ሙክታር ከድር የኦህዴድ ሊቀመንበር – አስቴር ማሞ ምክትል ሆነው ተመረጡ

የኦሮሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት(ኦህዴድ) ማዕከላዊ ኮሚቴ ድርጅቱን የሚመሩትን መሪዎች መረጠ።

በምርጫውም አቶ ሙክታር ከድር የድርጅቱ ሊቀመንበር፣ወይዘሮ አስቴር ማሞ ምክትል ሊቀመንበር ሆነዋል።

አቶ ሙክታር በፌዴራል መንግሥት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር አስተባባሪነትና በሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነት በማገልገል ላይ ናቸው።

ወይዘሮ አስቴር የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ሰርተዋል።

ድርጅቱን በሊቀመንበርነት የመሩት አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ በጤና ችግር ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው ይታወሳል።

አቶ ዓለማየሁ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድርነት መምራታቸውን ኢዜአ በዘገባው አስታውሷል።

የክልሉ መንግሥት ምክር ቤት(ጨፌ ኦሮሚያ)በሚጠራው ጉባዔ የክልሉን ርዕደ መስተዳድር ይሰይማል ተብሎም ይጠበቃል።

**********
ምንጭ፡- ኢዜአ – የካቲት 20/2006

Curated Content

Content gathered and compiled from online and offline media by Hornaffairs staff based on relevance and interest to the Horn of Africa.

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago