የትግራይ ክልል ሰንደቅ አላማና የተቃዋሚዎች ፖለቲካ

የግንቦት 7 አሸባሪ ቡድን ዋና ፀሃፊ የነበረው አንዳርጋቸው ፅጌ በኢትዮጵያ የደህንነት ሃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉ በአገርውስጥም በውጭም ያሉ ደጋፊዎቹን ሲበዛ አበሳጭቷቸዋል፡፡

ይህ በኢትዮጵያ ሕግ በተደጋጋሚ ወንጀለኛ ተብሎየተፈረደበትና በፓርላማውም ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀ ድርጅት አመራር ልክ እንደ ነፃነት ታጋይ ተቆጥሮ “አንዳርጋቸውይፈታ” እየተባለለት በአንዳንድ የውጭ አገር ከተሞችም ሰልፍ እየተወጣለት ነው፡፡

በስዊዘርላንድ ከተማ በተካሄደውሰልፍ ላይ ታዲያ ሰልፈኞቹ የትግራይ ብሔራዊ ክልል ሰንደቅ አላማን ሲያቃጥሉ ተስተውለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ያሉ የቡድኑደጋፊዎችም ይህንኑ ድርጊት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ በመደገፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ ከዚህ ፅሁፌ ጋር በቀጥታስለማይገናኙ ሌሎቹን የድጋፍ አይነቶች ወደጎን ልበልና ላነሳው ወደፈለግሁት አቢይ ነጥብ ልግባ፡፡ Ethiopian oppositin burning Tigrai flag

የቀድሞ የአረና አባል የነበረውና አሁን ደግሞ የአንድነት ፓርቲ አባል የሆነው አስራት አብርሃም በዉጭ ያሉት እነዚህየግንቦት 7 አባልና ደጋፊዎች ባንዲራ የማቃጠላቸውን ተገቢነት በፌስቡክ ገፁ ላይ አስፍሯል፡፡ ለዚህም ምክንያትያደረገው ባንዲራው የትግራይ ሕዝቦች ሳይሆን የህወሃት ነው የሚል ነው፡፡ ቃል በቃል ያለው ይህንን ነው፡፡

“ሰሞኑን በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሰልፍ ላይ የህወሀትን ባንዴራ በማቃጠላቸው ምክንያትአንዳንድ የህወሀት ካድሬዎች “የትግራይ ህዝብ ባንዴራ አቃጠሉት” እያሉ ህዝቡን ያልሆነ ስሜትውስጥ ለመክተት እየጣሩ ነው። ለመሆኑ የህወሀት እንጂ የትግራይ ህዝብ የሚባል ባንድራ አለእንዴ? ሲጀመር ይሄ ባንዴራ የኮሚኒዝም ርዕዮተ ዓለም እንዲወክል ሆኖ ነው የተቀረፀው፤ በምንምዓይነት ከትግራይ ህዝብ ባሕልና ታሪክ ጋር የሚያገናኘው ነገር ያለ አይመስለኝም። ለወደፊትበሚኖረው ፌደራል ስርዓት ውስጥ የትግራይ ህዝብ በራሱ ምርጫ የሚውለበለብ የክልሉ ባንደራሊኖረው ይችል ይሆናል እንጂ ይሄ የትግራይ ህዝብ የሚወክል ባንዴራ አይደለም። በግርግርህወሀትና የትግራይ ህዝብ ማምታታት ይቅር! አንድን ህዝብ እንደ ህዝብ የሚያጥላሉቱን ለይተንመቃወም እንችላለን፤ ህወሀት ሲነካ በትግራይ ህዝብ ስም ለመከላከል መሞከር ግን ፍትሀዊአይደለም!”

