የሰማያዊ ፓርቲ ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በሆኑት በኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ላይ የገንዘብ መቀጮ ሲጥል አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድን ከድርጅት ጉዳይ ኃላፊነት እንዲነሱ ውሳኔ ማስተላለፉ ተገለፀ።
የሰማያዊ ፓርቲ ኢዲትና ኢንስፔክሽን ኃላፊ አቶ ብርሃኑ መሰለ በበኩላቸው የተወሰደ የዲስፒሊን እርምጃ መኖሩን አምነው ቅጣት የተላለፈባቸው አባላት የይግባኝ መብታቸው የተጠበቀ በመሆኑ አሁን ላይ ሆኖ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት እንደሚቸገሩ ገልፀውልናል።
ኢንጅነር ይልቃል ባሳዩት ተደጋጋሚ የዲሲፕሊን ግድፈት መሆኑን ምንጫችን ጠቁሞ ግድፈቶቹ ምን እንደሆኑ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥቧል።
ጉዳዩ የቀረበለት የፓርቲው ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ በሊቀመንበሩ ላይ የ500 መቶ ብር መቀጫ እንዲከፍሉ ኦዲት ኮሚሽኑ ውሳኔ አስተላልፎባቸዋል።
እንዲሁም የፓርቲ ሚስጥር ለመገናኛ ብዙሃን አሳልፋ ይፋ አድርጋለች ተብላ ከሥራ አስፈፃሚ የታገደችው ሃና እና ሌሎች ተጨማሪ አባላት ከአንድ መቶ ብር እስከ ሰባት መቶ ብር መቀጫ የተጣለባቸው መሆኑን ለማወቅ ችለናል።
*******
ሰንደቅ፡- ጥቅምት 29፣ 2007