የውጭ ጉዳይ ሚ/ር የግብጽን አምባሳደር ጠርቶ ማብራሪያ ጠየቀ

ኢትዮጵያ በመከባበርና በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ እንደምታራምድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

ኢትዮጵያ ከጎረቤት እና ከሌሎችም አገሮች ጋር በመከባበርና በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ በጽናት ስታራምድ መቆየቷ ሚኒስቴር መስርያ ቤቱ አስታውቋል፡፡

በመሆኑም በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በግብጽ ዘንድ ሰፍኖ የቆየውን ጥርጣሬ ለማስወገድ ግድቡ ግብጽንም ሆነ ማንኛውንም የታችኛውን ተፋሰስ አገር እንዳይጎዳ የሚያረጋግጥ የግብጽ፣ የሱዳን፣ የኢትዮጵያ እና አለም አቀፍ ባለሙያዎች የሚገኙበት አጣሪ ቡድን እንዲቋቋምና ሪፖርት እንዲያቀርብ ሃሳብ አቅርባ ስራው ሲሰራ ቆይቷል፡፡

የአጣሪ ቡድኑ ስራውን ሰርቶ ግድቡ በታችኛው ተፋሰስ አገሮች ላይ የሚፈጥረው ችግር እንደሌለ ባረጋገጠበት ማግስት አንዳንድ የግብጽ ባለስልጣናትና የፖለቲካ ድርጅቶች ተቀባይነት የሌለውና በሁለቱ አገሮች መካከል ተጀምሮ የነበረውን መልካም ግንኙነት የሚያሻክር ፕሮፓጋንዳና ቅስቀሳ ማድረጋቸው የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ኣሳዝኗል፡፡

ባለፉት ጥቂት ቀናት የኢትዮጵያ መንግስት ችግሩ ወደተባባሰ ሁኔታ እንዳይገባ በትእግስት ለማለፍ ቢሞክርም ይህ ገንቢ ያልሆነ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ አሁንም ቀጥሏል፡፡ በመሆኑም በትላንትናው ግንቦት 27 / 2005 ዓ.ም የግብጽ አምባሳደር ወደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተጠርተው ስለዚህ ሁኔታ በአስቸኳይ የመንግስታቸውን አቋም ጠይቀው እንዲሰጡ ተነግሯቸው ምላሽ በመጠበቅ ላይ ነው፡፡

አገራችን አሁንም ዋነኛ ትኩረቷ ድህነትን ማሸነፍ እና ለዚሁ አመቺ ሁኔታ የሚፈጥር ከሩቅና ቅርብ አገሮች የወዳጅነት ግንኙነት መፍጠር በመሆኑ ከግብጽ ጋር የተጀመረውን የትብብር ግንኙነት በዚሁ መርህ መሰረት አጠናክራ መቀጠል ትሻለች፡፡ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድቡ ለአገራችን እድገት መፋጠን ከሚያደርገው አስተዋጽኦ በተጨማሪ ግብጽንም ጨምሮ ለሌሎች ጎረቤት አገሮች ያለውን ጠቀሜታ አሁንም በድጋሚ ማስታወስ ትፈልጋለች፡፡

ምንጭ፡- ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

9.14540.489673
Daniel Berhane

Daniel Berhane

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago