ሱር ኮንስትራክሽን ለህዳሴ ግድብ ቃል የገባውን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ገቢ አደረገ

ሱር ኮንስትራክሽን ኩባንያ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ቦንድ ለመግዛት ቃል የገባውን 25 ሚሊዮን ብር ሙሉ በሙሉ ገቢ አደረገ።

የኩባንያው ዋና ስራ አስከያጅ አቶ ታደሰ የማነ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ የ25 ሚሊዮን ብር ቦንድ ከተረከቡ በኋላ እንደተናገሩት ድርጅቱ  ገንዘቡን በአምስት አመታት ጊዜ ውስጥ ለመክፈል አቅዶ የነበረ ቢሆንም በኩባንያውና በሰራተኞቹ በተፈጠረው ከፍተኛ መነሳሳት ቀድሞ ሙሉ በሙሉ ገቢ አድርጓል።

ኩባንያው ከገዛው የ25 ሚሊዮን ብር ቦንድ መካከል 21 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በድርጅቱ ቀሪው ደግሞ በሰራተኞች የተሸፈነ ነው።

ኩባንያው የህዳሴው ግድብ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

የኩባንያው ሰራተኞች በበኩላቸው ከገንዘብ ድጋፍ ባሻገር በሙያቸው አገልግሎት ለመስጠትም ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ባህረ ሱር ኮንስትራክሽን ኩባንያና ሰራተኞቹ ቃላቸውን በማክበር ላደረጉት ድጋፍ አመስግነዋል።

ለግድቡ ግንባታ ቦንድ ለመግዛት ቃል የገቡ ድርጅቶችና ተቋማትም የሱር ኮንስትራክሽን ኩባንያን ፈለግ በመከተል ገንዘቡን በወቅቱ ገቢ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

ሱር ኮንስትራክሽን ኩባንያ ለ6 ሺ 290 ዜጎች ቋሚና ጊዚያዊ የስራ ዕድል የፈጠረ ተቋም ነው።
********
ምንጭ፡- ኢዘአ – ሚያዚያ 4/2006  ርዕስ ሱር ኮንስትራክሽን ኩባንያ ቦንድ ለመግዛት ቃል የገባውን 25 ሚሊዮን ብር ሙሉ በሙሉ ገቢ አደረገ

Curated Content

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago