​ግለሰቦችን በመግደል የሚመጣ ለውጥ የለም

(ካሕሳይ ቃሉ ከአዲስ አበባ)

ባለፈው ሳምንት የነሻዕቢያ ፣ ኦነግና ግንቦት ሰባት የከፈትዋቸው የፌስ ቡክ አካውንቶች ጄኔራል ሳሞራ ሞቱ ብለው በቅብብሎሽ ሲያናፍሱ ተመለከትኩ፡፡

እነዚህ አቅመ ቢስና ፀረ-ሰላም ሃይሎች ለቀናት ሳይሆን ለሰአታት እድሜ የሌለው የውሸት ጋጋታ ሲነዙ አዲስ ነገር ሆኖ አላገኘሁትም፡፡

ግለሰቦች በመግደል ሰርዓት/አስተሳሰብ መቀየር የሚቻል ቢሆን ኢህአፓና ደርግ በውሸት ሳይሆን በተግባር የገደሉዋቸው ታዋቂ ሰዎች በርካታ ነበሩ፡፡

ገዳዮች በአስተሳሰብና በአላማ ማሸነፍ ሲያቅታቸው በውሸትም ጭምር እገሌ የሚባል ሞተ እያሉ ያወራሉ፡፡

ታላቁ መሪ ክቡር አቶ መለስ ከተሰዋ በኋላም ኢትዮጵያን የተቆጣጠሩዋት ይመስል ያልደለቁት የደስታ ከበሮ አልነበረም ስርዓቱና አስተሳሰቡ ግን የመላ ኢትዮጵያዊያን ስለሆነ አሁንም ድረስ አለ ለወደፊትም ይቀጥላል፡፡

አሁንም ቢሆን ጄኔራል ሳሞራ ተቋም እንጂ ቡድን ወይም ቤተሰብ አይደለም እየመሩ ያሉት፡፡

በመሆኑም ጄኔራል ሳሞራ የራሱ እምቅ አቅምና ብቃት በሰራዊቱ ግንባታ ያለው የላቀ አስተዋፅኦ እንደተጠበቀ ሆኖ በሰራዊቱ ውስጥ ከላይ እስከታች ብቃት ባለው አመራር የተገነባ በአጠቃላይ ሰራዊቱም ባለው ህዝባዊ ወገንተኝነቱ በጉልህ የሚታይ ለህገ-መንግስቱና ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱ በፍፁም ታማኝነት እስከመጨረሻ የሚዋደቅ በዚህም በህዝብ ዘንድ አሜኔታና አድናቆት ያተረፈ ጠንካራ ሰራዊት እንጂ የእምቧይ ካብ አይደለም በጩኾት የሚፈርስ፡፡

ስለሆነም ለአገራችን ብሄር ብሄረሰቦችም ሆነ በአገራችን እድገት ለምንኮራው ዜጎች በህግደፍ፣ በኦነግና ግንቦት ሰባቶች የኛ ጀግና፣ የኛ ሰራዊት ቢባል ነበር ሞት የሚሆነው ስለሆነም እናንተ ውሸታችሁ ቀጥሉ ሰራዊቱ ደግሞ ጀግና ቢሰዋ ጀግና ይተካል እያለ በህገ-መንግስቱና በህዝብ የተሰጠውን ተልእኮ በአግባቡ ይፈፅማል ፡፡

ለኢትዪጵያ ህዝቦች የደስታ ለፅንፈኞቹና ለፀረ-ሰላም ራስ ምታት የሆነ ሌላ ተጨማሪ ዜና እንዲሆናችሁ በኢትዮጵያ የሚገኘው የአቢሲንያ ሽልማት የተባለ ለአገራቸው ታላቅ ስራ ለሰሩ የሚሸልም አለም አቀፍ የሽልማት ድርጅት የዘመኑ ታላቅ ሰው በሚል የክቡር /ሎሬት/ H:E ሽልማት እናንተ ሞተ ባላችሁበት ማግስት ጥቅምት 19 ቀን 2010 ዓ.ም ለጀነራል ሳሞራ ሽልማት አበርክቶላቸዋል፡፡

የልማት፣ የሰላም የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታችን ሳይሸራረፍ ይቀጥላል!!

ክብርና ሞገስ ለሰማእታት!!

********

Guest Author

Guest Author

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago