(ባሃሩ ይድነቃቸው)
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አመቺነት የአባይ ወንዝን ተፈጥሯዊ አቅጣጫ የማስቀየር ስራ ሲከናወን ቆይቷል ።
ይህ ስራ ተጠናቆ ዛሬ ወንዙ በይፋ ተፈጥሯዊ አቅጣጫውን ቀይሯል ።
የወንዙን ተፈጥሯዊ አቅጣጫ የማስቀየሩን ተግባር ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀ ስነ ሰርዓት ላይም የተገኙት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እለቱ አባይን በፈለግንበት መስመር የምናስኬድበት ቀን ብለዋል ።
“ስር በሰደደ ድህነታችን ምክንያት በፈለግነው ሳይሆን እሱ ባሰኘው መንገድ ሲፈስ ቆይቷል” ያሉት አቶ ደመቀ ፥ “አሁን አባይን በመዳፋችን ውስጥ እንዲገባ አድርገናል” ነው ያሉት ።
አባይ እጣ ፈንታው በእጃችን እንዲሆንና በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ እኛ በመራንበት እንዲጓዝ ማድረጋችን የኢትዮጵያንና የአፍሪካን ህዳሴ የሚያመላክት መሆኑንም ተናግረዋል ።
እንደ አቶ ደመቀ ንግግር እለቱም ከግንቦት 20 ጋር መገናኘቱም ልዩ ትርጉም ያለው ይሆናል ።
በዚህ ታሪካዊ እለት ከአገሪቱ ማህፀን ፈልቆ ኢትዮጵያን የበይ ተመልካች ያደረገው አባይ በኢትዮጵያ መዳፍ ላይ መውደቁ እለቱን የድርብርብ ታሪክ ባለቤት ያደርገዋልም ነው ያሉት ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ፥ የዚህ ታላቅ ፕሮጀክት ጠንሳሽ አቶ መለስ ዜናዊ የተሰዉለት ዓላማ የጠራ መሆኑንና የመላውን ህዝብ ድጋፍ ማግኘቱንም ያረጋገጠም ሆኗል ።
አገራዊው ደስታ ሙሉ የሚሆነው ግድቡ ስራ ሲጀመር በመሆኑም ህዝቡ ድጋፉን እንዲቀጥል ጠይቀዋል ።
በግድቡ ግንባታ ሂደት አራት አበይት ክንውኖች አሉ ያሉት የኢፌዴሪ የውሃና ኤኔርጂ ሚኒስትር አቶ ዓለማየሁ የተገኑ ደግሞ ፥ ዛሬም በይፋ የተከናወነው የወንዙን ተፈጥሯዊ አቅጣጫ የማስቀየር ስራ አንዱ ነው ብለዋል ።
የወንዙ ተፈጥሯዊ አቅጣጫ መቀየር የአይችሉም አመለካከትን በከፍተኛ ደረጃ የሚያከስምና ኢትዮጵያ ወንዙን ማልማት እንደምትችል የሚያሳይም ነው።
አቅጣጫውን ማስቀየር ለምን አስፈለገ ?
ወንዙ የሚገኘው ግድቡ በሚገነባው መሃል ላይ ሲሆን ፥ ወንዙ እየፈሰሰ ግድቡን መገንባት የማይቻል በመሆኑ ነው ተፈጥሯዊ አቅጣጫውን ማስቀየር ያስፈለገው ።
አቅጣጫ የማስቀየሩ ስራ በግንብታው ሂደት አስቸጋሪ ስራ መሆኑን የሚናገሩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ምህረት ደበበ ፥ ስራውም እጅግ ከፍተኛ ጥረት ውጤት መሆኑን አመልክተዋል ።
የግድቡ ፕሮጀክት ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ስመኘው በቀለ በበኩላቸው ፥ የወንዙን አቅጣጫ የማስቀየሩ ስራ ከተያዘለት ጊዜ በሁለት ሳምንት ቀደም ብሎ መጠናቀቁን በመጠቆም ይህ ስራዎች ከተያዘላቸው ጊዜ ቀደም ብለው በፍጥነት እየተከናወኑ መሆናቸውን እንደሚያሳይ ነው ያመለከቱት ።
በአሁኑ ወቅትም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 21 በመቶ መጠናቀቁ ተመልክቷል ።
*************
Source: Fana – May 28, 2013, titled “አባይ ተፈጥሯዊ አቅጣጫውን ቀየረ”.
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…