የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር "ዕጣው አልደረሳችሁም" ተብለው ከዕጩነት ውጭ ሆነዋል ተባለ

በግንቦት ወር በሚካሄደው 5ኛ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ

ሰማያዊ ፓርቲ ለማወዳደር ያዘጋጃቸው አንዳንድ ዕጩዎች ዕጣ ስላልደረሳችው በዕጩነት እንዳይቀርቡ መደረጋቸውን ፓርቲው ገለፀ፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ በዌብ ሳይቱ እና በፌስቡክ ገጹ ባሰራጨው ዘገባ ስሞታውን እንደሚከተለው አሰምቷል፡፡

———

አዲስ አበባ ከተማ ወረዳ 5 ለመጭው ምርጫ ለተወካዮች ምክር ቤት ሰማያዊ ፓርቲን ወክለው ሊቀርቡ የነበሩት የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹ከቀረቡት 17 ዕጩዎች መካከል በተጣለ ዕጣ ወድቀዋል›› በመባላቸው ለመጭው ምርጫ በዕጩነት እንዳይቀርቡ መደረጋቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል በዕጩነት በቀረቡበት ወረዳ 5 የምርጫ ጣቢያ ኢህአዴግ፣ የትግስቱ አንድነት፣ ቅንጅትን ጨምሮ ሌሎች ስድስት የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ያለ ምንም ዕጣ አልፈዋል የተባለ ሲሆን ‹‹የሚያልፉት በዕጣ ነው›› የተባሉት ሰማያዊን ጨምሮ 11 የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች መካከል ሰማያዊና ሌሎች አራት የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ‹‹ዕጣ አልወጣላቸውም፡፡›› ተብሏል፡፡

ስለ ጉዳዩ ያነጋገርናቸው የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹ሰማያዊ ህዝብ ውስጥ በሰፊው እየገባና እያንቀሳቀሰ ያለ ግንባር ቀደም ፓርቲ ነው፡፡ እንደ ኢህአዴግ ያሉን ጨምሮ ዕጣ ውስጥ አይገቡም፡፡ ሰማያዊ ደግሞ ይህ ነው የሚባል እንቅስቃሴ ከማያደርጉት ፓርቲዎች ጋር ዕጣ ውስጥ ገብቶ ወደቀ መባሉ ዴሞክራሲ ከጅምሩ ጀምሮ የህዝብ ድምጽ ሆኖ እያለ በእኛ አገር ሎተሪ ሆኗል ማለት ነው፡፡›› ብለዋል

ሊቀመንበሩ አክለውም ‹‹ሂደቱ ምንም ይሁን ምን አንድን ፓርቲ ወይንም ተወካይን ህዝብ ነው መምረጥ ያለበት፡፡ ህዝብ የሚፈልገውና የሚመረጥ ፓርቲ ነው ለምርጫ መቅረብ ያለበት፡፡ አሁን ግን እየተባለ ያለው በአንድ በኩል ህዝብ የማይፈልገው ያለ ዕጣ ሲገባ፣ በሌላ በኩል ህዝብ የሚፈልገው ሰማያዊን የመሰለ ፓርቲ ዕጣ ውስጥ ገብቶ አላለፈም እየተባለ ነው፡፡ በአንድ በኩል ህዝብ የተማረረባቸው ያለ ቅድመ ሁኔታ ህዝብን እንደሚያንቀሳቅስ የሚታወቀው ሰማያዊ ደግሞ ህዝብ ስፈለገው አሊያም በጥንካሬው ሳይሆን በሎተሪ ወድቀሃል ተብሏል›› ሂደቱ የተሳሳተ ነው ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

———

በአዲስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ሰማያዊ ፓርቲን ወክላ ለተወካዮች ምክር ቤት በዕጩነት ቀርባ የነበረችው ወይንሸት ሞላን ጨምሮ ሌሎችም አዲስ አበባ ውስጥ ሰማያዊ ፓርቲን ወክለው ለተወካዮች ምክር ቤት በዕጩነት የቀረቡ ዕጩዎች ‹‹ዕጣው ስላልደረሳችሁ አትወዳደሩም›› መባላቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ከወይንሸት ሞላ በተጨማሪ ብሌን መስፍንና አማኑኤል አዱኛ የተባሉ የሰማያዊ ዕጩዎች ‹‹ዕጣው አልደረሳችሁም›› ተብለው ከዕጩነት ውጭ ሆነዋል፡፡

ወይንሸት ሞላ ‹‹ዕጣው አልደረሰሽም›› በተባለችበት የምርጫ ጣቢያ የክልል ፓርቲዎችን የወከሉ ዕጩዎች አልፈዋል የተባሉ ሲሆን ወይንሸት ‹‹የክልል ፓርቲዎች ድምጽ ያሰባሰቡት በየክልሉ እንጅ አዲስ አበባ አይደለም፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ደግሞ ሐገራዊ ፓርቲ ነው፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ መራጭ የሌላቸው ፓርቲው በዕጣ አለፉ ተብሎ ሐገራዊ ፓርቲ የሆነው ሰማያዊ ወድቋል መባሉ ያለንበትን ስርዓት በድንብ የሚያጋልጥ ነው፡፡›› ስትል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻለች፡፡

በወረዳ 7 17 ፓርቲዎችን የወከሉ ዕጩዎች የቀረቡ ሲሆን 12 ያለፉ ሲሆን ሰማያዊን ጨምሮ ሌሎች አምስት ፓርቲዎች ‹‹ዕጣው አልደረሳችሁም›› ተብለዋል፡፡ በወቅቱ ወይንሸት ሞላ ለምርጫ አስፈጻሚዎች ‹‹12 ፓርቲዎችን በዕጣ አልፋችኋል ለማለት ለ80 ፓርቲ ፈቃድ መስጠት ለምን አስፈለገ?›› የሚል ጥያቄ ያቀረበች ሲሆን የምርጫ አስፈጻሚዎችም ‹‹ይህ ከምርጫ ቦርድ የመጣ ትዕዛዝ ነው፡፡ መዝግቡ የተባልነውን ነው የመዘገብነው›› የሚል መልስ እንደተሰጣት ገልጻለች፡፡

**********

ተዛማጅ፡- ከገደብ በላይ ዕጩዎች ሲመዘገቡ – ባለፈው ምርጫና በዕጣ መሠረት ይለያሉ፡- የምርጫ ቦርድ ኃላፊ

Daniel Berhane

Daniel Berhane

Recent Posts

ኪዳነ ኣመነ – እንደህዝብ አንድ ሆነናል ያስቸገረን የህወሓት አስተሳሰብ ነው

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…

5 years ago

ኪዳነ አመነ – ለትግራይ ታላቅነት ሼምለስ ሆነን እንሰራለን

ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ትዴት ኢትዮጲያዊ ማንነት ብቻ እንዳለ ነው የሚያምነው (video)

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…

5 years ago

መኮንን ዘለለው – ኢሳት የትግራይ ህዝብ እንዲጠፋ ነው የሰራው (Video)u

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…

5 years ago

የበረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ መታሰር -ሕጋዊ ወይስ ፖለቲካዊ እርምጃ?

(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…

5 years ago

ኣስተያየት በ’ኣብራክ’ ልብወለድ ድርሰት ላይ

(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…

5 years ago