ይህ ግለሰብ ያመነበትን ካሰፈረ በኋላ ብዙዎች ተቃውሟቸውን ገልፀውለታል፡፡ አብዛኞቹም ያጠነጠኑት በግለሰቡ እምነትላይ ነው፡፡ ይሁንና ይህ የአስራት አብርሃም አስተያየት ከግለሰቡ ተነጥሎ ከኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ ጋር ተሳስሮመታየት አለበት ብዬ አስባለሁ፡፡ ለዚህም ምክንያቶቼን አንድ ሁለት ብዬ በዝርዝር አቀርባለሁ፡፡

ከዛ በፊት ግን ስለሰንደቅ አላማው እኔ ያለኝን አረዳድ ላቅርብ፡፡ የኢፌዴሪ ሕገ መንግስት ስለ ሰንደቅ አላማ በሚያትትበትአንቀፅ 3 ንዑስ አንቀፅ 3 ላይ

“የፌዴራሉ አባሎች {ክልሎች} የራሳቸው ሰንደቅ አላማና አርማ ሊኖራቸውይችላል፡፡ ዝርዝሩን በየራሳቸው ምክር ቤት ይወስናሉ፡፡”

ይላል፡፡ የትግራይ ብሔራዊ ክልል ሕገ መንግስት ደግሞ“የትግራይ ብሔራዊ ክልል የራሱ አርማ ያለው ሰንደቅ አላማ ይኖረዋል” ይላል፡፡ በዚሁ መሰረት ክልሉ በህግ የተወሰነ ሰንደቅ አላማ አውጥቶ በመጠቀም ላይ ይገኛል፡፡

ሆኖም ከላይ ለማንሳት እንደሞከርኩት ይህ አይነት የሰንደቅ አላማን ህልውና የመካድ አመለካከት ከግለሰቦች እምነት አልፎየፓርቲዎችም እምነት ከመሆን የደረሰ፤ ከትግራይ ክልል ባንዲራም ከፍ ብሎ በኢፌዴሪ ሰንቅ አላማም ላይ የሚሰነዘርየአመለካከት ዝንፈት ነው፡፡ በርግጥ ችግሩ በሰንደቅ አላማ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ለሕገ መንግስት ካለ የአልገዛም ባይነትመንፈስ ጋር በቀጥታ የተቆራኘ ነው፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ

‘ፍኖተ ነፃነት’ በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የሚታተም ጋዜጣ ነው፡፡ በመስከረም ወር 2004 የፓርቲው አፈቀላጤ በሆነው በዚህ ጋዜጣ ላይ “ጋኖች አለቁና ምንቸቶች ጋን ሆኑ” በሚል ርዕስ የወጣ ፅሁፍ እንዲህ ይላል፡፡

“ቀደምት አያቶቻችንና አባቶቻችን ትንቢት የመቅሰምና የመተርጐም ብቃትና ችሎታ ስለነበራቸው፣ ነቢያት የተነበዩትን ሁሉ በተግባር አውለውታል፡፡ በመሆኑም በቀድሞው ሰንደቅ ዓላማችን ላይየነበረውንና በዚህ መንግሥት ከቦታው ተነስቶ ብቃትና ትርጉም በሌለው ኢትዮጵያን በማይወክልምስል የተተካውን የአንበሳ ዓርማ የመሲሁን የኢየሱስን ወደ ምድር መውረድ ኢትዮጵያን ወክሎመምጣት በመገንዘብና በመንደፍ የተባለውን ዓርማ ከሰንደቅ ዓላማው ላይ እንዲታይና እንዲኖርአደረጉ፡፡”

“ይሁን እንጂ፣ የእግዚአብሔርን አምላካዊነትና ጠባቂነት አምና ለተቀበለችው ጥንታዊት የአዳምመገኛ ምድረ ኤዶም ወይም ምድረ ገነት ለተባለችው ለኢትዮጵያ የተሰጣትን በረከት ምንነቱንናምሥጢሩን ሳይረዳ፣ ይህ መንግሥት የአንበሳውን ዓርማ አንስቶ ትርጉም በሌለው ዓርማ መተካቱታሪክ የማይረሳው ከፍተኛ ስህተት ነው፡፡”

አንድነት ፓርቲ በጋዜጣው ላይ ባወጣው ፅሁፍ በኢፌዴሪ ሕገ መንግስት የተደነገገውን ሰንደቅ አላማ እንደማይቀበል ግልፅ አድርጓል፡፡ አንድነት በዚህ ደረጃ ለኢፌዴሪ ሰንደቅ አላማ ተቃውሞውን የገለፀ ፓርቲ ሆኖ ሳለ አባሎቹ ለአገሪቱ ባንዲራ ክብር ይሰጣሉ ብሎ መጠበቅ ዘበት ነው፡፡ የክልሎችን ሰንደቅ አላማ ይቀበላሉ ብሎ መጠበቅም ሞኝነት ነው፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ

ሰማያዊ ፓርቲ ከአንድ አመት ቀደም ብሎ ከ1997ቱ የተቃውሞ ሰልፍ ወዲህ የመጀመሪያው የተባለለትን ሰልፍ አካሂዶ ነበር፡፡ በዚህ ሰልፍ ላይ ታዲያ አንድ አነጋጋሪ ድርጊት ተፈፀመ፡፡ ድርጊቱ የተፈፀመው ፒያሳ ከሚገኘው አፍሪካ ወርቅ ቤትፊት ለፊት ነው፡፡ ከግንፍሌ እየገነፈለ የመጣው ሰልፈኛ ቁልቁል ሲንደረደር ከወደ መርካቶ የመጣው የድጋፍ ሃይል ወደላይ እየተመመ ነበር፡፡ ከመርካቶ አቅጣጫ አራት ወጣቶች የኢፌዲሪ ሰንደቅ አላማን ወደጎን ዘርግተው ይዘው መጡ፡፡ ወደዋናው ሰልፍ ሊቀላቀሉ በግምት 100 ሜትር ሲቀራቸው የሰልፉ አስተባባሪዎች ወደነሱ ሲሮጡ መጡና አንደኛው “ይህንባንዲራ ለምን ይዛችሁ መጣችሁ? የኛ እንዳልሆነ አታውቁም?” እያለ በቁጣ ደነፋባቸው፡፡ በመካከላቸውም በተፈጠረ ግጭት ሰንደቅ አላማ የያዙ ተሰላፊዎች ጥቃት ደርሶባቸዋል፡፡

በወቅቱ ሰንደቅ አላማዋ እርስ በርስ በተካሄደ መጓተትና ትንቅንቅ ተረጋግጣና ተጎሳቁላ ስለነበር በኢቲቪ ዜናውንየተመለከቱ ኢትዮጵያውያን ተግባሩን አውግዘውታል፡፡ ያኔ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎች ምላሽ የነበረው ታዲያ ይሄ የኢሕአዴግእንጂ የእኛ ባንዲራ አይደለም የሚል ነበር፡፡

አክራሪው የእስልምና ሃይል

በኢፌዴሪ ሰንደቅ አላማ ላይ ከተፈፀሙ አፀያፊ የቅርብ ጊዜ ተግባሮች ከብዙዎች ትውስታው የማይጠፋው ራሱን‘ድምፃችን ይሰማ’ በሚል የሚጠራው አክራሪና ፅንፈኛ ሃይል የፈፀመው ነው፡፡ ይህ ሃይል የኢትዮጵያ ሙስሊሞችንየመብት ጥያቄዎች ለራሱ ፖለቲካዊ ግቦች ማስፈፀሚያነት ለመጠቀም ባደረገው እንቅስቃሴ ‘እምነታችሁ ተነካ’ በሚልያደናገራቸውን ወጣቶች አደባባይ ማስወጣት ችሎ ነበር፡፡ ከአመት በፊት በዚሁ በአዲስ አበባ በፈጠረው ሁከት ላይ እጅግየተጎሳቆለችና የተበጣጠሰች ሰንደቅ አላማን በማውለብለብ ለሰንደቅ አላማ ያለውን ጥላቻ በግላጭ አሳይቷል፡፡

