‘ህጉን ስናወጣ መጀመሪያ ሲጋራ ያቆሙት የክልሉ ፕሬዚዳንት ናቸው’ – ዶ/ር ሓጎስ ጎደፋይ

​የትግራይ ክልል ጤና ቢሮን ለዓለም-አቀፍ ሽልማት ያበቃው የትንባሆ ቁጥጥር እንቅስቃሴ ሲጀመር፤ ህጉን በማክበር እና ሲጋራ ማጨስን በማቆም አርአያ የሆኑት የክልሉ ፕሬዚዳንት አባይ ወልዱና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች እንደነበሩ ዶክተር ሓጎስ ጎደፋይ ገለጹ።

የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሓጎስ ጎደፋይ ይህን የገለጹ የሳቸው ቢሮ ከአለም ጤና ድርጅት (WHO) የአመቱ የትንባሆ ቁጥጥር ተሸላሚ (World Health Organization’s 2017 World No Tobacco Day Award) መሆኑን ምክንያት በማድረግ በተለይ ለሰናይት መብራሕቱ ባለፈው ረቡዕ በመቐለ በሰጡት ቃለመጠይቅ ነው።

በቃለመጠይቁ  ላይ ዶ/ር ሓጎስ ጎደፋይ:-

* የክልሉ ጤና ቢሮ ህጉን ለማስፈፀም ምን አይነት ተግባራትን አንዳከናወነ፣

* በህጉ ተፈፃሚነት ዙርያ የህብረተሰብ ተሳትፎው ምን ይመስል እንደነበረ፣

* አጠቃላይ የቢሮ እቅድ ተግባር እና ክንውን ምን ይመስል እንደነበር፣

* በቀጣይ ምን ለማከናወን እንደታቀደ እና

* ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

 የዶ/ር ሓጎስ ጎደፋይን ሙሉ ቃለምልልስ ከታች ባለው ቪዲዮ ወይም ይህንን ሊንክ በመጫን (link) ይመልከቱ።

********

Daniel Berhane

more recommended stories