ይድረስ ለክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እና ለተከበሩ የአማራ ብሄራዊ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው
በወልድያ እና በቆቦ በፀጥታ ሃይሎች እርምጃም ይሁን በዘረኛ መንጋዎች ጥቃት ለደረሰባቸው ሁሉም ዜጎች የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘን በቅድሚያ እየገለፅኩ ለቤተሰቦቻቸዉና ለሁላችንም መፅናናትን እመኛለሁ። አስፈላጊ ማጣራትና ምርመራ ተደርጎ ከሁሉም ወገን መጠየቅ ያለበት አጥፊ መጠየቅ አለበት እላለሁ፡፡ ያንዱ ጥቃት የሁሉም ስጋት ነው ብየ የማምን ሰላማዊት፣ የበለፀገች፣ ዴሞክራስያዊት ኢትዮጵያ እና ምክንያታዊና የሞራል ስብእና የተላበሰ ህዝብ ያላት ሀገር እንድትገነባ የምሻ ዜጋ ነኝ። የከዚህ በፊት ተሳትፎየም መነሻና መድረሻው ይህ መሆኑ እሙን ነው።
በዓለም አቀፍ የዘር ማጥፋት ወንጀል ህግ እና በተባበሩት መንግስታት የሽብር ወንጀል መረዳት መሰረት ዘር ተኮር የሂወትና የንብረት ጥቃት እንዲሁም የዘር ማጥፋትና (Genocide) የዘር ማፅዳት (Ethnic Cleansing) ወንጀሎች በምንም ዓይነት አመክንዩ ተቀባይነት ሊኖራቸው እንደማይችል ይደነግጋል። Justifiable ድርጊት አይደለም። ኢትዮጵያም እነዚህን ህጎች አፅድቃ የህጓዋን አካል ያደረገች ሀገር መሆንዋ ይታወቃል።
በተጨማሪም ከ አስራ ሰባት ዓመት የእርስ በርስ ጦርነት በኃላ ትፈርሳለች፣ አብቅቶላታል፣ እንደ ሶቭየት ህብረት ትበተናለች የተባለችዉኢትዮጵያ የሁሉም ብሄር ቤት ትሆን ዘንዳ ብዝሃነትን መሰረት ያደረገ ፌዴራላዊ ስርዓት በማቆም ህዝቦች በማንነታቸው ጥቃት እንዳይደርስባቸው የሚደነግግ ሕገ-መንግስት በዝቅተኛ ደረጃም ቢሆን ተግባራዊ ማድረግ የጀመረች ሀገር ናት ኢትዮጵያ።
አሁን በወልድያና በቆቦ እየተደረገ ያለው ነገር ሀ-እና-ለ የሌለው ዘር ተኮር ጥቃት በዓለም አቀፍ የዘር ማጥፋት ወንጀልም፣ በሕገ መንግስታችንም ከፍተኛ ደረጃ የሚይዝ የህግና የፖለቲካ ወንጀል ብቻ ሳይሆን የሞራል ዝቅጠትም ማሳያ ነው። ይህ ድርጊት በምንም ዓይነት መንገድ አመክንዮ (Justification) የሚቀርብለት ጉዳይ አይደለም። እምንበታተነው ብሄራዊ ማንነት የኩራት ሳይሆን የጥቃት ምንጭ የሆነ እለት ነው።
የክልሉ መንግስት ምን እያለ ነው?
አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የችግሩ መንስኤ የብአዴን ችግር እንደሆነና ከመልካም አስተዳደር እና ከተመሳሳይ ነገሮች የሚመነጭ እንደሆነ እንደተናገሩ ሰምተናል። ልክ ነው ወልድያም፣ ጎንደርም፣ መቐለም፣ ቆቦም፣ ወለንጪቲም ብቻ አብዛኛው የኢትዮጵያ አካባቢዎች የአስተዳደር ችግር አለ። ይህ ማለት ግን በንፁሃን ዜጎች ላይ፣ ለዛዉም ክልሉን በማስተዳደር ምንም ተሳትፎ በሌላቸው ዜጎች ላይ እርምጃ ለመዉሰድ ምክንያት ይሆናል ማለት አይደለም። የወልድያን ወጣት ያስለቀሰው የከተማው የብአዴን አመራር እንጂ አብረሀት የተባለች ጉሊት ቸርቻሪ አይደለችም።
አቶ ገዱ ይህን ትግራዋይ ላይ በብሄራዊ ማንነቱ ምክንያት እየደረሰበት ያለዉን የዘር ጭፍጨፋ ድርጊቱን በሚመጥን ቃል ሊኮንኑት ይገባል። ዘር ተኮር ጥቃት ዓለም አቀፍ የዘር ማጥፋት ወንጀል እንደሆነና የፌዴራል ስርዓታችን የመጨረሻው ቀይ መስመር መሆኑ ተገንዝበው ድርጊቱን በምንም ምክንያት እና አመክንዩ ተቀባይነት ሊኖረው የማይደረግ መሆኑ ተገንዝበው በማያሻማ አገላለፅ ሊኮኑኑት ይገባል። ይህ ማለት ለክልላቸው ህዝብና መንግስት ተመሳሳይ ድርጊት እንዲታገሉም አቅምና ስልጣን መስጠት ማለት ነው።
የክልሉ መንግስት መኮነን ብቻ ሳይሆን ይህን የወንጀሎች ሁሉ ቁንጮ ወንጀል የሆነዉን የዘር ማጥፋት ወንጀል ለመከላከል ምን እንደሰራ፣ ምን ዉጤት እንዳስገኘ፣ ምንስ እያደረገ እንደሆነና፣ በሌሎች የክልሉ አካባቢዎች እንደማይፈጠር ምን ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ በይፋ ለህዝቡ ማሳወቅ አለበት። የክልሉ መንግስት “አይ እየተፈፀመ ያለ ጥቃት ዘር ተኮር አይደለም” እሚል ከሆነም በግላጭ አቛሙን ያሳዉቅ። አብሮ የሚያኖረንን የብዝሃነት መስመር እየተጣሰ አንድ ሃገር ብሎ ነገር የመኖር እድሉ የኮሰመነ መሆኑ የዘርፉ ሳይንስም ዓለማዊ ሃቁም ይነግረናል።
የተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስቴር
የፌዴራል መንግስትም ፌዴራላዊ ስርዓቱንና ሕገመንግስቱን የመጠበቅ፣ የህዝቦች የግልና የቡድን መብቶችን የመከላከል ሃገሪትዋን ከመፍረስ የማዳን ግዴታ እንዳለበት ተገንዝቦ እየተፈጠረ ስላለው ሁኔታ ያለዉን መረዳት (Understanding of the problem) ፣ ያደረገው ተግባራዊ እንቅስቃሴ ፣ እንዲሁም የወደፊት እቅዱን በይፋ ለህዝቡ ማሳወቅ አለበት። መንግስት በቦታው እንዳለ ማሳወቅ አለበት፣ ዜጎች በሃገራቸው የመኖር መብታቸው በቦታው እንዳለና የመኖር ዋስትና እንዳላቸው እርግጠኛ መሆን ይሻሉ።
