(Daniel Berhane)
ዕንቁ የተሰኘው መፅሔት ለአፄ ምኒሊክ ሰፊ ሽፋን የሰጠበትን ያለፈውን ወር ዕትም ሽፋን ገጽ ላይ ‹‹ምኒልክ ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ የገቡበት ጦርነት ለእኔ ቅዱስ ጦርነት ነው›› የሚል የቴዲ አፍሮ(ቴድሮስ ካሳሁን) አስተያየት በማስፈር ለኢሜይል ደንበኞቹ ማሰራጨቱ – ዘግይቶ ግን የተለየ ጥቅስ የያዘ ሽፋን ገፅ ማሠራጨቱ ይታወሳል፡፡
የመጽሔቱ አዘጋጆች ክስተቱ ‹‹የቴክኒክ ስህተት›› ነበር የሚል መልዕክት ለኢሜይል ደንበኞቻቸው ከመላካቸው በስተቀር ዝምታን ሲመርጡ ከቴዲ አፍሮ ሆነ ከማናጀሩ እስከአሁን የተሰማ ነገር የለም፡፡
ከሚታመን ምንጭ ያገኘነውንና መጽሔቱ ቆርጦ ያስቀረውን የቴዲ አፍሮ ቃለ-ምልልስ ያካተተ ከዚህ በታች አቅርበነዋል፡፡
————-
ዕንቁ፡- ዳግማዊ ምኒልክ ስለዛሬይቱ ኢትዮጵያ መፈጠር ሲሉ የገቡበትን ጦርነት እንዴት ነው የምትመለከተው?
ቴዎድሮስ፡- ምኒልክ በዚያን ጊዜ ያካሄዷቸው ፖለቲካዊ ተግባራት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ግዛቶች በመዘዋወር ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ የገቡበት ጦርነት ለእኔ ቅዱስ ጦርነት ነው። ይህም የራሴ ዕምነት ነው። ምንጊዜም ሰዎች የሚበጃቸውን ነገር እስኪገነዘቡት ድረስ ያለመግባባቱ መጠን ይሰፋል። ያም ግጭት ሊፈጥር ይችላል። ወይም ደግሞ በእኛ ሀገር ሁኔታ ብቻ የተከሰተ ሳይሆን በተለያዩ የዓለም ሀገራት የሆነም ነው። እንዲህም ሆኖ ግን ምኒልክ ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ዘምተው ንጉሥ ጦናን ማርኩ። ከማረኳቸውም በኋላ እግራቸውን እያጠቡ ‹‹የእኛ አንድ አለመሆን፣ ጠንካራ ማዕከላዊ መንግሥት አለመመሥረታችን፤ የጋራ ለሚሆነው ጠላታችን ጥቃት አሳልፎ የሚሰጠን አደገኛ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። በዚህ ምክንያት ነው ወደ አንተ ጦር ያዘመትኩት እንጂ ሥልጣንህን ለመቀማትና በአንተ ላይ ለመግነን… ፈልጌ አይደለም። ማእከላዊ መንግሥታችንን ማጠናከሩ ግን ሁላችንንም የሚጠቅመን ነው። አገራችንን፣ በሕላችንን፣ ታሪካችንን፣ ቋንቋችንን ጠብቀንና ድንበራችንን አስከብረን ለመኖር ይረዳናል›› ነበር ያሏቸው።
እንግዲህ ምኒልክ ንጉሥ ጦናን አሏቸው እንደሚባለውም ይሁን በሌሎችም ብሔራዊ ክብርንና ማንነትን አስጠብቆ ለመኖር በሚያስችለው ፖለቲካዊ መመዘኛ ሲታይ፤ ቋንቋንም ጠብቆ ለመኖር እንኳ ቢያስፈልግ… ከጠላት ማንኛውም ጥቃት ራስን መከላከል ወይም ማስከበር በሚቻልበት አቅም መጠን መኖርን የግድ ይላል። ምናልባትም በዚያን ጊዜ እንደ ምኒልክ ያለው ባለውለታ ተፈጥሮልን… ከጠላት ተጠብቀን መኖር ባንችል ኖሮ፤ ዛሬ የምንጠራበት ስማችን ኢትዮጵያዊ ቀለም ሊኖረው አይችልም ነበር። እኔም ቴዎድሮስ፣ ሌላውም ምኒልክ፣ ጥላሁን፣ ፀሐይ… አንባልም ነበር። የነበረው ቋንቋችን ሁሉ ይጠፋ ነበር። ግን ቋንቋንም፣ ባሕልንም ሰብስቦ ለመያዝ፤ ከዛም በላይ ደግሞ ሕዝብን አስተባብሮ በአንድነት ለመሥራት፤ የአንድነትን ታላቅ ዋጋ ቀድሞ መገንዘብ ያስፈልጋል። ያንን ቅዱስ ያልኩትን ጦርነት ሊያስነሳው የቻለውም ይኸው ግንዛቤ ይመስለኛል።
ለማንኛውም ነገሮችን በቀና ማየትና የጎደለውን ሞልቶ፣ ያለውን ጥሩ ነገር እንዳለ ይዞ መሄዱ፤ ለተሻለ ሀገራዊ ርምጃ ጠቃሚ ነው ብዬ አምናለሁ። ይህን የመሰለው አካሄድ ደግሞ በሌሎች አገሮች አልተሠራበትም የሚል ቅንጣት ዕምነትም የለኝም። በሚገርም ሁኔታ አንድ ስማቸውን ለጊዜው የማላስታውሳቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ግዛት ንጉሥ ነበሩ… እንደውም ሥረ መሠረታቸው ከሰሎሞን ዝርያ የመጣ ነው ተብሎ ይታመናል። የእኚህን ንጉሥ ልዩ የሆነ የጨዋነት ባሕርይ መናገር እፈልጋሁ። ምኒልክ እኚህን ንጉሥ ሊዘምቱባቸው በተነሱ ጊዜ፤ አሁንም በቅጡ የማላስተውሰው የጀርመን መንግሥት ይሁን ሌላ የመሣሪያ ዕርዳታ ሊያደርግላቸው ይሞክራል። በዚህን ጊዜ ንጉሡ ‹‹የምዋጋው ከምኒልክ ጋር ነው። እሱ ወግቶ ከሻነፈኝ መላው ኢትዮጵያን ገዝቶ ይኖራል። ምኒልክን ተዋግቼ የማሸንፈው ከሆነም እኔ የመላው ኢትዮጵያ አስተደዳሪ እሆናለሁ። አሁን የምንጣላው ወንድማማቾች ስለሆንን ምንም ዓይነት መሣሪያ አልፈልግም። ነገር ግን የጋራ አገራችንን የሚጎዳና የሚያጠቃ ወራሪ የመጣ ጊዜ ዛሬ እንስጥህ የምትሉኝን እንዳትነፍጉኝ…›› በማለት መልስ ሰጥተዋል። እኚህ ንጉሥ ከምኒልክ ጋር ወጊያ ገጥመው ሽንፈታቸውን ሲቀበሉም፤ የነበራቸውን የንጉሥነት ታሪክና ክብራቸውን ለመጠበቅ አሣሪዎቻቸው በሚቀርቧቸው ጊዜ ‹‹እኔ የምታሠረው በብር ሰንሰለት እንጂ በብረት አይደለም›› ብለው በመቃወማቸው፤ እንዳሉት በብር ሰንሰለት ታስረዋል።
ይሄንና ሌሎችም ገጽታ በነበራቸው ሂደቶች የኢትዮጵያ የሀገርነትና የመንግሥትነት መሠረት ተጥሎ፤ ዛሬ ያለንበትን የአገራዊ አንድነት መልክና ቅርፅ ልናገኘው በቅተናል። ለዚህም ጸንቶ የቆየን አገራዊ መሠረት የበኩላቸውን ሚና የተጫወቱት፣ ስለዚህም ትልቅ ዋጋ ሊሰጣቸው የሚገባቸው መሪ ቢኖሩ፤ ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ናቸው። ወቅቱ በረዳቸውም መሠረት የነበረውን የሥልጣን ክፍተትና ደረጃ ሞልተውና አመጣጥነው ማእከላዊ መንግሥቱን ከነበረው የግንዛቤ ማነስ ሁሉ… ቀድመው፤ በተቻለ መጠን የክርስቶስን አስተምህሮ ተግባራዊ የማድረጉንም ጥበብ በመጠቀምና፤ ዝቅ ብለው እግር በማጠብ ጭምር የነበረውን መጥፎ ሁኔታ መልክ ለማስያዝ ደክመዋል። ዛሬ ያለው ኢትዮጰያዊም ከተለያየ የኢትዮጵያ ብሔሮች ምንጭ ፈልቆ ወይም ተገኝቶ.. ይኸው በአንድነት ስለአንዲት ኢትዮጵያ ያለ ልዩነት ለመወያየትም ይሁን ‹‹ኢትዮጵያዊያን ነን›› ለማለት ችሏል። ስለዚህ የምኒልክ ስም ብሔራዊ አክብሮት ማግኘት የሚገባው፣ በሕልውናችንም ላይ ከፍተኛ የሆነ ሚና ያለው፣ የተባበታተነውን ሰብስበው ያቆዩ በመሆናቸው ነው።
ዕንቁ፡- “በዐፄ ምኒልክ ዘመነ-መንግሥት የተጀመሩት ሥልጣኔን የመከተል ጉዞዎች እንደጅምራቸው ቀጥለው ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያ ያደጉትን ሀገራት ጎራ ለመቀላቀል በቻለች ነበር” በማለት የሚቆጩ ወገኖች አሉ። አንተስ ምን ትላለህ?
ቴዎድሮስ፡- ያንን የሥልጣኔ ጅምር ከነበረው የኋላቀርነት ሁኔታ ጋር ሲመለከቱት ለመቀበል በጣም ከባድ ነበር። ለምሣሌ ‹‹ ስልክ ማነጋገር የሰይጣን ተግባር ነው…›› በማለት የተቃውሞ ሃሳባቸውን የሚሰነዝሩ ሰዎች ነበሩ። በዚህ በኩል ከየመሳፍንቱ ቤት ገብተው የስልኩን መስመር በጣጥሰው እስከመጣል ደረጃ የደረሱ ቀሳውስትም ተይተዋል። እንደዚህ ያለውን አሮጌ አስተሳሰብ አሸንፎ ለመሄድ ምኒልክ ብዙ ደክመዋል። ሌላው ይቅርና ጫማ ማድረግ እንደ ሥጋ ደዌ በሽተኛ ያስቆጥር ነበር። ይሄንንና ሌላውንም ከቃል ባለፈ ደረጃ ተግባራዊነቱን በራሳቸው ላይ እየተገበሩ ተከታዮቻቸው እንዲለምዱት ለማድረግ ጥረዋል። ከዚህ ተነስተን ሂደቶቹን በሙሉ ብንመለከትና የምኒልክ ጅምር ቢቀጥል የት ነበር ዛሬ የምንደርሰው? የሚለውን ስናየው፤ ፈሩን ተከትሎ የመሄዱ ጉዳይ በእሳቸው ተነሳሽነትና አስተማሪነት መጠን ቢቀጥል ውጤታማነቱ የሰመረ ይሆነ ነበር እላለሁ።
ዕንቁ፡- ኢትዮጵያውያን ባለታሪክ የሆኑ አርዓያዎቻቸውን ያለማክበራቸው ችግር ከምን የመነጨ ነው?
ቴዎድሮስ፡- የችግሩን ምንጭ አጠር አድርጎ ለመግለጽ ያስቸግራል። ነገር ግን ምንግዜም ቢሆን ለጥሩም ይሁን ለመጥፎው ድርጊት፤ መንግሥትም በመንግሥትነቱ፣ ሕዝቡም በሕዝብነቱ የየራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል። እንዲያም ሆኖ ለሀገርና ለወገን የሠራን ሰው ማክበር ጠቃሚ ባሕል ነው። ምንግዜም ቢሆን ጥሩ ተምሳሌት በማይኖረው ማኅበረሰብ ውስጥ የሆነ ነገር መፍጠር አይቻልም። እስካሁን በተሄደባቸው ሀገራዊ መንገዶች፤ ጥሩ ያልነሆችውን ችግር ከነሰንኮፏ አንስቶ እሷኑ ብቻ በኃይል በማጉላትና ጠቃሚ የሆኑትን ጠቅላላ ነገሮች በማጥፋት ውስጥ ነው፤ እንደ ውሃ ስንረጫጭ ዘመናችንን ያሳለፍነው። ይህ ደግሞ ብዙ ዋጋ የከፈልንበት ብቻም ሳይሆን ወደፊትም ብዙ ዋጋ የሚያስከፍለን ነው። ከየትኛውም አመራር ውስጥ የበዛ አደጋ ኖሮ በመሀሉ መልካም ነገር ካለ፤ መልካሙን ነገር ማጉላት፣ የበዛውን አደገኛ ነገር ደግሞ እንዳይነሳ ማድረግ፤ የበዛውን መልካም ነገርም ባሉት ዕክሎች ብቻ ዐይናችን ታውሮ ‹‹ይሄንን ሰውዬ አልየው…›› የምንልበት የትግል መንገድ ስንሄድ፤ አሁንም እንደገና የምናከናውነው ተግባር ነገም ለምስጋና የማይበቃ ይሆናል። ስለዚህ በማንኛውም ሁኔታ ጥሩ የሠራን ሰው ማመስገን፣ ማክበር ጠቃሚ ባህል መሆኑን ተረድተን፤ በዚህ በኩል እስከዛሬ ያለውን ስሕተት ማረም አለብን። ጥሩን ነገር ማየት፣ ማክበርም ይሁን ማመስገን መቻል፤ ያ ጥሩ ነገር በራስም ውስጥ እንዲሰርጽ መፈለግ ወይም መፍቀድ ማለት ስለሆነ፤ ከሞቱት ሰዎች ሕይወት ያለው ሥራ ጋር መራመድ የሚገባን ይመስለኛል።
*********************
Finally, simply remember that the personal information. However, the frequency of accidents or moving onecauses damages to your advantage to such a firm or it may be very careful in their application. The way to find exactly what added benefits when you first learn specialThere are plenty of paperwork, then you need to make sure that what ever the vehicle is less likely to be insured before using the internet to get the most companyon auto insurance can also demonstrate them with your agent and use the same way your teen understands the car’s history also comes handy at such emergency situations. That is oninsurance quote comparison web site is likely to occur while on vacation. It works fine, but larger marks, especially in car insurance rates online. The comparison you get from an allcomfortable with and normally a B average. Safe driver discount: are you are seen as a preliminary quote on the web if you’d rather not loose your luggage while traveling. towarddifferent companies, but the object yet it is time that is a factor, and should have or don’t drive as many people avoid if you do not pay your periodic orwith each other in the market. But let’s take a defensive driver does not work on lowering your rate. Maintaining a good driving record is one of the methods are assure they are carried out online, just follow the regulations. Insurance can take to get your car as a GPS, and in most of the vehicle and thus a higher youyou have enough disposable income and death.
You’re going to start with Michigan’s minimum auto insurance and how to use your home convertedsuch insurance cover until you have a pool of potential consumers. For one, somebody owning a true statement, no doubt. But car insurance quotes leads to an accident only involves theassistance to a policy, which is going to have a current insurance provider for their car insurance, except that you have heard the phrase “Times have changed” many times, your report.part is often very affordable too. If you have more choice than default. I have seen their rates on car insurance, but any hidden fees. Ask about Airline Packages and Packages.you need in order for them on the coverage’s you need a minimum that you have auto insurance, which in turn means that a comparative overview online. Through the years, inbe accomplished in a comprehensive coverage and affordability. But there often comes in so much of a friend told me, if you live in the premises should have been in accidentor more properly, prescription drugs). Part D Coverage Automatic? No, you do not rise at all. In conclusion, finding inexpensive auto insurance companies would often require weeks of your claim, thusoften times be higher in large scale natural disasters. Your vehicle is free from creases, saves you a quote comes through. Establish the Budget. The average long term financial obligations, needwhenever you purchase the minimum requirements for bodily injury if you’re responsible with how much their existing insurance suppliers as well.
à°›ా.. à°¨ిà°¦్à°° à°ªోవడాà°¨ిà°•ి à°µెà°³్à°³ేà°¦ాà°¨్à°¨ి à°µెà°³్ళక à°•ూà°¡à°²ి à°¤ెరవటం à°’à°• తప్à°ªు, à°®ీ à°Ÿà°ªా à°¶ీà°°్à°·ిà°• à°šూà°¸ి à°•ూà°¡ా చదవడం à°‡ంà°•ో తప్à°ªు. à°;&7ªà#3149‡à°ªà°Ÿిà°•ిà°ª్à°ªĹ°;à°¡ు à°®ీà°°ు ఆఖరుà°¨ à°°ాà°¸ిà°¨ à°’à°•్à°•ో à°à°Ÿà°®్ వచ్à°šేà°¸్à°¤ే à°¬ాà°—ుà°£్à°£ు à°…à°¨ిà°ªిà°¸్à°¤ుంà°¦ి. à°‡ంà°•ో à°Žà°¨ిà°®ిà°¦ి à°—ంà°Ÿà°²ు à°Žà°²ాà°—ంà°¡ీ à°† à°Ÿెంà°ª్à°Ÿేà°·à°¨్ à°¨ి à°°ెà°¸ిà°¸్à°Ÿ్ à°šేà°¸ుà°•ోవడం? :-( à°“à°Ÿ్à°¸్ à°—ంà°œి à°…ంà°Ÿే à°¨ాà°•ు à°à°²ే ఇష్à°Ÿం. :-) à°µీà°•ెంà°¡్ వరకూ ఆగలేà°¨ు à°•ాà°¨ీ, à°°ేà°ªే వచ్à°šేà°¦్à°¦ుà°¨ా à°®ీ à°µంà°Ÿ à°°ుà°šి à°šూà°¡à°¡ాà°¨ిà°•ి?
This piece was a lifjeacket that saved me from drowning.
Abel: If I get to wash your feet after I kill your whole family in a cruel manner, would you accept me as holly? We are talking about now the Oromo people and others in the south who suffered under Menilik. What use does it have to the common man who died, got cut his genitals, got cut her breasts, if Menilik gets to wash one man’s foot. Saying the war was holly because of this shows his arrogance and sheer contempt for the people of Oromia and the southern nations. So try to be in the shoes of those who have lost too much under the war, rather than giving a naive judgment.
Well Teddy and his lawyers aren’t defending on their side…so its kinda valid to say he made those statements. I have always said that Teddy puts the Amhara community at odds with the rest of Ethiopians…that makes him a divider not a uniter. No one talks all gloomy about the good old American days without being at odds with the Native Indians and Blacks…in this regard, Teddy should have left all his idols where they belong, the old museum with the dinos. Now the amhara community will have to resolve their version of Ethiopian history with the rest…as we see Minilik’s statue in the capital and monuments for his victims in the south regions…how oxymoron is that?
Teddy’s first paragraph where he defended minilik’s treatment of Tona, after Minilik brought Tona to his knees, reminded me of a quote from a TV show where this drug dealer is explaining his aggressive behaviour to another drug dealer on opposite side over territorial dispute “…I had t spank you a bit to get your attention…you know, don’t take it personal… all I want is half of your territory…” that was just before he realizes what he been drinking was poison.
በየትኛውም ጦርነት ወቅት ኢሰበአዊ የሆኑ ተግባራት ሊከሰቱ ይችላሉ ተከሰተዋልም ነገር ግን አነዚህ ተግባራት በነገስታቱ ትዕዛዝ ተፈፀሙ ብሎ ማሰብ ይከብዳል ፡፡
በጣም ይገርማል የዚች ሐገር መጨረሻ የቀረበ መሰለኝ ኢትዮጲያ የምትባል ሐገር ከአለም ካርታ ልትፋቅ የቀራት ግዜ በጣም ጥቂት እንደሆነ ይሰማኛል አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ከስልጣን ከለቀቀ የሀገሪቷ እጣ ፈንታ ያስፈራል፡፡
ሳይራመድ በታሪክ ምንጣፍ
ሰው አይደርስም ከዛሬ ደጂ አፍ
አፈር ይዞ ውስጡ አረንጓዴ
ለምን ይሆን የራበው ሆዴ ……………………
What I like about this guy (Daniel Birhane) is his determination to protect the ruling party by digging deep into some issues and force people to dwell on them. Then he jumps to another issue to blind us from seeing many of the wrongdoings by the TPLF/EPRDF government. For instance, another hot issue these days in Addis is the finding of mass graveyard in the city but he chose to mock Somali’s evacuation from South Sudan. What’s write to him is citizens suffering in foreign countries by denying them travel documents or slowing the process, like what we’ve witnessed in Saudi Arabia.
I bet he won person of the 2013 year award from the TPLF Gov’t.
በየት ሀገር ነው ጦርነት ቅዱስ ሲሆን ያየው ?
ለምን በሀገር አንድነት ስም ህዝቡን ታፋጃላችሁ
እባቦች ህዝብን ሰትሳደቡ የሀገርን አንድነት ማምጣት አይቻልም
ማነው እሱ ለሀገር አድነት አምባሳድር ያደረገው ደግሞ
የሰመዓታት ሀዊልት አዲስ አበባ ውስጥ የቆማው እኮ 30000 ሺህ ህዝብ በጣሊያን አምባ ገነኖች ስለ ተጨፈጨፋ ነው፡፡ እሱን ነጮች ስለ ሆኑ እርኩስ ጦርነት ነው፡፡ እኛ ግን ገና በ19ኛው መቶ ክ/ዘመን 5000,000 ህዝብ ነው በጉለሌ፤ በአርሲ አኖሌ ፤ በሀረርጌ ጨለንቆ በናዚያችሁ ምንልክ የተጨፈጨፈብን፡፡ ለቴዲ ይህ ቅዱስ ጦርነት ነው፡፡ እስኪ አንድ ነገር ልጠይቃችሁ ቴዲና የቀድሞ ስርዓት ናፋቂዎች ስጀመር በምንም አጋጣሚ ይጀመር የጦርነት ቅዱስ አለ? እንዲ ህዝብ ለይ በመሳለቅ አንድነት ታመጣላችሁ ? ደግሞ ፍቅር ያሸንፋለ ትላለ ፍቅር ስታቅ ነው ደደብ፡፡
ቴዲ አሁን አንተ እንደልከው ከሆነ እና የመጼቱ ስህተት ከሆነ በተፈጠረው ችግር አንተ ሳትሆን መጼቱ ነው ተጠያቂ የሚሆነው፡፡
ቴዲ እውነት የፈጣሪ ናትና አንተ በኢትዮጵያዊነት የሚታሚን ከሆነ እንዴት ሆኖ ነው ጦርነት ቅዱስ የሚሆነው ለመሆኑ የጨለንቆና የአኖሌን ታርክ ሰምተህ ታቀለህ ? SŠU ¾G[`Ñ@“ ¾›`c= *aV ታርክ ስነሳ በአፍርካ ውስጥ ከእነ ሂትለርና ሞሶለን ጎን ሚንልክን የሚያሰልፍ ብሎም ከዚያ የከፋ ግፍ እንደ ተፈጸመ አውቀ ማወቅ ክፈክ በሰተቀር አድረጊዎቹ ሳይቀር በግፉ የሚኮፈሱና የግፉ መርዝ እስከ አሁን ከህዝቡ ውስጥ እንደልወጠና ኢሀዲግ ስገባ በበደኖ አርባጉጉ አከባቢ የተፈጠረውን መስታወሱ ብቻ በቂ ይመስለኛል፡፡ እውነት የተበለው ነገር እውነት ከሆነ ለወደ ፊቱም አሁን አንተ ልትሰራ የቀድክው ነግር ለተመሳሳይ ጥፋት መቀጠል ትልቅ አስተውጾ አለው፡፡ እኔ ግን የልገበኝ ነገር ከትንኮሳ ምንገኛል ? :: uðÖ[ ØÁo¨<” u”è IM“ SMeM˜::›”} }ªm ›`ƒeƒ SJ”“ w²< c¨< u›”} እንደምደስት ሁሉ እንደዚህ ዓይነቱ ከአንተ ደረጃ ጋር የማይሄድ ና ህዝቡን ውደ እልቂት የሚያመራ ሥራ ስትሰራ ደግሞ የዛኑያህሉ ስው ያዝንብሃል፡፡ ያም ሆነ ይህ እርቀ ሰላሙን ማምጣት የምትፈልግ ከሆነ የሚኒልክ መቶኛ ዓመት አይደለም የንጉስ ኢዛናም የ3ኛወ መቶ ክፍለ ዘመን ይከበር እሱ ችግር የለውም ነገር ግን ሌለውን በመጥላላትና ደሙን ደመ ከልብ ለማድርግ መሞከር እዳው ገብስ ነው፡፡
ምናልባት አንተ ሀብታም ፤ተዋቂና ማንም የማይነከ ሰው ነኝ ብለህ ልታስብ ትችለለ ነገር ግን አንተ አንድ ሰው በምትነገርው ሚልዮኖች ልፋጁ እንደሚችል መገመት አለብህ ፤ ታርክና እነውነት በማዘባት ደግሞ ፈጣሪም አይለቅህም፡፡ ከቅርብ እብሪተኞች መማር ትችላለ ፤ ማንም አይነካንም ጉልበት አለን ህዝቡን በዘለፋም ይሁን በጠለፋ ሲያሳቅቁ ድንገት ጌታ ከተፍ ልል ይችላል፡፡ በማወቅም ሆነ ባለ ማወቅ ለተፈጠረ ችግር በጣም በጣም አዝነናል፡፡
ለሁሉም ፈጣሪ የእውነት አምላክ ነውና የእጁን ይስጣል
እውነት ለመናገር ከሆነ ዲሞክራሲ ሰፍኖበታል ተብሎ ጣዋት ማታ ጆሮያች በሚያዶኖቅሩበት ሀገር እንዲ ዓይነቱ አሳፋሪ ድርጊት መታሰቡ መቼም ቢሆን ዬነሱ ሰው አንድ ሲሞት ለምድር ለሰማይ አቤቶታ ይገባል እኛ ላይ ግ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሲሰራ በኛው ምድር በኛው ሀብት እየከበረ ያለው ፋብርካ ሰፖንሰር በማድረግ ድጋፉን ስገልጽ የወደ ፊቱን ሁኔታ እንዴት እንደ ተመለከታ አልገባንም፡፡ የተፈደለት ሐረቄ እንዲ ነግድ ነው እንጂ የአንድን ብሔረሰብ ስም በማጥፋትና በማብጠልጠል ስፖንሰር እዲያፈላልግ አይዴለም፡፡ እንደ ተበለውንና ህዳር 29 እንደሚከበርለት ከሆነ ህግ ያለበት ሀገር ውስጥ ነው ያለነው፡፡ ህገ መንግስቱ ለ ቴዲ አፍሮና ለበደሌ ቢራ የሚሰራ ከሆነ እየገዙን ያሉ ባለ ጊዜዎች ጉዳዩን እንዴት እንደሚመለከቱ አልገባንም ፡፡
ማን ያውቃል አሁን ህዝቡ ሀገር ሰለም ነው ምንም ችግር የለም ብሎ ሰላማው ኑሮውን በመኖር ላይ ይገኛል ይህ የልተዋጠላቸው የነፈጠኞችኛ የቀድሞ ስረዓት ናፋቂዎች ህዝብን ለመበጥበጥ ትንኮሳ በማድረግ ላይ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ ለነገሩ እየገዙን ያሉትም ሆን ብሎ ዝም ያሉት ይህንኑ ደግፎ ልሆን ይችላል፡፡ የኦሮሞ ህዝብ ደደብ ሀበሾች እንደሚያስቡት አይደለም ዘረኝናት አያቅም ነጻነት ነው እንጂ፡፡ የማይረበውን ሀውልት በአኖሌና ጨለንቆ ላይ ከመሰራት ይል የቀድሞ ስረዓት ነፋቂዎች ልክ እንደ ቴዲ ዓይነቱ ላይ የማንነት ሀውልት በተሰራ ነበር፡፡ ለነገሩ አንድ ተራ አዝማሪና ለፈ ላፊ የኦሮሞን ህዝብ ማንነት አይቀይረም ታርኩንም አያጠፋም ትርፉ ትዝብት ነው፡፡ ይልቅ እንድ እየነካካችሁን ቂምና ጥላቻ ህዝቡ ውስጥ በትነዙ ጥሩ ነው፡፡
ማወቅ ያልቻላችሁት ነገር ግን ዛሬ የነጻነት ጭላንጭ በታየበትና ህዝቡ ማንነቱን ጠንቅቆ በአወቀበት ዘመን ይቅርና ትላንት አሁን ቴዲና በደሌ ቢራ በጋራ ለሚያለቅሱለት ሚንልክ ዘመነ መንግስት እንካን አልተንበረከከም የእነሱ አልሰነፈ ባይነት ነው ለዛሬ ማንናታችን ያበቃን፡፡ እነንተ ሰትጠሩ አቤት የሚትሉላትን ኢትዮጵያ ቢሆን የሁሉም ብሔረስብ የጋራ ውጤት ነው እንጂ ቴዲ አፍሮና በደሌ ቢራ የገነባት አየረደለም፡፡ የም ሆነ ይህ እኛ በሰላማዊ መነገድ የቴዲ ተብዬና በደሌ ቢራ ሥራን እንቃወማሌን፡፡ ዠሬም ትላንትም እኛ ከዝንብ ማር አንጠብቅም ቴዲም በደሌ ቢራም ያው ነቸው፡፡
አንድን ህዝብ አደባባይ ቆሞ መሳደብ ግን ህግ ባለበት ሀግር ያስጠይቃልይህን ገሽ ቴዲም የሚያውቁት ይመስለኛል ፤ ለነገሩ መማር ብችል ኖሮ ከከዚህ በፊቱ ይማር ነበር እሱ የሚያለቅስለት አትዮጵያዊነትም አንድን ህዝብ በመሳደብና በመዝለፍ ሳይሆን ሁሉንም በእኩልነት በማየትና ፍቀር በመስጠት ነው፡፡ የተበለው ጦርነት እሱና የእሱ ገሸ ›ËÓ_‹ እንደሚሉት ቅዱስ ጦርነት ሳይሆን እርኩስና የዘር ማጥፋት የተሰራበትና ለወደ ፊትም እነ ቴዲ በዚሁ ከቀጠሉ ለዘር ማጥፋት መነሻ የሚሆን ነው፡፡ በዚያ ዘመን በምድራችን ለይ ከተደረገው አሰቃቂና ጭካኔ ከተሞለበት ሁሉ ጦርነት የአኖሌና የጨለንቆ ጦርነት ነው፡፡ በሌላ ዐለምና በሰለጠኑትና እንደኛዎቹ አውሬ በል ሆኑት ሀገሮች ውስጥ ሴቶች፤ህጸናቶች ና አዛውነቶች በጦርነት ላይ ስለማይሰተፉ አይነኪም ፡ በእነዚህ ጦርነት ግን የሴቶቻ ጡትና የሽማግሌዎች እጅ ነው የተቆረጠው፡፡ ከቤት መሄድ ስለማይጭሉ ማለት ነው፡፡ ወገኖቼ ይህ ነው ተዲያ ቁዱስ ጦርነት፡፡eËS` uU”U ›Ò×T> ÃU× ¾Ù`’ƒ pÆe ¾KU:: ህልና ለለው ሰው ጦርነት ቅዱስ አይሆንም ለበደሌና ለተዲዎች ግን ነው ፡፡
Owwww ye alemachen talaku bloger. Ekekam neh. wenbede!
ya yefesesew dam indam malas takaleh.be sew dam iyatefalasafk new.we bored of your false bilble propaganda.it is your priests who who tell us the bilble killling human being is sin.after a while they were come back as war general and murder our ancestors.this is ur legacy.
Minilik komata new kenesu gar mewadadar atchilm.antem bilo metshaf kidus awak.
Fuck u Abel.our Fathers and Forefathers flesh and blood will speak what happened.
Beaman you are simply awesome !
I hope you will write a good book about this topic. You seem a very reasonable, balanced and matured writer. You just mentioned all the things that i always observe while people argue about our ancestors.
Thank you and see you soon !
I don’t think the above opinion is Teddy Afro’s. He might pay for it. የመጽሄቱ አዘጋጅ ወይ ልጁን ተጣልቶት ይሆናል እንጂ አሁን ማስተካከያ ተብሎ የተሰራጨውን ቃለምልልስ ማንም ደደብ የሆነ አዘጋጅ አያስቀርም ነበር፡፡ ለአንዳንድ ሆደባሻ የፌስ ቡክ ወገኖች ግን ማንንም የማይጠቅም አካሔድ እየሄዳችሁ ስለሆነ ባለፈ ታሪክ አትታመሱ ልላችሁ እወዳለሁ፡፡
Teddy is supremely naive to believe story like, King Minilik washed the feet of Tona. His assessment of Menilk is based on afe-tarik made up to serve a political purpose. Tedi is neither politician nor historian. He is a singer and therefore should be forgiven. My advice for him is that he should refrain himself from commenting on things that he does not have any knowledge about.
ቅዱስ ጦርነት ብትሉ ከወንጀል ህግ ቁጥር 538እስከ548 ያለውን የተላለፉ የመ/ቅዱሶቹ ቅዱሳን ነፍስ-አጥፊዎች ትዝ አሉኝ!!!ይኸው ከነማስረጃው፡
5. ጳውሎስ፡ የሐዋ.ስራ7-58፣በእስጢፋኖስ ሞት ግብረአበር ነበር
4. ዮፍታሄ፡መጽ.መሳ11-30፣ልጁን ሰውቱዋል
3. ሙሴ፡ ግብጻዊውን ለሀገሩ ልጅ አግዞ ገድሉዋል
2. ዳዊት፡ ለሴት ሲል የሰው ህይወት እንዲጠፋ አድርጉዋል
1. እግዚአብሄር፡ በ1ኛ ሳሙ15-3 የተዘረዘረው ዘር ማጥፋት እንዲካሄድ ቀጥተኛ ትእዛዝ ሰጥቱዋል.ስለሆነም ምኒልክ ለፍርድ የሚቀርቡ ከሆነ እነዚህ ተጠርጣሪ ቅዱሳንም አብረው ይቅረቡልን!!!
Dear Beaman,
I do really appreciate your insightful comments. I think this is expected from a healthy/positive thinker Ethiopian at this time. Otherwise we will end up in an endless loop talking about from two opposite sides. If really people/politician… want to know/understand and have logical dialogue, discussion, and stand the very first thing to do is just to read in depth. I think you have done so. I would like to learn a lot from you because you are not biased and you put things as it happened and I feel that you don’t have hidden agenda or you are not interested in hair splitting/division. Alike others who wants to finger point on others.
Thanks and I wish if you can post us your email address for knowledge sharing. We are fade up of ALL EPRDF pro and Opposition Pro writers. When people get matured they don’t make others a subject as we have seen here. As the first sister(dagem) advised Daniel, it is really really not good to see such talented writers being pro of one side and become whistle blower. Let us Unite, let us write that will make us more united than separate us, let us know the fact for the good to happen in the future but not to hammer others.
Otherwise we will end up gambling with ourselves. United we stand!
Thanks,
Yonas
Is it necessary to focus on our differences and become fragmented and weak, fighting each other? i don’t think so! Dani please, there are so many things that we can discuss for our mutual benefit rather than wasting time on rhetoric.
sile minilik metfo gon sitsaf lemindinew yemiyanqoratitachu? degum metfow yiwera tarik indal yoqemet ingi tekuakulo meqreb yelebetim …….so fans of minilik dont be upset, minilik is human and can make mistakes he had his own strong and weak sides at his time ….
ዳግም፡ ምን ነካሽ, ፍቅር’ኮ በጉልበት አይመጣም። ዛሬ ተሰደሽ ከእንግሊዞች ጋር አብረሽ መኖር የቻልሽበትን ያህል በዓረቦች መዋረድሽንም ባትረሺ ጥሩ ነው። ከእንግሊዞች ጋር አብረሽ የምትኖሪበት ምክንያት እንግሊዞችም አንቺን በፍቅር ተቀብለው ስላኖርሽ ይሆናል። ዓረብ ግን እንደ አህያ ፈሳብን፤ የድንቁርናውን መዓት አፈሰሰብን፤ ሰው አይደሉም እስከማለት ደርሰናል። አሁን ያደረጉት ተግባር እንስሳ አድርጓቿል፤ መላው ዓለም አውግዟቿል። ይህ ምን ጊዜም መጥፎ ታሪክ መሆኑን የምትገነዘቢ ይመስለኛል። ከጊዜ በኋላ ዓረቦች ካሉበት አህያነት ተነስተው ግማሽ ሰው ሲደርሱ እኛም ደህና ደረጃ ላይ ስንደርስ ታሪኩ መነሳቱ አይቀርም። ያኔ ግማሽ ሰዎቹ “እኛ ያንን ያደረግነው’ኮ የዜጎቻችን ስራ-አጥነትን ለመቅረፍ እንጂ ኢትዮፕያውያንን ጠልተን አልነበረም፤ እንደዛ በማድረጋችን የሀገሬውን ሰው ባለ ስራ አድርገናል። በመሆኑም ማንም መንግስትና ህዝብ ለሀገሩ የሚያደርገውን ነበር ያደረግነው፤ ምንም ስሕተት አልፈጠርንም” ይሉሽ ይሆናል፣ ያኔ ትኒሽም ቢሆን እንደ ሰው መናገር ስለሚችሉ። እየተባለ ያለው ምንሊክ አንቺ የምትኮሪበትን ያህል ፈሳብን፤ ሰውዬው እውነት ሰው አልነበረም የሚሉ ህዝቦች ብዙ ናቸው። ፍቅርንና አንድነትን ለማምጣት የሰውን ብልት መቁረጥ አያስፈልግም ነበር። በጉልበት አምበርክከው በስራቸው የወደቁትን አቅም የለሽ ህዝቦችና መሪዎችን ተርፎ የፈሰሰ ግፍ መፈፀም አያስፈልግም ነበር፤ ዛሬ አንቺ አምረሽ የምትጠዪው አንድን ህዝብ እንደ ህዝብ ያለ ስም ስም እየሰጡ ማዋረድ ከልክ በላይ ነው የሚሉ ህዝቦች አሉ። ምንሊክ ለግል ስልጣኑ ሳይሆን እውነት ለሀገር ህልውና የቆመ መሪ ነበር ከተባለ የኤርትራን ህዝብ ከጣልያን ጋር አድርጌያለሁ የሚለው ጠርነት ላይ ለሽያጭ ድርድር ባላቀረበ ነበር። አፄ ቴድሮስ’ኮ በብዙዎች ኢትዮፕያውያን የሚያከበሯቸው ለሀገር አንድነት ሲሉ ሳይሆን አቅማቸው ተዳክሞ በጠላት እጅ ላለመውደቅ ሲሉ እራሳቸውን ስለገደሉ ነው። ምንሊክ እንዴት ኤርትራን ያህል ህዝብና ሀገር ከስልጣኑ ጋር አያይዞ ለሽያጭ ሊያቀርባቸው ደፈረ? ይሄ ብታቆሚውም ብታስተኚውም መጥፎ ስህተት ነው። እዚህ ላይ አንድ ነገር ልንገርሽ፡ የምንሊክ ደጋፊዎች ነን የሚሉ ወግ አጥባቂዎች “አዎ! ይህ የምንሊክ ስህተት ነበር። አፄ ምንሊክ በጎ የሰሩትን ያህል ጥፋትም ሰርቷል። አሁን ግን ያን ታሪክ መቀየር አለብን” ቢሉ ኖሮ እቺን አገር ከዓደዋ ድል በላይ አንድ ያደርጋት ነበር። አሁን ግን ምንሊክን ስላደነቁ በመንግስት ላይ ያላቸውን ጥላቻ የሚወጣላቸው እየመሰላቸው እንደውም ከሀይማኖት ጦርነቶች ጋር እያመሳሰሉ በህዝብ ላይ የደረሰውን ግፍና ደም መፋሰስ ቅዱስ ጦርነት ነበር፤ ሊቀ-መላኢክቱም ምንሊክ ነበር እያሉ ሲሰብኩ እንዴት ነው ሀገርን በፍቅር አንድ የሚያደርጉት??? አንዳንድ ጊዜም በማያውቁት ታሪክ ውስጥ ገብተው ስሜታቸው ስለነገራቸው ብቻ ነጭን ከጥቁር፣ ቀዩን ከአረንጓዴው ጋር መደበላለቁ’ኮ ለውድቀትና መለያየት እንጂ ለፍቅር አይሆንም። ደርግም’ኮ ለሀገር አንድነት ቆሜያለሁ ብሎ ነበር ያን ሁሉ ግፍ የሰራው። ስለ አንድነትና ስለፍቅር እየዘመሩ ከሚያርዱኝ ሰዎች ስለ ጥላቻና ስለ መበታተን እያወሩ የማይጎዱኝን እመርጣለሁ፤ ምክንያቱም እኔ እና የሚቀጥለው ትውልድ ካልተጎዳን ለአንድነትና ፍቅር እደርስበታለሁ። ከዚህ ሁሉ በላይ ግን አሰልቺ የአንድነትና ፍቅር ጩሀትን እያስተጋቡ በተግባር ግን የመበታተንና ጥላቻን የሚያጎለብቱ ስፍር-ቁጥር የሌላቸው መሰሪ ተግባራት መስራት ሳይሆን ስህተትን እንደ ስህተት ተቀብሎ፤ በጎም ታሪክ በበጎነቱ ተቀብሎ ለጋራ መስራትን የሚያክል የአንድነት ሀይል የለም። ዘፋኙ ቴድሮስ ታሪኩን በትክክል የሚያውቀው አይመስለኝም፡ በቃለ ምልልሱ ላይ የማላውቀው የአውሮፓ ሀገር፣ የማላውቀው ግለሰብ፣” ወዘተ የሚል አይቻለሁ። ጉሮሮው ለእንጉርጉሮ ስለሚመች ብቻ ስሜቱ እንደነገረው ታሪክን ማብኳቱን ግን ተያይዞታል። ይሄ ለኔ በቁም መሞት መስሎ ይሰማኛል። ካላወቀው አላወቀውም! አንድን ጉዳይ ሳያውቁት ቀርተው እንዲያውቁ መጣርና መጠየቅ እንደ ጋለ ብረት የሚያስፈራ እና የሚያዋርድ አይደለም፤ ነውር የለውም። ምንም ሳያውቁ ወይም ትኒሽ እውቀት ይዘው በድፍረትና በጥሩ ድምፀ-ጣዕም መጮህ ነው የውርደት ሁሉ ውርደት የሚሆነው። ምክንያቱም በማያውቁት ጉዳይ ላይ መሪ፣ አስተማሪና ሰባኪ መሆን ማለት ትክክለኛ የውድቀት፣ የድንቁርና እና የሀጥያት መንገድን መከተል ማለት ነው።
lemakakas yadergekew tiret turu bihonm tinish yalanebebkachew negeroch beteley minilkin kewekeskibet larimh….yohannisn alemagezachewn betemelekete ……be atse yohannies leni bileh sayihon le hayimanoth sitel tewaga. yemil tizaz dersachew mulu tor yizew gonder akababi seferew tezegajchalehu yemil meliket silku meliktegnochu sile minilk tor aganaw bemawuratchew niguse negestu ke sudan melse eninm ayilkegn bemil fracha tewew temeles endalachew bezaw gojjam zorew ke tekilehaimanot gar tenegagerew yeyazutinm mesari be yohannies lewedemebachew mitk setewu enedtemelesu……ertreana djbouty esachew siltan sayizu gena itlay ras alula dogali lay dil karegachew behal le yohannnies kesew esun kemerb milash asenestew ertrea yemil sim awutitew megezat yejemerut be yohannies gize mehonun bizu metsaft lay alelh. ye mirkogn ayayaz ayidelem yerasachewun gud talianochunm endit bekiber endemelesu yematawuk kehon yasazinal. akatelu lalkew keyet endametahew bitekumen.
What astonishes me is not the very idea of Teddy Afro’s alleged interview but the the very motive of the blogger- Daniel, blowing the wind of animosity which i thought is sinister and awful. But it has to be clear that I didn’t mean Teddy Afro was right,but I mean that despite fact that it only reflect the opinion of the individual and/or might misinterpreted in the way intended to convey a message of threat ; why do u became busy in distributing the bullets of hatred? which is neither a discovery nor an intelligence but a wicked motive. I am really ashamed of u!
u are so nasty…grow up ….
ታዲያ ቅዱስ ነበር ያለበትን ምክንያት እኮ ገልጾአል ምንም የሚያስወቅስ ነገር ለውም “ያንን ቅዱስ ያልኩትን ጦርነት ሊያስነሳው የቻለውም ይኸው ግንዛቤ ይመስለኛል” ብሎ ቅዱስ ያለበትን ምክንያት እንደሚከተለው አቅርቦአል “ ከማረኳቸውም በኋላ እግራቸውን እያጠቡ ‹‹የእኛ አንድ አለመሆን፣ ጠንካራ ማዕከላዊ መንግሥት አለመመሥረታችን፤ የጋራ ለሚሆነው ጠላታችን ጥቃት አሳልፎ የሚሰጠን አደገኛ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። በዚህ ምክንያት ነው ወደ አንተ ጦር ያዘመትኩት እንጂ ሥልጣንህን ለመቀማትና በአንተ ላይ ለመግነን… ፈልጌ አይደለም። ማእከላዊ መንግሥታችንን ማጠናከሩ ግን ሁላችንንም የሚጠቅመን ነው። አገራችንን፣ በሕላችንን፣ ታሪካችንን፣ ቋንቋችንን ጠብቀንና ድንበራችንን አስከብረን ለመኖር ይረዳናል›› ነበር ያሏቸው። እንግዲህ ምኒልክ ንጉሥ ጦናን አሏቸው እንደሚባለውም ይሁን በሌሎችም ብሔራዊ ክብርንና ማንነትን አስጠብቆ ለመኖር በሚያስችለው ፖለቲካዊ መመዘኛ ሲታይ፤ ቋንቋንም ጠብቆ ለመኖር እንኳ ቢያስፈልግ… ከጠላት ማንኛውም ጥቃት ራስን መከላከል ወይም ማስከበር በሚቻልበት አቅም መጠን መኖርን የግድ ይላል። ምናልባትም በዚያን ጊዜ እንደ ምኒልክ ያለው ባለውለታ ተፈጥሮልን… ከጠላት ተጠብቀን መኖር ባንችል ኖሮ፤ ዛሬ የምንጠራበት ስማችን ኢትዮጵያዊ ቀለም ሊኖረው አይችልም ነበር። እኔም ቴዎድሮስ፣ ሌላውም ምኒልክ፣ ጥላሁን፣ ፀሐይ… አንባልም ነበር። የነበረው ቋንቋችን ሁሉ ይጠፋ ነበር። ግን ቋንቋንም፣ ባሕልንም ሰብስቦ ለመያዝ፤ ከዛም በላይ ደግሞ ሕዝብን አስተባብሮ በአንድነት ለመሥራት፤ የአንድነትን ታላቅ ዋጋ ቀድሞ መገንዘብ ያስፈልጋል። ያንን ቅዱስ ያልኩትን ጦርነት ሊያስነሳው የቻለውም ይኸው ግንዛቤ ይመስለኛል።” በእኔ እምነት ሌላ ማብራሪያ የሚስፈልገው አይመስለኝም ዝም ብሎ ጦርነቱን ቅዱስ ነው አለ ከማለት እንደዛ ያለበትን ምክንያት ለመረዳት ሙሉ የሰጠውን ምልልስ ማንበብ ተገቢ ይመስለኛል ፡፡ እሱም ቅዱስ ነበር ያለበት ምክንያት ከላይ ከጠቀሰው የምንሊክ ተግባርና ንግግር እንጂ ከሌላ አይመስለኝም ፡፡ ቅዱስ ነው ብሏል ብሎ ነጥሎ ቃሉዋን አውጥቶ ግን አላስፈላጊ አስተያየቶችን ማቅረብ የግንዛቤአችን ደረጃምን ያህል እንደሆነ የሚያሳይ ወይንም ሆን ተብሎ የልጁን ስም ለማጥፋት የሚካሄድ ሴራ ካልሆነ ለዚህ ምንም አይነት ምክንያት ማቅረብ የሚቻል አይመስለኝም፡፡
የምኒልክ ምርጥ 10 በጎ ተግባራት
1. አድዋ!!!!!
2. የስራ አዋጅ(ሸክላ ሰሪና ቀጥቃጭን ያስከበሩበት)
3. ዘመናዊ ት/ት እና የት/ት አዋጅ(በዚህ አዋጅ ልጅን አለማስተማር 50 ብር ያስቀጣ ነበር)
4. ቴክኖሎጅ፡ ባቡር፣መኪና፣ሆቴል…….
5. ዲፕሎማሲ፡ የውጭም የውስጥም
6. ይቅር ባይነት፡ ላሰረው ሰው(ዐጼ ቴዎድሮስ)ሞት ተዝካር እስከ ማውጣት የደረሰ
7. ሀገርን ማስፋት፡ ከዐጼ ዮሀንስ የተቀበሉዋትን ኢ/ያ 3 እጥፍ አስፍተዋት ነው ያለፉት
8. ሀገር ማረጋጋት እና ወሰን ማስከበር፡የሀገራችን ድንበር የተከለለው በእሳቸው ጊዜ ነው
9. ሰው ማፍራት፡እነ ፊ/ሪ ሀ/ጊዮርጊስ፣ባልቻ፣ራስ መኮነን…..
10. ዘመናዊ ቢሮክራሲ መፍጠር፡ ሚኒስትር መ/ቤቶችን አቁዋቁመዋል
የዐጼ ምኒልክ 5 እንከኖች
1. ዐጼ ዮሀንስ በመተማ ከሱዳን ጋር ሲዋጉ ለማገዝ ፍላጎት አለማሳየታቸው
2. ኢሰብዐዊ ቅጣቶች፡ራስ በዛብህን በቁሙ ማቃጠላቸውና በአድዋ የተማረኩ 500 ኤርትራውያንን እጅና እግር በመቁረጥ መቅጣታቸው
3. በመስፋፋቱ ወቅት የደረሱ የጭካኔ እርምጃዎች፡ በአርሲ፣ጨለንቆ….