በአጠቃላይ በአገራችን የሰንደቅ አላማ ጉዳይ በቀጥታ ከአገሪቱ የተቃውሞና የአክራሪነት እንቅስቃሴ ጋር በጥብቅ የተቆራኘነው፡፡ ለዚህም ነው በአለም ከምናያቸው የተቃውሞ ሰልፎች በተለየ መልኩ በአገራችን የተቃውሞ ሰልፎች ሲካሄዱባንዲራችንን የማናየው ወይም ሰልፈኞቹ በሕገ መንግስቱ ከተደነገገው ውጭ አርማ የሌለው ባንዲራ ይዘው የሚወጡት፡፡

ሌላው ጉዳይ ተቃዋሚና ፅንፈኛ ሃይሎች ስለ ሕገ መንግስቱ ያላቸው አረዳድ ነው፡፡ እነሱ ሕገ መንግስቱን ስለማይቀበሉት/ስለማያምኑበት በሕገ መንግስቱም ሆነ ከሱ በታች ባሉት ሕጎች ለመመራት እንደማይገደዱ ያስባሉ፡፡ ለምሳሌ ሰማያዊፓርቲ ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ

“ነፃነት በሌለበት ሀገር ዜጎች ሰብዓዊ ክብራቸውን ለማስጠበቅ የሚያደርጉት ጥረት የሌሎች ሀገርመንግስታት የሚያደርጉትን ጣልቃ ገብነት በዓለም አቀፍ ስምምነቶችም ሆነ በተለይ በሁለቱ ሀገሮችግንኙነት ላይ ከፍተኛ ጥላ የሚያጠላ መሆኑን ግንዛቤ አለመወሰዱ እጅግ የሚያሳዝን ድርጊት ነው”

በማለት ለግንቦት 7 የሽብር ቡድን ያለውን የቁርጥ ቀን አጋርነት አሳይቷል፡፡ ልብ በሉ፤ ግንቦት 7 የመንግስት ስልጣንንበሃይል ለመያዝ ጦር ሰብቆ በኤርትራ በረሃዎች የመሸገ ነው፡፡ ሕገ መንግስቱ ደግሞ በአንቀፅ 9 “በዚህ ሕገመንግስት ከተደነገገው ውጭ በማናቸውም አኳኋን የመንግስት ስልጣን መያዝ የተከለከለ ነው” ይላል፡፡ በተጨማሪም የፀረሽብር ሕጉ በምክር ቤቱ ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀውን ግንቦት 7ን ማበረታታትን ወንጀል ያደርጋል፡፡ ለሰማያዊ ፓርቲፖለቲከኞች ግን ሕጉን ስለሚቃወሙት እነሱን የሚገዛ አይመስላቸውም፡፡

በተመሳሳይ ሕገ መንግስቱ የኢፌዴሪ ሰንደቅ አላማ ምን እንደሚመስል ይደነግጋል፡፡ ክልሎችም የራሳቸውን እንዲሁ፡፡ ተቃዋሚዎች ግን አሁን ያለው ሰንደቅ አላማ በሚቃወሙት ሕገ መንግስት የተደነገገ በመሆኑ የሚያከብሩት ሳይሆንኢሕአዴግና ደጋፊዎቹ ብቻ ሊያከብሩት የሚገባ ይመስላቸዋል፡፡ ህልውናቸውን ካረጋገጠላቸው ሕገ መንግስት ጀምሮበየትኛውም ሕግ የተጠቀሱ መብቶቻቸው በተጣሱ ወይም የተጣሱ በመሰላቸው ጊዜ ደግሞ ወዲያዉኑ ተገልብጠው የሕገመንግስት ዘብ ሆነው ይቆማሉ፡፡

በርግጥ አስራት አብርሃም ለራሱ የሰጠው ማዕረግ ‘የፖለቲካ አክቲቪስትና ደራሲ’ የሚል መሆኑ በአንድነት ፓርቲ ውስጥ ካለው ሃላፊነት ጋር ሲደመር አስራት ይህን መፃፉ ሊያስገርም ይችላል፡፡ ሆኖም ግን የግለሰቡ እምነት የተቃዋሚዎቻችንእምነት መገለጫ ተደርጎ መታየት ያለበት ነው፡፡

******

Kebede Kassa

more recommended stories