በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሽ ዞን ያሶ ወረዳ የሚኖሩ የአማራ ብሄረሰብ ተወላጆችን ያለአግባብ አፈናቅለዋል ተብለው የተጠረጠሩ 28 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ፡፡
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ጋዎ ጃኔ ትናንት እንደገለጹት ተጠርጣሪዎቹ ካለፈው እሁድ ጀምሮ የተያዙት በቅርቡ በያሶ ወረዳ ለረጅም ዓመታት የኖሩ የአማራ ብሄረሰብ ተወላጆችን በማፈናቀል ወንጀል ተጠርጥረው ነው፡፡
በቁጥጥር ሥር የዋሉት 28 ግለሰቦች በክልሉ የካማሽ ዞንና ያሶ ወረዳ ከፍተኛ አመራር አባላት ፣ፖሊሶችና ሌሎችም እጃቸው በጉዳዩ እንዳለበት የተደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ወንጀሉ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ቡድን አቋቁሞ የተጠናከረ ምርመራ ሲያካሂድ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት የምርመራውን ውጤት መሰረት በማድረግ ሲሆን፤ ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት መታየት እንደጀመረ ኮሚሽነሩ ገልጸዋል፡፡
ሕገ-መንግሥቱን መሰረት በማድረግ እየተካሄደ በሚገኘው የፍትህ ሂደት በተለይ የአካባቢው ኅብረተሰቡ ትክክለኛ ማስረጃ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ አቶ ጋዎ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በክልሉ ያሶ ወረዳ አራት ቀበሌ ነዋሪ የነበሩ ሁለት ሺ የአማራ ብሄረሰብ ተወላጆች የተፈናቀሉት በሚያዚያ 2005 ዓ.ም ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት አብዛኞቹ ወደ ቀድሞው መኖሪያቸው መመለሳቸው መገለጹ ይታወሳል፡፡
**********
Source: Addis Zemen – June 19, 2013.
Previous:
* ቤኒሻንጉል:- በዜጎች መፈናቀል ሳቢያ የም/ቤት አባላት ታሠሩ
* ከቤኒሻንጉል ክልል ዜጎችን ያፈናቀሉ ኃላፊዎች ተባረሩ
* የቤንሻንጉል ተፈናቃዮች እንዲመለሱ ተወሰነ
* የቤንሻንጉል ተፈናቃዮች ተመፅዋች ሆኑ
* የቤንሻንጉል ፕ/ት: ተፈናቃዮቹ ኦሮሞዎችም ናቸው – አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን
* በቤንሻንጉል ክልል የሰፈሩ ዜጐች “ሕገወጥ” በሚል ተባረሩ
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…