(Daniel Berhane)
ከትላንት በስቲያ – የዘመን መለወጫ ዕለት – ጀምሮ በፌስቡክና ትዊተር <<ርዕዮት ዓለሙ የረሀብ ዐድማ ጀመረች>> የሚል ዜና ሲሰማ ቆይቷል፡፡
ስለሁኔታው የማረሚያ ቤት አስተዳደርን ዛሬ በስልክ ጠይቄ ‹‹ከውጭ የሚመጣላትን ምግብ እየተቀበለች ነው›› ብለውኛል፡፡ በራሴ ላረጋግጥ የምችልበት መንገድ የለም፡፡
ለረሀብ አድማው መነሻ የተባለው፡- ማረሚያ ቤቱ ሰሞኑን በርዕዮት ላይ የጣለው ዕግድ ነው፡፡ ከአባቷ፣ እናቷ እና የንስሀ አባቷ ውጭ ጠያቂ እንዳታገኝ መከልከሏ፡፡
ያነጋገረኝን የማረሚያ ቤት አስተዳደር ሀላፊ፡- ‹‹ለምን ጎብኝዎች ላይ ገደብ አደረጋችሁ›› ብዬ ጠይቄያቸው ነበር፡፡
ጉዳዩን ሳያምንም ሳይክድም (ያመነ ይመስላል)፡- ‹‹ማረሚያ ቤቱ ሕግን አልጣሰም፣ በታራሚዎች ላይ የዲሲፕሊን ዕርምጃ የመውሰድ የሕግ ስልጣን አለው›› አሉኝ፡፡
የወንጀል ሕጉን፣ የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ማቋቋሚያ አዋጅንና ደንብን ይዘትና መንፈስ ስለማውቀው (ከሥር ተመልከቱ) በዚያ ላይ ሳልከራከር፣ በድፍኑ፡- ‹‹ሕጎቹ ጥቅል ናቸው- ማስፈፀሚያ ደንብ ወይንም መመሪያ አላችሁ ወይ›› ብዬ ጠየቅሁ፡፡
በሕጉ በግልጽ ያልተቀመጡ መብቶችን በተመለከተም ቢሆን እንኳን ‹አንድን ታራሚ ከሌላ ታራሚ በተለየ ለማስተናገድ ግልጽ አሠራር ያስፈልጋል› በሚል ዕሳቤ ያነሳሁት ጥያቄ ነበር፡፡
‹‹አዎ ማረሚያ ቤቱ የውስጥ መመሪያ አለው – ያን ተከትለን ነው የምንሠራው›› አለኝ፡፡
በስልክ ከዚህ በላይ መረጃ መጠየቅ አዳጋች ስለሆነ አመስግኜ ተሰናበትኩ፡፡ (እንደአስፈላጊነቱና ከተባበሩኝ ዝርዝር መረጃዎችን – ለሌላም ግዜ እንዲሆን – ሰኞ በአካል እጠይቃለሁ)
ሌላው ተያይዞ የሚወራው ወሬ፡- በቅርቡ በሙስና ተጠርጥረው የታሠሩት ወ/ሮ ሀይማኖት እየዛቱባት በፍርሀት ውስጥ ትገኛለች የሚል ነው፡፡ አንድ ዕድሜያቸው በ40ዎቹ መጨረሻ ላይ የሚገኙ፣ ባለትዳርና የልጆች እናት – እንዴት ለአንዲት ወጣት ስጋት እንደሚሆኑ ስላልተዋጠልኝ፤ ጥያቄውን አንስቼ ራሴን ማስገመት ስላልፈለግሁ አልፌዋለሁ፡፡
በነገራችን ላይ፡- አንዳንድ ሰዎች ትንሽ የተምታታባቸው ይመስላል፡፡ የረሀብ አቆም አድማ ማለትኮ አድመኛው ‹‹ምግብ አልበላም›› አለ/ች ማለት እንጂ ‹‹ምግብ ተከለከለ›› ማለት አይደለም፡፡
እንደሚባለው ርዕዮት ዓለሙ የረሀብ አድማ መትታ ከሆነ፤ ተቃዋሚዎች ለመንግስት ማለት ያለባቸው ‹‹እረ እቺ ልጅ እንዳትሞትባችሁ ጥያቄዎቿን ፈጽሙላት›› እንጂ ‹‹መንግስት በረሀብ ሊገላት ነው›› አይደለም፡፡
ለማንኛውም አዲስ መረጃ ሲገኝ እንአግባቡ አቀርብላችኋለሁ፡፡
********
ante betam mitgerm sew new be’ewnet ehetih bithon endezi attsifim neber …tawkalachu enante EPRDF kekito yeserachu nachu anferdibachum ante gin le simu gazetegna neh …gin lemn le hilinah atseram esti esua set nat le hagerua min yahl endemitichneq aytehal endante bitagobedid eko tibeltihalech ,,,,,,gazetegna malet min malet endehone ene alnegrihim tawkewalwh tadya lemn ye mahiberesebun dimts atasemam lemn yetecheqonutn dimts atasemam ???le birr lemn timotaleh…balefew sile eskindir nega yehone sew negeregn bileh yetsafkewn anbibe azenku lemn endehone tawkaleh ewnetun debikeh endezi widaki wishet ena minim techbach yalhone neger bemetsafh esti erasih lemn chek ataregm IFJ hone CJ …bediregetsachew lay yetenagerutn ante gin bewishet egnan litatalen timokiraleh …..lemn??..esti kom bileh asib ene yihen sinegrih ende asteyayet new…wishet yatefahal enji ayatsedkihim pls atwash….demo eko niket new ante mereja ayagegnum bileh new ende endezi mitikelilodobin we r ethiopians mengist bihed mengist yimetal ,,,,,,,ye hilinah tegezhi hun………lastly..UR BLOG CAN NOT BE THE LEADING ITS JST THE LIER…
yemotik…. minale zim betel….afihin bekefetk kutir yechinkilatehin badonet new yemetasayen