የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በዲሲፕሊን ግድፈት ተቀጡ

    (ፋኑኤል ክንፉ)Semayawi Party Chairperson - Eng Yilkal Getnet

    የሰማያዊ ፓርቲ ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በሆኑት በኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ላይ የገንዘብ መቀጮ ሲጥል አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድን ከድርጅት ጉዳይ ኃላፊነት እንዲነሱ ውሳኔ ማስተላለፉ ተገለፀ።

    የሰማያዊ ፓርቲ ኢዲትና ኢንስፔክሽን ኃላፊ አቶ ብርሃኑ መሰለ በበኩላቸው የተወሰደ የዲስፒሊን እርምጃ መኖሩን አምነው ቅጣት የተላለፈባቸው አባላት የይግባኝ መብታቸው የተጠበቀ በመሆኑ አሁን ላይ ሆኖ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት እንደሚቸገሩ ገልፀውልናል።

    ኢንጅነር ይልቃል ባሳዩት ተደጋጋሚ የዲሲፕሊን ግድፈት መሆኑን ምንጫችን ጠቁሞ ግድፈቶቹ ምን እንደሆኑ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥቧል።

    ጉዳዩ የቀረበለት የፓርቲው ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ በሊቀመንበሩ ላይ የ500 መቶ ብር መቀጫ እንዲከፍሉ ኦዲት ኮሚሽኑ ውሳኔ አስተላልፎባቸዋል።

    እንዲሁም የፓርቲ ሚስጥር ለመገናኛ ብዙሃን አሳልፋ ይፋ አድርጋለች ተብላ ከሥራ አስፈፃሚ የታገደችው ሃና እና ሌሎች ተጨማሪ አባላት ከአንድ መቶ ብር እስከ ሰባት መቶ ብር መቀጫ የተጣለባቸው መሆኑን ለማወቅ ችለናል።

    *******

    ሰንደቅ፡- ጥቅምት 29፣ 2007

    Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

    more recommended stories