ስለዚህም የዘር ማጥፋት ወንጀል በዓለም አቀፍ ህግም ይሁን አብሮ ያኖረናል ብለን ባፀደቅነው ሕገ መንግስታችን መሰረት በአመክንዮ ሊስተባበል የሚችል ወንጀል እንዳልሆነ ተገንዝበው የአማራ ክልል መንግስት እና የፌዴራል መንግስት ድርጊቱን በስሙ ጠርተው በፅኑ እንዲኮንኑና፣ ይህን ወንጀል ለመከላከል የሄዱበት ርቀት ገልፀው፣ ድርጊቱ ዳግም እንዳይደገም እየሰሩት ያለን ስራ ለህዝቡ በይፋ በመግለፅ መንግስታዊ ኃላፊነታቸው ሊወጡ በሚችሉበት የአመራር ቁመና እንዳሉ በማሳየት ህዝቦች አሁንም ኢትዮጵያ እምትባል ተማምነው የሚንቀሳቀሱባት ሀገር እንዳለቻቸው ማሳየት ይገባቸዋል።
በሰው ሂወት ክቡርነት የሚያምን ሁሉ ሼር እንዲያደርገው እጠይቃለሁ።
*******
በታሪክ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጻሚ በስልጣን ላይ ያለ ዘር ብቻ መሆኑ ከሩዋንዳ እና ከሂትለር ጭፍጨፋ መረዳት ይቻላል፡፡ ስልጣን ላይ የሌለ ዘር ጄኖሳይድ መፈጸም አይችልም፡፡ በታሪክም አልተመዘገበም፡፡ በአሁኑ ጊዜ በአማራ እና ኦሮሞ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጥፋት ወንጀል ስልጣን በያዙ በትግራይ አጋዚ ወታደሮች የተፈጸመ ነው፡፡ በቅርብ ጊዜ በወልድያ፣ ቆቦ፣ መርሳ፣ ባህርዳር፣ ጎንደር እንዲሁም ቀደም ሲል በጨለንቆ፣ ነቀምት፣ ሻምቡ፣ ሀረርጌ፣ ጅጅጋ፣ ወዘተ… በመሳሰሉት ቦታዎች በስናይፐር ጥይት ተደብድበው የሞቱትት ህጻናት፣ ሴቶች እና ወጣቶች አማራዎች እና ኦሮሞዎች እንጂ ትግሬዎች አይደሉም፡፡ 99 ፐርሰንት ትግሬዎች በሚመሩት ሠራዊት እና በኣጋዚ (ትግሬ ወታደር) አልሞ ተኳሽ በሆኑ ልዩ የትግራይ ኃይሎች የሚፈጸመውን የዘር ማጥፋት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሳይቀር ተገንዝቦ ለሠራተኞቹ ማስጠንቀቂያ እየሰጠ ነው፡፡
እስካሁን በመከላከያ ሠራዊት (አጋዚ) ስናይፐር ተመቶ የሞተ አንድም ትግሬ በሌለበት ሁኔታ በትግራይ ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል የተፈጸመ ለማስመሰል መሞከር የቁራ ጩሀት ነው፡፡ ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሀል እንደሚባለው ዳንኤል ብርሀኔ እና የህወሀት ተከፋይ ብሎገሮች ልብ አውልቅ ልፈፋ የሚያሰሙት ህዝቡን ለማደናገር እንጂ አውነቱን አጥተውት አይደለም፡፡ ይልቁን ትግሬዎች የሚፈጽሙትን የዘር ማጥፋት ወንጀል በማስረጃ አስደግፎ ወደ ዓለም አቀፍ የጦር ወንጀል ፍርድ ቤት ለመውሰድ ዝግጅት ማድረግ የጠንካራ ኢትዮጵያውያን መለያ ነው፡፡
ኣንድ መንግስት በሂደቱ ብዙ ጥሩና መጥፎ ነገሮች ሊፈፅም እንደሚችል ማንም ኣይዘነጋውም። ኢሕአዴግም ቢሆን ከዚህ ሊርቅ ኣይችልም። ኢሕዴግ በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ ለሚፈጠሩ ችግሮች የመጀመርያ ተጠያቂ መሆኑ ማንም ይስማማበታል ብዬ ኣምናለሁ። ስለዚህ የመልካም ኣስተዳደር እጦት ጥያቄ ያለበት ማንኛዉም ወገን መንግስትን መጠየቁ፣ እሚሰማው ካጣ መቃወሙና ገፋ ቢል እስከ ኣመፅ መሄድ የሚያጋጥም እውነታ ነው ። ነገር ግን ይህንን ምክንያት ወይ ሰበብ በማድረግ በማይመለከተው ወገን ወይ እሱም በዚህ ችግር ምክንያት ተጎጂ በሆነን የህዝብ ኣካል ጥቃት መሰንዘር ማለት በምላሹ የከፋ ኣፀፋ መቀበል መሆኑን “ኣቶ Ab Alemu” የሚያጡት ኣይመስለኝም። እንደኔ ከሆነ ገልቱ ዘረኛ! የመለው እሚገልፀው እርሶን ነው። ምክንያቱ ማሰብ ብቺሉ ኖሮ በሚድያ ካፖርት ተደብቀው ይህንን ኣፀያፊና ኢትዮጵያዊ ያልሆነ የከረፋ ኣስተሳሰቦትን ባላመለጦት ነበር። እትዮጵያ ሁላችን ኣብረን የምንኖርባትና የምንመካባት ኣገር እንጂ እንደ Ab Alemu” ያሉ የኣመለካከት ድሃ የሚዘባነኑባትና እንደፈለጋቸው የመተፉባት ኣገር ልትሆን ኣይገባም፤ ማንምምም ኣይፈቅድም። ያ ኣቶ Ab Alemu” የፎከሩበት ህዝብ በደል በዝቶበት ከተነሳ ምን ማድረግ እንደሚችል ስለሚያውቁት እኔ መንገር ኣይጠበቅብኝም። እሚያዋጣው ሁላችንም ተባብረን ለሚያጋጥሙ የኣስተዳደር በደሎች መጠየቅና መታገል እንጂ የርሶንና መሰሎችዎ ኣይነት መንገድ ፈፅሞ ኣያዛልቅም። ውጤቱም እጅግ የከፋና እርሶ ከሚያስቡት የተገላቢጦሽ ነው። ስለ ኢትዮጵያ ኣንድነት እሚታገል ካለ እኔ ማንም የለም እያለ ከሚያላዝን ወገን በዘር ላይ ካነጣጠረ ዳፋው በርሱ እንደሚሆን ኣይጠራጠሩ። የትግራይ ህዝብ ከሆነ የርሶ ጠላት ለምን ራስዎ ግልፅ ኣድርገው እንደ ዘመዲችዎ እኒ ካልገዛሁህ ኣትኖራትም በሚል የተለመደ ባዶ ፉከራ ታጅበው ብረት ኣንስተው ብቅ ኣይሉምና ኣይሞክሩትም፤ የፈሪ ዱላ ከመወርወር ስለሚሻልና በውጤቱም ስለሚማርበት።
ለዚህ ነገር ዋናው ተጠያቂ ማንም ሳይሆን ሕወሐት-ወያኔ መሆኑን መዘንጋት አይገባም። ደብዳቤ ሊጻፍ የሚገባውም ለሕወሐት-ወያኔ ብቻ ነው። በአገራችን አንድ ጥሩ አባባል አለ። “ጉድጓዱን ስትቆፍር አታጥልቀው የሚገባበት አይታወቅምና” ይባላል። የዘር ልዩነቱን፣ ጠባብነቱን፣ በጎጃጀሉን፣ ወዘተ ያመጣው ሕወሐት ነው። ሕወሐት ለከፋፍለህ ግዛው ይጠቅመኛል ብሎ ያመጣው ጠባብነት በአማራው ሕዝብ ላይ ሲፈጸም እንደ ድራማ ይቆጠር ነበረ። አሁን ግን ሕወሐት ራሱ ያስፋፋው ዘረኛነትና ሕወሐት በተዘዋዋሪ ዘረኛነትን ያስተማራቸው ሰዎች ሕወሐታዊ ዱላውን የዘር ጥላቻ ዓላማቸውን ሊያራምዱበት ሲሞክሩ እየታዩ ነው።
በጣም አስገራሚው ነገር ግን ሕወሐት-ወያኔ ይህንን በትግራይ ሕዝብ ላይ የሚቃጣውን የዘረኛነት ዱላ አጥብቆ ሲመኘውና ሲፈልገው የነበረ ነገር መሆኑ ነው። ሕወሐት-ወያኔ ዘወትር ለትግራይ ሕዝብ ሌላው ሕዝብ ጠላቱ እንደሆነ ሲሰብከለው ኑሯል፣ ሕወሐት-ወያኔ ከሌለች አማራውና ኦሮሞው ይውጡሀል ወደ ቀድሞው ባርነት ውስጥ መልሰው ይደፍቁሀል፣ ሕወሐት-ወያኔ ከሌለች የትግራይ ሕዝብም ሊኖር አይችልም እያለ ሲወተውትና በትግራይ ሕዝብ ጀርባ መሽጎ ሲመቸው ደግሞ በትግራይ ሕዝብ ትከሻ ላይ ሆኖ ዕድሜ ልኩን ለመግዛት እየቋመጠ ቆይቷል
አሁንም ሕወሐት-ወያኔ በትግራይ ሕዝብ ላይ ቀጥተኛ ዛቻና ማስጠንቀቂያ መሰል ጽሑፎችን ይዘው የሚወጡ በአገር ቤት የሚታተሙ መጽሔቶችንና ከውጭ እየታተሙ የሚመጡ መጽሐፍንት በዝምታ የሚመለከተው ለዚህ ስንኩል ዓላማው መሳካት ይጠቅማሉ ብሎ መሆኑ የታወቀ ነው።
ይህ ሁሉ የሚሆነው ሕወሐት-ወያኔ የ1968 ዓም ማንፌስቶውን እርግፍ አድርጎ ስላልተወው መሆኑን መገመት ይቻላል። ሕወሐት-ወያኔ የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያዊነቱ ዘወር ማድረጉ ሊሳካለት የሚችለው በዚህ ምንገድ ብቻ እንደሆነ እያለመ ነው። በዘረኛነት ተነሳስተው ምንም በማያውቁ የትግራይ ተወላጆች ላይ ጥላቻን የሚያራምዱ ሰዎችም በተዘዋዋሪ የሕወሐት-ወያኔን ዓላማ እያሳኩ መሆኑን ቆም ብለው ማየት ይገባቸዋል።
ሠላም የሁሉም ንፁህ አየር ነው የግል ጥቅም ከህዝብ አይበልጥም
ገልቱ ዘረኛ! ዘመዶችህ የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ደም (ከትግራይ በስተቀር፣ ምክንያቱም እናንተን ካሁን በኋላ ኢትዮጵያዊ ናችሁ ለማለት ስለሚያሳፍር ) 27 ዓመት ሲያፈሱት ዘር ማጥፋት የሚለው ቃል የት ነበር? በጉርብትና ስም ተጠግቶ እየሰለለ የንፁሃንን ደም የሚመጠውን ወያኔን መግደል የውጊያው ባህሪ ነው። ገና ገና ብዙ ዕዳ አለባችሁ። ያፈሰሳችኋት የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ደም ለዘላለም ትከተላችኋለች! አንድ ቆርቆሮ ወያኔ ሲገደል እየወጣህ እንደ ቁራ ከመጮህ እና Genocide የሚለውን ቃል አላግባብ ከመጠቀም ይልቅ፣ Tell your puppets to stop Amhara Genocide! Tell your puppets to stop Oromo Genocide! Tell your puppets to stop Konso Genocide! Tell your puppets to stop Gambella Genocide!
እኔ.ኢ.ህ.ዲ.ግ ክልሎችን እዳቋቋመ ከ አ/አ ከጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወደ ወልድያ ሆ/ል የአንድ እርከን የደሞዝ ጭማሪ, ቦነስ እና የአንድ ወር ደሞዝ ብድር እንዲሁም የመጒጔዣ ተከፍሎኝ(ቅድሚያ የመንግስት ቤት የማግኘትንም ይጨምራል) በወልድያ ሆ/ል ተመድቤ ስሰራ በጣም የገረመኝ እና የማልረሳው አጠቃላይ በሚባል ደረጃ ህዝቡ የመንግሰት ደጋፊ ነበር። እና ምን ያስደንቃል? የሚያስደንቀው ቢያንስ ለኔ ኢ.ህ.አ.ዲ.ግ አ/አ ተቀዋሚ ነበረው። ወልዲያ ውስጥ አማራውን ከ ትግራይዮ መለየት ሁሉ አይቻልም ነበር። ለምን እኛ(እኔ) ከ አ/አ የመጣነው ባለሙያዎች የኤርትራ መገንጠል ያንገበግብን ስለነበር በየተገኘው አጋጣሚ አንቃወም ነበር ነገርግን ህዝቡ ልክ እደ ታጋዬቹ ነበር ልክልክእችንን የሚነግረን። አሁን ከ ሀያስድስት ዓመት በኃላ ዘር አጥፊ መባሉ ግርምትን ቢፈጥርብኝ ነው ይህን ማለቴ!!!!