLF and TPLF have controlled the the Ethiopian political power. Look, ELF was the first Established guerrilla group to separate Eritrea from Ethiopia. Because of its Arabic ideology, CIA dismantlement it. I can mention names of many liberation movements languished by the CIA. So long as the TPLF serves the interests of CIA believe me, It can stay in power for a long period of time. If I were you, before I start my struggle, I would assess the political environment and set the right tactic and strategy to defeat my enemy. Emotional struggles engulf the lives of innocent citizens.