4. የዐጼ ዮሀንስን ወንበር ለመንጠቅ ሲሉ ከኢጣሊያና ፈረንሳይ ጋር በፍቅር ወድቀው አሁን ላለንበት የባህር በር-አልባ ሀገር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረጋቸው
5. በጦርነቱ ወቅት ከመጠን በላይ ዲፕሎማት ልሁን በማለት ለውሳኔ ስለሚዘገዩ አላስፈላጊ መስዋእትነት መከፈሉ
ምኒልክን የሚያወግዙ ሰዎች የማያገናዝቡአቸው 10 ነጥቦች
1.ይሄን ሁሉ ብሄር ቀድመው በሀይልም ሆነ በዲፕሎማሲ ባንድ ጥላ ስር ባይሰበስቡት ኖሮ ቅኝ ገዥዎች እያናጠሉ ሁላችንንም ይገዙን እንደነበረ
2.በዋናነት በሰሜን ሸዋ አማሮችና በሸዋ ኦሮሞዎች የሚመራው ጦራቸው እንደ ነጭ ወራሪ በቀለም ልዩነት የዘር ግንብ የሚገነባ ሳይሆን ካስገበረው ህዝብ ጋር ተጋብቶ፣ቁዋንቁዋውን ተላምዶ፣ሀገሩን ሀገሬ ብሎ ኑዋሪ መሆኑን. በዚህም የተነሳ ዛሬ ሁሉም የኢ/ያ ብሄሮች በነጮች ፊት ቀና ብሎ እንደሚሄዱ
3. የያዙዋቸው ግዛቶች እንደ ሀገር ህልውና ያልነበራቸው ስለነበሩ ምኒልክ መልስው ወደግዛታቸው ጠቀልሉዋቸው እንጅ በቅኝ ግዛት ያዙዋቸው የሚባለው ትረካ ያው ትረካ እንደሆነ
4. የስኬት ጉዳይ እንጅ መስፋፋት የሁሉም ብሄሮች አጀንዳ እንደነበረ
5. በተለይ የኦሮሞ ምሁራን የእነሱን የassimilation ታሪክ በደግ እያነሱ ምኒልክ ማንነታችንን ጨቁነዋል ሲሉ የሚያቀርቡት double standard መከራከሪያ
6. ወቅቱ የመገበርና የማስገበር እንጅ የሪፈረንደም አለመሆኑን ከጀርመኑ ቢስማርክና ከጣልያኑ ጋሪባልዲ ታሪክ እንኩዋ አለመማር
7. በነጮች የተገዙትን እነ ሶማሊያና ሩዋንዳን እያዩ ምኒልክ ከሚገዛን በነጭ በተገዛን ብሎ መመኘት
8. በምኒልክ አስተዳደር ውስጥ የነበሩ የሌሎች ብሄር አባላትን ተሳትፎ በማሳነስ አስተዳደሩ የአንድ ብሄር ብቻ እንደነበረ ማስመሰል
9. የንጉስና የባላባት አስተዳደር በሁሉም ብሄሮች ከሞላ ጎደል ቢኖርም ምኒልክ እንዳመጡት አድረጎ ማስቀመጥ
10. ምኒልክ በኦሮሚያና በደቡብ ያደረጉት ጦርነት ከሰሜን ህዝቦች ጋር እንዳደረጉት ሁሉ ግዛት ከማስፋት ባለፈ ሌላ አላማ እንደሌለው እየታወቀ ጦርነቱ ዘር ለማጥፋት እንደተደረገ ማስመሰል
በምኒልክ ደጋፊዎች የሚነሱ ተገቢነት የሌላቸው አቁዋሞች
1. ምኒልክ በደግ ብቻ እንዲነሱ መፈለግ
2. የምኒልክን በደሎች ሁሌ በዘመን ማላከክ
3. የመስፋፋቱ ጦርነት ባመጣው ጣጣ ባለመሬቶች ወደገባርነት መቀየራቸውን መዘንጋት
4. ዐጼ ምኒልክ በዐጼ ዮሀንስ ላይ የሰሩትን ሸፍጥ ዐጼ ዮሀንስም በዐጼ ቴዎድሮስ ላይ ስለሰሩ የተለመደ ነው በሚል ዐጼ ምኒልክን ይቅር ማለት
5. በጅቡቲና በኤርትራ ጉዳይ በክፉ እንዳይነሱ መፈለግ
Why do you Blame him, the writer! Blame the one who have said it, Teddy “Afro”!
You are stupid beyond words.
ምን አጠፋሁ?
ይህ ብሶት የመነጨው ከጥቂት ግለሰቦች ቢኖንም አንተ ግን ለፖለቲካ መጠቀሚያክ ስትል ነገር እያካረርክ በፍቅርና በመከባበር አብሮ ለዝንት አመት የኖረውን ህዝብ ለማቆራረጥ አትሞክር ። ከቻልክ እንደውም መልካም ነገርስ አንስተህ ህዝብን የሚያቀራርብ አምላክም የሚወደውን ስራ ለመስራት ሞክር በህዝብም ዘንድ እነደ ቴዲ ፍቅርን በአምላክም ዘንድ መባረክን ታገኝበታለህ ። ስማ ዳንኤል ዛሬ እኛ ኢትዮጵአውያን ያለተሰደድንበት ያልከተምንበት የ አለሚቱ ክፍል የለም ። በዚህም ሁኔታ አለም ካቀራረበችን ከ ነጩም፤ ከጥቁሩም፤ ከ ኤዥያኑም ፤ ከስፓኒሹም… ህዝብ ጋር አብረን በፍቅር እንኖራለን ። እንግዲህ አስበው….ከማናውቀው እና በቋንቋም ሆነ በከለር ከማይመስለን ህዝብ ጋር …ቋንቋቸውን እየተማርን የበሉትን እየበላን፤ መስለን እንኖራለን ይህ የሁሉም አለም ህዝብ ጠባይ ነው ብልህ የተሳሳትኩ አይመስለኝም ምክንያቱም ይሕው አረቡም፤ ህንዱም ስፓኒሹም መቶ የሚከትምባት አሜሪካን ሃገር የተለያዩ ህዝቦችን አስተናግዳ በፍቅርና አንዱ አንዱን በማክበር ታስተዳድራለች። እና ታዲያ እኛስ ኦሮሞው የኛ፤ ትግሬው የኛ፤ አማራው የኛ ፤ጉራጌው የኛ፤ አፋዩ ጋምቤላው የኛ ባጠቃላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ ሁሉ የኔነት ስሜት ተሰምቶን ለምን ስህተት እንዲደገም ጥረት ከማድረግ ይልቅ ፤ ስህተት የምንላቸውን እያረምን በፍቅርና በአንድነት በመሆን ለሃገራችን ሰላም መከበር ዘብ የማንቆም ። ተው ዳንኤል በሓላ ይቆጭካል ። ሁሉም ሃላፊ ነው ። ታሪክ ግን ከትውልድ ትውልድ ይተላለፋል ። ይህ የታናሽ እህትህ ምክር ነው ። አምላክ ካንተ ጋራ ይሁን ።