(አብዱረዛቅ ካፊ)
የኢትዮጲያ ሶማሌ ክልላዊ መንግስት ቴሌቪዠን ጣቢያ የአማርኛ ቋንቋ ስርጭት መጀመሩንና ይህም የቴሌቪዥንኑን ተመልካች ቁጥር እንደሚጨምር እንደሚጠበቅ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አክሎ አስታውቋል።
የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ ኢንጅነር ኢድሪስ ኢስማኢል ጣቢያው የአማርኛ ቋንቋ ስርጭት መጀመሩ በርካታ ጉዳዮች ታሳቢ ተደርጎበት እንደሆነም ገልጿል።
በሀገሪቷ ሰፊ ተናጋሪ ያለው አማርኛ ቋንቋ በጣቢያው እንድንጀምር ባለፉት ወራት በርካታ ዝግጅቶችና የዳሰሰ ጥናት የተደረገበት ሲሆን ይህም የሀገሪቷ የስራ ቋንቋ የሆነውን አማርኛ ቋንቋ ለአማርኛ ተናጋሪ ለሆኑት ተመልካቾች ተደራሽ ለማድረግ ሲባል ነው ብለዋል ኢንጅነር ኢድሪስ ኢስማኢል።
ኢንጅነር ኢድሪስ ኢስማኢል አክለውም የክልሉ ቴሌቪዥን በክልሉም ሆነ በአምስቱ የአለም አህጉራት ለሚኖሩ የክልሉ ተወላጅ ዲያስፖራ ማህበረሰብንና ነዋሪዎች ስለሀገራቸውና ስለተወለዱበት ክልላቸው መረጃ በማሰራጨትና ተደራሽ በማድረግ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ መሆኑን አስታውሰዋል።
በተጨማሪም በክልሉ መንግስትና ህዝብ እየተከናወኑ ያለው የልማት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እንዲሁም በአጠቃላይ በክልሉ ላለው የቆዳ ስፋትና የክልሉ የተፈጥሮ እምቅ ሀብቶቻችን እንደሁም በክልሉ ላለው የቱሪዝም መስህቦችና ታሪካዊ ቅርሶችን ለክልሉ የአማረኛ ተናጋሪና ለአጠቃላይ የሀገራችን ህዝብ የክልሉን ዘርፈብዙ የልማት አውተሮችን ግንዛቤ ለማስጨበጥና የክልሉን ገጽታ ግንባታ ስራዎችን የአማርኛ ቋንቋ ስርጭቱ በከፍተኛ ደረጃ ያግዛል ብሏል ኢንጅነር ኢድሪስ።
በመጨረሻም የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ ኢንጅነር ኢድሪስ ኢስማኢል ለክልሉ አማርኛ ተናጋሪ ማህበረሰብን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
*********
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…