የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ግንባታ 34 ከመቶ ደርሷል

(ጥላሁን ካሳ)

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ግንባታ ፕሮጀክት ዋና ዋና ስራዎች ክረምቱ ከመጠናከሩ በፊት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው አለ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን።

ኮርፖሬሽኑ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገረው በዚህ አመት ይጠናቀቃል ከተባለው 40 በመቶ ስራ እስከ ግንቦት መጨረሻ 34 ከመቶ በላይ የሚሆነው ተከናውኗል።

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ፕሮጀክት ከሚያልፍባቸው ቦታዎች መካከል በዋነኛነት ጊዮርጊስ አካባቢ በሚገኘውን የዋሻ አናት ላይ አፈር የማልበስ ስራ ተከናውኗል።

ስራውን ለማፋጠን እስከ ምሽት ድረስ በመስራት ርብርብ እየተደረገ በመሆኑ የኮንክሪት እና ብረት ማልበስ እንዲሁም የሀዲድ ስራው እስከ ሀምሌ አጋማሽ እንደሚጠናቀቅም ነው ኮርፖሬሽኑ የገለጸው።

ሳሪስ አካባቢ ባለው የባቡሩ ሳይትም በአካባቢው የብረታ ብረት ማማረቻ ውስጥ የሀዲዱ ርብራብ እየተመረተ በመሆኑ ስራው እንዲቀላጠፍ አስተዋጽአ እንዳለው ታምኖበታል።

በፒያሳ ፣ ጎጃም በረንዳ አውቶብስ ተራ ለሚያልፈው የባቡር መስመር ስራም ጎጃም በረንዳ አካባቢ የመንገድ ዳር ቦታዎችን ለባቡር መስመሩ ምቹ የማድረግ ስራዎች በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።

ነባሩ የውሀ መስመር ከሜክሲኮ እስከ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ድረስ በአዲስ በመቀየሩም የባቡር መስመሩ ከትናንት እስከ ዛሬ ምሽት ድረስ ፤ ከስፖርት ኮሚሽን እስከ ቡና እና ሻይ ያለውን ቦታ በማጠር ስራው የተጀመረ ሲሆን ፥ እስከ ቡናና ሻይ ያለው ቦታም በመታጠር ላይ ይገኛል ።

**********

Source: Fana – June 19, 2013, titled “የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር መስመር ዝርጋታ ዋና ዋና ስራዎችን ከክረምቱ በፊት ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ ነው”

9.14540.489673
Daniel Berhane

Daniel Berhane

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago