የኦሮሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት(ኦህዴድ) ማዕከላዊ ኮሚቴ ድርጅቱን የሚመሩትን መሪዎች መረጠ።
በምርጫውም አቶ ሙክታር ከድር የድርጅቱ ሊቀመንበር፣ወይዘሮ አስቴር ማሞ ምክትል ሊቀመንበር ሆነዋል።
አቶ ሙክታር በፌዴራል መንግሥት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር አስተባባሪነትና በሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነት በማገልገል ላይ ናቸው።
ወይዘሮ አስቴር የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ሰርተዋል።
ድርጅቱን በሊቀመንበርነት የመሩት አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ በጤና ችግር ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው ይታወሳል።
አቶ ዓለማየሁ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድርነት መምራታቸውን ኢዜአ በዘገባው አስታውሷል።
የክልሉ መንግሥት ምክር ቤት(ጨፌ ኦሮሚያ)በሚጠራው ጉባዔ የክልሉን ርዕደ መስተዳድር ይሰይማል ተብሎም ይጠበቃል።
**********
ምንጭ፡- ኢዜአ – የካቲት 20/2006
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…