(አሉላ ሰለሙን)
ሠሞኑን በአጼ ምንሊክ የሙት ዓመት መከበር እና እሱን ተከትሎ አንድ አርቲስት በሠጠው ያልተገባ አስተያየት የተነሳ ሐሳቦች ሲንሸራሸሩ እና ንትርኮች ሲካረሩ ተስተውሏል። ይህንን በመንተራስ ኢትዮጵያዊያን የኦሮሞ ክልል ተወላጆች በተለይ በአርቲስቱ የ”ቅዱስ ጦርነት” አስተያየት የተሰማቸውን ቅሬታ በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።
የቀኝ ዘመም ፖለቲከኞቻችን በአጼ ምንሊክ እና የበደል አሞካሻቸው አርቲስት ላይ በተከፈተው የአጸፋ መልስ ተከፍተዋል። እነዚህ በዚህ ጸረ ምንሊክ እና የበደል አቀንቃኛቸው በተካኼደ ዘመቻ የተከፉትን በሁለት ጎራ ከፍሎ ማየት ይቻላል። እነሱም 1) በተነሳው ተጨባጭ ኹነትን የማጋለጥ ኺደት የተከፉ “አትንኩብን” ባዮች እና 2) ከስጋት በመነጨ የራሳቸው ስሌት የወሰዱ ድንጉጦች ናቸው።
“አትንኩብን” ባዮች
እነዚህ በተጨባጭ የዘውድ አምላኪነት የተጠናወታቸው ኃይሎች፣ ሠማያዊ ፓርቲ እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል፣ በአንድ በኩል የምንሊክ ጉድ ለምን ተነሳ የሚል ኩርፍያ ያደረባቸው ሲኾኑ፤ ጉዳዩም አጼ ምንሊክ ከፈጸሟቸው ውጫዊ እና ውስጣዊ ስሕተቶች በቀጥታ የሚገናኙ ናቸው። በሌላ በኩል አሁን ካለው የሀገራችን ነባራዊ የፖለቲካ ኹኔታ ጋር ተያይዞ፣ የምንሊክን ስሕተት መደበቁ አኹን ያለውን ገዢ ፓርቲ ብቻ በብሄራዊ ጥቅሞች ዙሪያ ተጠያቄ የማድረግ ስሌት በመያዙ ነው። በዚህ ጎራ የተሰለፉ በብሔር የተለያዩ ናቸው። ከሰሜኑም ደቡብም አሉበት። ለምሳሌ የትግራይ ተወላጅ ኾነው አኹን በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት የሚቃወሙ አንዳንድ ግለሰቦች በዚህ ጎራ ተሰልፈዋል። ለዚህም ቀደም ብሎ የተገለጸው የብሄራዊ ጥቅም እና ገዢውን መቃወም እንደ ግብ የመቆጠር አካሄድን መሠረት ያደረገ ነው። ይህ አካሄድ በተለይ አቶ መለስ ዜናዊን ብሄራዊ ጥቅማችን አሳልፎ እንደሰጠ እና ለኤርትራ መገንጠል ኹነኛ ሚና እንደተጫወተ መሪ አድርጎ ከመውሰድ ይመነጫል። በዚህም ምክንያት፣ አንድም አጼ ምንልክን ማጋለጥ የህወሓት አጀንዳ ተደርጎ ስለሚወሰድ፣ “አጼ ምንሊክን ከነኩ ህወሓትን እንደ መደገፍ ተደርጎ ይቆጠርብናል” ከሚል ስጋት እና ህወሓትን ለማበሳጨት ምንሊክን መከላከል እንደ ጊዚያዊ ስትራቴጂ፣ በሌላ በኩል ደግሞ፣ አጼ ምንሊክ በብሄራዊ ጥቅም አሳልፎ በመስጠት ተወቃሽ ከሆኑ እና ከተጋለጡ፣ መለስ ዜናዊን ባህር በር ያሳጣን፣ ኤርትራን ያስገነጠለ በሚል ለመክሰስ እና ለማጠልሸት የሚጠቀሙበት ሴራ ዋጋ ቢስ ያደርግባቸዋል። ስለዚህ በደምሳሳው ለጊዚያዊ ፖለቲካዊ ትርፍ ሲባል ምንሊክን ባይነኩ ይመርጣሉ። በተለይ የዓረና ፓርቲ ካድሬዎች ለአንድነት ፓርቲ ያቀረቡት የውህደት ጥያቄ ተቀባይነት ያገኝ ዘንድ ከምንሊክ አሞካሺዎች ጎን መቆምን እንደ እጅ መንሺያ እየተጠቀሙበት ይገኛሉ። ከዚህ በተጨማሪ ግን በአጠቃላይ፣ በቀኝ ዘመም ጎራ የተሠለፉ የተለያዩ ብሔር ተወላጆች በውል ለታወቁ እና ላልታወቁ ምክንያቶች በዚህ “ምንሊክን አትንኩብን” በሚል ጅምላዊ አስተሳሰብ (bandwagon) ተሳፍረዋል።
ስጋት
ይህ ሁለተኛው ጎራ ደግሞ የአጼ ምንሊክ ስሕተቶች በአንዳንድ ቅጥ ባጡ አስተያየቶች እና ጉዳዩ ከህዝብ ጋር በማያያዝ ስሕተቱን ለማካስ የሚወሰድ የበቀል እርምጃ ለኛም ይተርፋል በሚል ስጋት የተሰባሰበ ነው። አጼ ምንሊክ የፈጸሟቸው በደሎች የብሔር ባለቤትነት ታርጋ ተለጥፎባቸው ጉዳዩ ወደ ብሔር ግጭት እንዳያመራ የሚሠጉ አሉ። በዚህ ጎራ ፖለቲካውም ታሪኩም በቅጡ ያልገባቸው፣ በጉዳዩ ጠለቅ ያለ ዕውቀት የሌላቸው አብዛኛዎችም ይጨነቃሉ። ነገር ግን ፖለቲካዊም ታሪካዊም ሂደቱን ተረድተውም የሚፈሩ አሉ። እነዚህ የኋላዎቹ፣ ከዚህ አሁን ከተፈጠረው የሙት አመት ዝክር እና የ”ቅዱስ ጦርነት” ጉዳይ የአጼ ምንሊክ እውነተኛ ታሪክ መጋለጥ ሲጀምር እና በፊት ነገሮች ሲብላሉ ጀምሮ፣ የብሔር ጭቆና እና የምንሊክ በደሎች እመኑ በሚል በተደጋጋሚ በቀረበላቸው ሐሳብ ተደናግጠው ጉዳዩ ወደ ብሔር ግጭት ሊያመራ ይችላል በሚል፣ አንዳንድ ትንታግ የማህበራዊ ድረ ገጽ ጸሀፊዎቻቸው ሳይቅር ወላፈኑን መቋቋም ተስኗቸው ኮብልለዋል። በፌስቡካዊ አነጋገር አካውንታቸው ዲአክቲቨት አድርገዋል። ገሚሶቹ ደግሞ ዝምታን መርጠዋል። አንዳንዶቹ፣ በተሳትፎ ቢቆዩም እንኳ፣ በማህበራዊ ደረ ገጽ “በቃ!” በሚል መፈክር አመጽ አነሳስተው መንግስት ይቀይርልናል ብለው የጠበቁት ሳይኾን ቀርቶ በዚህ ጉዳይ መጠመዱ በእንብርክክ ሄደብን ወይም አስኬደን ብለው ሲጽፉ ተመልክተናል።
ከዚህ አጼ ምንሊክ የፈጸሙትን በደል ከህዝብ ማቆራኘት የወለደውን ፍርሃት እና በተዛባ አስተሳሰብ ምክንያት ይህ ጎራ የተለያዩ ብሔሮች አላቀፈም። አጼ ምንሊክን የአማራ ወኪል አድርጎ በማስቀመጥ፣ እሳቸው የፈጸሙት በደል ሒሳብ ለማወራረድ የሚደረግ ማናቸውም፣ እውነተኛ ታሪኩንም የመፃፍ ጨምሮ፣ ለኛም ይተርፋል የሚል የስጋት አስተሳሰብ ያነገበ ነው። እዚህ ላይ ግን፣ አጼ ምንሊክን ማነው የአማራ ወኪልም አማራም ያደረጋቸው? ይህንን ለማጥቃትም እና ለመከላከልም የሚደረገው ትንቅንቅ ነገሩን አባብሶታል። ይህ ግን ፈጽሞ የተሳሳተ አረዳድ ነው። ሰውዬው አማራም አይደሉም አማራንም አይወክሉም። እንድያ ቢሆን ኖሮ ቁጥር አንድ ላይ የተገለጹ “ምንሊክ አትንኩብን” ባዮች የተለያዩ ብሔር ተወላጆች አይኾኑም ነበር። የምንሊክ ስም በክፉ ሲነሳ የሚከፋቸው ጉራጌ፣ ትግራዋይ ጓደኞች አሉኝ።
የአጼ ምንሊክ አማራነት አማርኛ ቋንቋን ባስቀጠለ፣ በተናገረ እና ባስፋፋ ከኾነ፣ አጼ ዮውሃንስም አቶ መለስም አማራ ናቸው ማለት ነው። ከዚህ በዘለለ አጼ ምንሊክን አማራ እና የአማራ ወኪል የማድረግ አካሄደ ስሕተት ነው። በነገራችን ላይ፣ እንደ አቶ መለስ ዜናዊ መንግስት አማርኛ ያስፋፋ ስርዓት በኢትዮጵያ አልታየም። ይኽ የአሃዝ ጉዳይ ነው። ነገር ግን አቶ መለስ አማርኛን ያስቀጠሉት እና ያስፋፉት ጡት በመቁረጥ፣ እጅ በመበጠስ አይደለም። አስገድዶ በመጫን ሳይኾን፣ በፍላጎት እንዲስፋፋ አድርገዋል። ከሀገሪቱ አጠቃላይ የምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት፣ ትምህርትና የሥራ ዕድል ከመስፋፋቱ ጋር ተያይዞ አማርኛውም የሚነገርበት ሽፋኑ ሰፍቷል።
ከታሪክ በስተጀርባ ያለ የፖለቲካ “ትብብር”?
መግቢያ ላይ ከተገለጸው ሐሳብ ጋር ተያይዞ፣ በፖለቲካ አቋም የማይመሳሰሉ በፊት በሁለት ጫፍ የነበሩ አሁን የፖለቲካ ዝሙት በሚመስል ግንባር ፈጠሩ በሚል የተከሰሱ የፖለቲካ ጎራዎችም አሉ። እነዚህም፡ ጃዋር የሚመራው ኢትዮጵያዊያን የኦሮሞ ክልል ተወላጆች በከፈቱት ዘመቻ በቀጥታ የሚሳተፉ እና ተባብራችኋል ተብለው የተከሰሱ ይገኙበታል። በፊት ሲቃወሙት ከነበሩት የጃዋር ቡድን ጋር አሁን በዚህ ጉዳይ ላይ እንዴት ሊተባበሩ ቻሉ? ይህ የፖለቲካ ዝሙትነት አይደለም ወይ? ነው ክሱ። በፖለቲካ አቋም ከጃዋርም ኾነ ከኦነግ የተስማማ የለም። በአጼ ምንሊክ እና