ፕሬዝዳንቱ አዲሱ አመት የመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ማብቂያና የሁለተኛው ዘመን እቅድ ለመጀመር ከፍተኛ ዝግጅት የሚደረግበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው ያሉ ሲሆን ሃገሪቱ በሁሉም ዘርፍ የደረሰችበትን የለውጥ ጎዳና ለማስቀጠልና የተገኘውን ውጤት አጎልብቶ ወደ ሌላኛው ምዕራፍ የምንሸጋገርበት፣ እየተመዘገቡ ያሉ የልማት የሰላምና የዴሞክራሲ ውጥኖች የሚሳኩበት፣ የዜጎች የኑሮ ደረጃ አሁን ካለበት በተሻለ አኳኋን ከፍ የሚልበት፣ ዜጎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ የሚያረጋግጡበት እንደሚሆን ይጠበቃል ብለዋል፡፡
አዲስ አመትን ስናከብር በአዳዲስ ራእይና በአዲስ መንፈስ የምንነሳሳበት እንደመሆኑ በአዲስ የሃገር ፍቅርና መንፈስ በመነሳሳት ሃገሪቱ እያስመዘገበች ያለውን ለውጥ ይበልጥ ለማሳካት የመንሰራበት እና ለእድገትና ትራንስፎርሜሽን ሁላችንም ለአንድ አላማ የምንቆምበት ይሆናል ብለዋል፡፡
ፕሬዝዳንት ሙላቱ አክለውም በዓሉን ምክንያት በማድረግ ለ995 የፌደራል የህግ ታራሚዎች በምህረት እንዲፈቱ ይቅርታ ማድረጋቸውን ገልፀው፤ ታራሚዎችም ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ ማህበረሰቡንና ሃገራቸውን በልማት በመደገፍ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አስተላልፈዋል ።
ፕሬዝዳንቱ በቅርቡ በሃገር የደህንነት ሃይሎች የተያዘው የግንቦት 7 የሽብር ቡድን መሪ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ “የይቅርታ ደብዳቤ ማስገባቱን” በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ: ስለተባለው ጉዳይ እስከ አሁን የሰሙት ነገር እንደሌለ ጠቅሰው በጥያቄው እንደተባለው የይቅርታ ደብዳቤ ገብቶ ከሆነ በሕገ መንግስቱ በተቀመጠው አሰራር መሰረት ከይቅርታ ቦርዱ ሲላክ ይስተናገዳል ብለዋል፡፡
********
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 2 - ለውጥ…
ከብሔራዊ ባይቶ ኣባይ ትግራይ (ባይቶና) አመራር ኪዳነ አመነ ጋር የተደረገ ቃለ-ምልልስ ክፍል 1 - ለትግራይ…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ (ክፍል 2)- ስለትዴት…
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት) አመራር መኮንን ዘለለው ከሆርን አፌይርስ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ (ክፍል 1) -…
(የማነ ካሣ) እንደሚታወቀው አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያያዘ…
(መርስዔ ኪዳን - ሚኔሶታ) ኣብራክ የተባለውን የሙሉጌታ ኣረጋዊ መጽሓፍ ኣነበብኩት። ኣገራችን ከሊቅ አስከደቂቅ በዘውጌ ብሄርተኝነት…