አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ዛሬ ሰኔ 13/2005 በጽ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳሳወቀው ለ3 ወራት የሚዘልቅ “ሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” የተሰኘ ሕዝባዊ ንቅናቄ አውጇል።
ሕዝባዊ ንቅናቄው የአዳራሽ ስብሰባ፣ የተቃውሞ ሰልፍ እና የፀረሽብር ሕጉ እንዲሰረዝ የሚጠይቅ ፊርማ (ፒቲሽን) ይሰበሰባል። በዚህም በአዲስ አበባ 6 እና በክልል ደግሞ ለመጀመሪያ ዙር ዐሥር ስብሰባዎች ይካሄዳሉ።
የንቅናቄው ዓላማ የፀረሽብር ሕጉ እንዲሰረዝ፣ የዜጎች መፈናቀል እና የመሬት መቀራመት እንዲቆም፣ የሥራ አጥነትና የኑሮ ውድነት እንዲቀረፍ እና የንግዱ ማኅበረሰብ ውስጥ ፍትሐዊ ውድድር እንዲሰፍን መሆኑ በመግለጫው ተጠቁሟል።
የፓርቲው ተወካዮች “ሌላ ፓርቲ ሲያደርግ አይታችሁ ነው ወይ?” በሚል ለቀረበው ጥያቄ ሲመልሱ “ከሌላ መማር ለአንድነት ይጠቅመዋል እንጂ አይጎዳውም ሆኖም ስር እስክንሰድ ጊዜ ወስደን ነው እንጂ ዓመታዊ ዕቅዳችን ላይ ነበር። ፓርቲያችን በዕውቀት ላይ የተመሠረተ እንጂ በግብታዊነት አይሠራም” ብለዋል። የፀረ ሽብሩን ሕግ እንዲሰረዝ ስለሚያስፈልግበት ምክንያት ሲናገሩ ደግሞ የፀረ ሽብር ሕጉ ከአሸባሪዎች ይልቅ ዜጎችን ለማጥቃት የተዘጋጀ ነው በማለት ንቅናቄው ለሕዝብ ጥቅም መሆኑን “አሁን እየጠየቅን ያለነው ስለአንዱዓለም ወይም ስለአንድነት አይደለም። ስለኢትዮጵያውያን ነው” በሚል ገልጸውታል።
“ፀረ ሽብር ሕጉ እንዲሻር ነው ወይስ እንዲሻሻል የምትጠይቁት?” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ተወካዮቹ “አንድ አዋጅ ሕገ መንግሥቱን አንዴ ከጣሰ ይሰረዛል። ይህ አዋጅ ግን እስከ15 ጊዜ ሕገ መንግሥቱን ስለሚጥስ መሰረዝ አለበት” ብለው መልሰዋል። “ኢትዮጵያ የውጭ ሽብር ስጋት ቢኖርባትም አዋጁ ዜጎችን ለማፈን የወጣ ነው። ማሰብም ሳይቀር ይከለክላል” ብለውታል።
“የሰልፍ ፈቃድ ብትከለከሉስ?” ለሚለው ጥያቄ ደግሞ “ሕግ ማሳወቅ እንጂ ፈቃድ መጠየቅ አይጠይቀንም። ትግላችን ሰላማዊ ነው፣ አይቆምም” ብለዋል።
*********
Source: Fenote – June 20, 2013, titled “አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ሕዝባዊ ንቅናቄ በይፋ ጀመረ”.
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…