አሞካሺዎቻቸው የተያዘው አቋምም፣ ከእነ ጃዋር ዘመቻ በፊት የነበረ ጉዳይ ነው። ለዚህም ነው እላይ ቁጥር አንድ ላይ ከተገለጹ “አትንኩብን” ባዮች መግባባት ያልነበረው። አኹን ላይ ደርሶ በዚች ነጥብ ከጃዋር እና ቡድኑ የተወዳጀ የለም። በዚህ ረገድ ጊዚያዊ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ተብሎ አዲስ የተፈጠረ ግንባርም የለም። ለምን ሐሳቡ ተመሳሰለ ከኾነ፣ ሐሳቡ አስቀድሞም ነበር፤ ለዛውም ከአጼ ምንሊክ መቶኛ ሙት አመት መከበር እና “ቅዱስ ጦርነት” በፊት። ጃዋር በፊት በሜንጫው ተውግዟል። አሁን ላይ ደርሶ ይኼ ውግዘት አይነሳም፤ ይቅርታ እስካልጠየቀ ድረስ። ጃዋር ከኢሳት እና የአንድነት ቀኝ ዘመም ፖለቲካ ፍቅር ከመመስረቱ በፊት ባለው ጊዜም ይህ የምንሊክ እውነተኛ ታሪክ፣ የፈፀሙት በደል እና ሀገራዊ ክህደት የማጋለጥ ሂደት ነበረ። አኹንም ይቀጥላል። ይህ ሂደት አሁን እነ ጃዋር ስለተቀላቀሉትም አይቆምም። ለምን ተቀላቀሉ ተብሎ የባለቤትነት መብት ጥየቃም የለም። እንዲሁም የአቋም ለውጥም አይኖርም። እነ ጃዋር ተገቢ እና ተቀባይነት የሚያገኙበት መስሎ ሲሰማቸው ኢሳትን እና የአንድነት ኃይሎች ተሰናብተው መጥተዋል። እንኳን ወደ እውነታው በሰላም መጣችሁ ሊባሉ ብቻ ነው የሚገባው፤ የፖለቲካ አቋም ልዩነቱ እንደተጠበቀ ኾኖ።
************
*The author Alula Solomon is a lecturer in Mekelle University, he is a guest writer on this blog and can be reached at [email protected]
ene endemimeslengh meriwoch bezemenachew tirum metfom yiseralu letru sirachewm hone letfatachew mewekesm memesgenim yalebachew rasachew gilesebochu nachew enesu yemetubet bher weym gosa lezih halafinetun aywesdim.enkuan tiwlid teshagro ahun lay kerto begizew yeneberutm bihon bezih mewekes yelebachewm tekebabreninna tewaden adisituan ethiopia engenba ahun yalut meriwoch kedirochu bememar sitetochn balemedgem tiru gonochin degmo bemagolbet meketel alebachew.
gashe alula, mejemriya amarigna telemamed. keziya behuala newu yemitsafew. eskeziyaw gen aiga forum laay beziyaw bemesadebiya quanquah endefelgegeh zelabd. Gud eko newu anten manew degmo awgaj and wegez anshi yaderegehe bakih?!
@ nigusu ,calm down, minew gin endi tilacha wust gebah, be sime ab endi phobia tizihal. minim Eko merja na mikniat yelehim silawerahew negere, erasavhihu bemimechachihu menged tsifachihu esunu manebneb.ye ethiopia history be endante aynet ye chinkilat cancer balebet sew understand ayderegim. ezi area lay man nebere giltsi new, oromo’s are the endigineous people of this area. read many books which written by impartial historians if u’ve an ability to read. rather than shouting without knowledge. budha, mikegna , komata , dingay ras yemagebaw, shermuta addisin yatlekeleku, lemagn , selfish are the characters of ur people amharas. esti ye oromo, tigre, sidama somale……..lemagn komata budha ayteh takaleh yelem. hiBih gar hedeh enezihin negeroch bitastekakil yishalal ezi zimbleh kemitchoh. i know tigreans are1000000000*better than ur neftegna sireat, even if there are some problems that should be corrected in the future.
One more thing for Alula. In the first place you did not deserve the name Alula Never Never Never. Everybody knows that How much Weyane did not like any history about Ethiopia, specailly about Minilik. so all such thing comes form Weyane using Galas, what ever you said no one kills ethiopians morethan Weyane even morethan Italians. Endesew sebiseba sew badereg zare ??????????????????????????
The Emperor Minilik Said “Do not kill any one even Gala.” And He saves you all. Now you said what you are saying.. Because You are Galas. as Somalians and Sedama called you Gala. which means unbeliever and pagans… Today you try to shout because you have no any history . offcourse you are not Ethiopians you came form Madagascar following cattle, Thanks to Minilik, Gobena and the rest of the Ethiopian people. You know how Gala’s are stupided. They did not read anything and write any thing, Please read ” Kemahu Gala”, Yegala Tarik. and so on. Then you will understand your self. Again Minilik is the great Emperor for Ethiopia, For Africa even for Galas.
P.S Oromo and Gala are not alwayes similar.
For all you ????? guys please read this
http://ayyaantuu.com/horn-of-africa-news/oromia/history-101-fiction-and-facts-on-oromos-of-ethiopia/
i have no reason not to agree with this article
I absolutely agree with this article !