በሺሻ ማስጨሻና ጫት ማስቃሚያ ቤቶች ላይ ህጋዊ እርምጃን መውሰድ የሚያስችል ህግ እየረቀቀ ነው ተባለ።
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የምርመራ ሀላፊ የሆኑት ምክትል ኮማንደር አበራ ጉሊና ፤ የህጉ መዘጋጀት እስካሁን ይወሰድ የነበረውን የማሸግ ብቻ እርምጃ ከፍ በማድረግ ድርጊቱን ለማሰቆም ያግዛል ብለዋል።
እስካሁን በድርጊቱ ላይ የሚሳተፉ አካላትን ማስቀጣት የሚያስችል ህግ ባለመኖሩ ፥ የሺሻ እቃዎችን ከማቃጠልና ቤቶቹን ለጊዜው ከማሸግ ያለፈ እርምጃ አይወሰድም ነበር ነው ያሉት።
አዲስ የሚረቀው ህግ ግን ድርጊቱን በዘላቂነት ለመከላከል እንደሚያስችል ተናግረዋል።
ፍትህ ሚኒስቴርም የጉዳዩን አሳሳቢነት በመረዳት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ለጉዳዩ የህግ ማእቀፍ የማዘጋጀት ስራ እያከናወነ መሆኑን ገልጿል።
የህግ ማዕቀፉ እስኪጠናቀቅ ድረስም ፖሊስ የጀመረውን ሰራ የሚቀጥል ሲሆን ፥ ህብረተሰቡም ትብብሩን ሊያጠናክር እንደሚገባ ሚኒስቴሩ ጠቁሟል።
*********
ምንጭ፡- ፋና፣ መጋቢት 10-2006፣ ርዕስ ‹‹በሺሻ ማስጨሻና ጫት ማስቃሚያ ቤቶች ላይ ህጋዊ እርምጃን መውሰድ የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ ነው››፣ በብርሀኑ ወልደሰማያት
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…