‘ኢትዮጵያ  የአባይ ወንዝን መጠቀሟን አጠናክራ ትቀጥላለች’ አቶ መለስ ዓለም

(የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር – ፕሬስ መግለጫ)

ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን ፍትሐዊ  እና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ፣  ዓለም ዓቀፍ ህግን አክብራ የአባይ/ናይል ወንዝን የህዝቧን የአሁን እና የወደፊት ትውልድ ፍላጎት ለማሳከት መጠቀሟን አጠናክራ እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አቶ መለስ ዓለም ገለጹ።

ቃል አቀባዩ ዛሬ በሰጡት ጋዜጠዊ መግለጫ እንደገለፁት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብት ለመጠቀም የማንንም ፈቀድ አትጠይቅም።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ረሀብን ለማጥፋት የምታከናውነው ፕሮጄክት መሆኑን ጠቅሰው ይህ ፕሮጀክት የኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያ በመሆኑ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው።

የግድቡ መገንባት ጥቅሙ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ግብፅና ሱዳንን ጨምሮ ለሌሎች ጎረቤቶቻችን ጭምር መሆኑንም አቶ መለስ ገልፀዋል፡፡

ይህም ግድቡን አፍሪካን ከማስተሳሰር አንፃር አፍሪካዊ ፕሮጀክት ያደርገዋል፡፡ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ ከሱዳን እና ግብጽ ጋር ተባብራ መስራቷን ትቀጥላለች።

በዚሁም ኢትዮጵያ የመርሆዎች መግለጫ ስምምነቱ (DoP) በሁሉም ሀገራት እንዲከበር በአጽንኦት ታሳስባለች ብለዋል አቶ መለስ፡፡

Photo – Meles Alem, Spokesperson of Ethiopian Ministry of Foreign Affairs

የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ከአሜሪካው አቻቸው ሬክ ቴሌርሰን፣ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር አምባሳደር ዶናልድ ያማማቶና ሌሎች የኋይ ትሀውስ ባለስልጣናት ጋር በአካባቢያዊና በአለም ዓቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡
በውይይቱም ሁለቱ አገራት ስትራቴጅክ አጋር መሆናቸውን እና በአፍሪካ ቀንድ ሠላም እና የጸረ ሽብር ትግሉ ላይ በጋራ እንደሚሠሩ ቃል አቀባዩ ገልፀዋል። ኢትዮጵያ በደቡብ ሱዳን የሠላም ሂደት  እና በሶማሊያ እያደረገችው ያለችው አዎንታዊ አስተዋፅኦንም አድንቀዋል።

በኤርትራ መንግስት ላይ በተበበሩት መንግስታት የተጣለው ማዕቀብ መቀጠሉ ለአካቢቢው አገራት ሠላም በጎ አስተዋጵዖ እንደሚኖረው ቃል አቀባዩ ገልፀዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

ቃል አቀባይ ጽ/ቤት 

ህዳር 14 ቀን 2010 ዓ.ም.

********

Guest Author

Guest Author

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago