ሉሲ ከ5 ዓመት የአሜሪካ ቆይታ በኋላ ዛሬ አዲስ አበባ ገባች

ሐምሌ 29/1999 ምሽት 1፡30 ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ የተጓዘችው ሉሲ ዛሬ ሚያዝያ 23/2005 ከረፋዱ 4፡20 ላይ አዲስ አበባ ገብታለች፡፡

ሉሲ ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ስትደርስ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ፣ ፕሮፌሰር ዶናልድ ጆሀንሰንና ሌሎች ግለሰቦች አቀባበል አድርገውላታል፡፡Lucy-discovered-in-1974-in-Ethiopia-is-a-3.2-million-year-old-female-of-the-early-human-species.jpg

ከሉሲ ጋር ወደ አሜሪካ ተጉዘው የነበሩ ሌሎች 148 ቅርሶችም ሚያዝያ 22/2005 ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

ሉሲ ወይም ድንቅነሽ ወደ አሜሪካን የሄደችው ለአምስት ዓመት ቆይታ ሲሆን አሜሪካን በነበረችበት ወቅት በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሀገሪቱ ነዋሪዎችና ጎብኝዎች ተመልክተዋታል፡፡

በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ ሉሲ በህዝብ ለህዝብና የመንግስታት ግንኙነት ላይ አምባሳደር ሆና ማገልገሏ ተገልጿል፡፡ ከጎብኝዎችም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት ተችሏል፡፡

ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎችም በቅርስ አያያዝና ጥናት፣ በቅርስ አውደ ርዕይ ዝግጅትና መሰል ዘርፎች ከአሜሪካዊያን ባለሙያዎች ጋር የልምድ ልውውጥ ማድረግ ችለዋል፡፡

የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን እንዳስታወቀው ሉሲ ከግንቦት 1 እስከ ግንቦት 6/2005 ድረስ ለህዝብ እይታ ትቀርባለች፡፡ ከዚያም ለበለጠ ሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር አመቺ በሆነ ቦታ እንድታርፍ ይደረጋል፡፡

የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር አቶ አሚን አብዱልቃድር ሉሲ ወደ አሜሪካ ከመጓዟ በፊት ሲቲ ስካን የተነሳች በመሆኗና በርክክቡ ወቅትም ለመጀመሪያ ጊዜ በቁፋሮ ያገኟትን የስነ ቅርስ ባለሙያዎች ጨምሮ ሌሎች አለማቀፍ ባለሙያዎች የተገኙ ስለሆነ በማንነቷ ላይ ምንም አይነት ጥርጣሬ የለንም ብለዋል፡፡

Source: ERTA – May 1, 2013. Originally titled “ሉሲ እና 148 ቅርሶች አዲስ አበባ ገቡ“.

Daniel Berhane

more recommended stories