በደቡብ ሱዳን ያሉ ኢትዮጵያዊያን መንግስታቸው እንዲታደጋቸው ይሻሉ

(የዚህ ዜና ምንጭ ቪኦኤ ነው – መጋቢት 21/2006)

ደቡብ ሱዳን፤ ማላካል ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እጅግ በከበደና አደገኛ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ አስታወቁ፡፡

ኢትዮጵያዊያኑ ደቡብ ሱዳን ውስጥ የሚገኙት ከሃገሪቱ ነፃ መውጣት ጋር ተያይዞ የአካባቢው ሃገሮች ዜጎቻቸው ያለድንበር፣ ጉምሩክና ሌላም ቁጥጥር እየገቡ የአዲሲቱን ሃገር ምጣኔ ኃብት እንዲያጎብቱ ለማገዝ አስበው በወሰዱት እርምጃ እንደነበር ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ገልፀዋል፡፡

በተለይ ሰሞኑን የአፐር ናይል ግዛት ዋና ከተማ ማላካል በተቃዋሚዎች ቁጥጥር ሥር ከወደቀች ወዲህ ኢትዮጵያዊያኑ ብዙ በደልና እንግልት እንደደረሰባቸው፤ በሴቶችም በወንዶችም ላይ ጥቃት እንደሚፈፀም፣ እስከ ሐሙስ፣ ታኅሣስ 17 / 2006 ዓ.ም ባለው ጊዜም ቢያንስ የሰላሣ ኢትዮጵያዊያን ሕይወት መጥፋቱን ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጁባ እንደነበሩ መስማታቸውን፤ እንዲሁም ጁባ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ደውለው ያሉበትን ሁኔታ መናገራቸውንና ምንም የመፍትሔ ምላሽ አለማግኘታቸውን እነዚሁ በጭንቀት ላይ ነን የሚሉ የአፐር ናይል ስቴት ኢትዮጵያዊያን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥትም እንዲደርስላቸውና ከዚያ በአፋጣኝ እንዲያወጣቸው ጠይቀዋል፡፡

ለተጨማሪ ዝርዝር የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ::

*******

*******

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

more recommended stories